Thursday, February 27, 2014

መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ ተሰጣቸው

ከዚህ በፊት መምህር ግርማ ወንድሙ ከ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አገልግሎት መታገድ በተያያዘ የቀድሞው የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አስተዳዳሪ መላከ ሰላም ዘላለም እሰይ ስለ መምህር ግርማ ምን ይላሉ? በሚል አገልግሎታቸው የተቋረጠበትን መልካም ያልሆነ ድርጊት እና የመምህር ግርማ ወንድሙን እውነተኛ ማንነት የሚያስረዳ ቃለምልልስ አስደምጠን ነበር:: ከታች በተያያዘው ደብዳቤ ላይ መላከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ የተሰጣቸው መሆኑን ያሳያል::
ደብዳቤው እንደሚከተለው ይነበባል
ቀን 26/12/2005
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ የወንጌል አገልግሎትና እንዲሁም የሕሙማን ሐብተ ፈውስ እንዲሰጡ ከብጹዕ ወቅዱስ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልካም ፍቃድ የተፈቀደልዎት ሲሆን ይህን አውቀው በፍቅር በሰላም እንዲያገለግሉ እናስታውቃለን::
በክርስቶስ ሰላም
ተጨማሪ መረጃ
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13144
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ማናቸው?

VDC part 26 ወጥቷል::

የቀድሞው የእገዳ ደብዳቤ

በሮም ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የተላከ ደብዳቤ 25/09/2006