Wednesday, June 24, 2015

ተናገሩ ድንቅ ስራዉንም መስክሩ

"ተናገሩ ድንቅ ስራዉንም መስክሩ"
ከአዲስ አበባ 650 ኪሎ ሜትር መጓዝ ግድ ይላል ታላላቅ የገጠር ከተሞች አሉ በተለይ ከጊቤ በረሃ እንደተሻገርን ግራና ቀኝ አይናችንን እንዲንከራተት ፈቀድንለት ወሊሶ፣ ወልቂጤ፣ ጅማ፣ በደሌ፣መቱን እንዳለፍናት ጎሬ ስንደርስ አንድ ሐውልት ከቤተክርስቲያኑ በር አካባቢ በግርማ ሞገስ ተሸፍኖ ቆሟል፡፡




"ብጹዕ አቡነ ሚካኤል"
ይባላሉ ፋሽስት ኢትዮጵያን በወረራት ጊዜ ልክ እንደ አቡነ ጴጥሮስ በተመሳሳይ ጊዜ ህዝቤም መሬቱም አይገዛልህ ብለው በማውገዛቸው በግፍ በመትረየስ ተረሽነዋል ተገድለዋል፡፡ሰኔ23
ከፓትሪያርኩ ጀምሮ ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት የሐውልት
ምርቃትና የሰማዕትነትን ስም ያገኛሉ፡፡
ይህንን በረከት ለመሳተፍ ከመላው ኢትዮጵያ በርካታ ህዝብ ከየአካባቢው ይጎርፋል፡
እኛም ተገኝተን ሰፊውን ታሪክ ያኔ እናቀርባለን፡፡
የኢሉባቡር ሀገረ ስብከት ይህንን ታላቅ በዓል
ሐይማኖቱንና ታሪኩን የሚወድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ
እንዲገኝ ጥሪ አቅርበዋል፤ይኸው ይድረሳችሁ፡፡

በተለይ ጅማን ይዛችሁ የኢሉባቡር ክልል በግራና
በቀኝዎት ጥቅጥቅ ያለው ደን የተለያዩ የዕጽዋት
ዘር ያለበት ሲሆን በተለይ አመቱን መሉ በአረንጓዴ የተሸፈነው እጅግ ውብና ማራኪ ስፍራ፦ ቀረሮ፣ሰሳ፣ዋንዛ፣ማንጎ፣አቡካዶ፣ቡና፣በቆሎ የመሳሰሉት ተክሎች ይገኙበታል፤
አንዳንዴም እንደው የራበው
መንገደኛ ጫካ ውስጥ ገባ ብሎ ቢወጣ የእለት ጉርሱን አያጣም ይባላል፡፡
አሁን ትንሽ ጉዞ ነው የቀረን ጉመሮ ሻይ ቅጠል ሰፊ የእርሻ መሬት ላይ ደርሰናል
"የመስሊሟ ታሪክ ጀመረ"
፦የዛሬ 3ወር እዚህ ቦታ ላይ
14ሰው የተፈቀደለት ዶልፊን መኪና የዛን ዕለት ግን
27ሰው ጠቅጥቆ ከመቱ ወደ ኡካ ከተማ ጉዞ ጀመረ ፀሐይ ለጨረቃ ፈረቃዋን ቀይራለች ጭለማው በርትቷል የመኪናው ከፍተኛ ፍጥነት ቀጥሏል ከምሽቱ 1ሰዓት ግን ፊለፊቱ ቢራ የጫነ የጭነት መኪና ጋር ፊት ለፊት ተገናኙ ያኔ ነበር እጅግ የአመቱ ዘግናኝ አደጋ ነው የተከሰተው 11ሰዎች ወድያው ላይመለሱ አንቀላፉ ፤ከባድ ጉዳት የደረሰባቸውም አካላቸውን አተዋል ታዲያ "አዋጉ ሠኢድ ኢመማ"
አምቡላንስ እስኪመጣ ከ11አስክሬን ጋር ቅጠል
አልብሰዋት ከሞቱት ጋር ተቆጠረች፤በቆይታ በኋላ
ፊቷ በደም ቢሸፈንም የተረፈው አንድ አይኗ እንደመንቀሳቀስ ሲል የአምፑላንሱ ሹፌር ድንገት
አይቷት ከሞቱት መካከል ለያት ወደ መቱ ሆስፒታል
ሄደች አልተቻለም በኮንትራት መኪና አዲስ አበባ
ጥቁር አምበሳ ሆስፒታል ታከመች፤ እንደ እድል ሆኖ
የተሰበረው እግሯን ሳይጠግኑላት በሚያሳዝን ሁኔታ
ወደ መንደሯ ተመለሰች፡፡
3ወር ሙሉ አትናገርም አትጋገርም ተኝታ ብቻ ማቃሰት መወራጨት ብቻ በሙስሊሞች ባህል ሁሉን አረጉላት መፍትሔ የለም፡፡
አንድ ነገር ቤተሰብ ተማከሩ ይሄ ነገር አንደበቷን የቆለፋት ሰይጣን ሳይሆን አይቀርም ብለው ወደ ቤተክርስቲያን አመሩ አባቶችንም አናግረው ወደ
ቤታቸው ጸሎት እንዲደረግላቸው ተማጸኑ
የቅዱስ ገብርኤልን ጸበል ቤተሰቦቿ በጀሪካን ይዘው
ቀሲስ ትህትና ደግሞ ዳዊታቸውን ሸክፈው አመሩ፡፡
እንግዲህ ሂዱና አህዛብን ሁሉ "በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃቹኃቸው" ያዘዝኳችሁን ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራቹኃቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፡፡
እነሆ እኔ እስከ ዓለም ፍፃሜ ድረስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ፡(ማቴ 28፥28)
እንደ ስርዓተ ቤተክርስቲያን ከዳዊት፣ውዳሴ ማርያም፣ ኪዳንና ትምህርተ ኀቡአት ካዳረሱ በኋላ
ጸበል እረጯት ጆሮዋም እየተከፈተ መጣ ለካ ከመኪናው በወደቀችበት ሰዓት አጅሬ ሰይጣን አግኝቷታል፡፡
ቀሲስ በሥላሴ ስም በድንግል ማርያም
ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እያሉ በመስቀል ይዳብሷታል ኡኡኡ እለቃለሁ አጋንንት ነኝ ጂኒ ነኝ መስቀሉ አቃጠለኝ,,,,,,ቄሱም እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቤተሰብ "አንደበቷ መከፈቱ "ለነሱ እንደ ተአምር ነው በልባቸው ለገብርኤል ተስለዋል::
አሁን ልቀቅ አታሰቃያት ይሉታል ለቅቄ ወዴት እሄዳለሁ? በተረፈው አንድ ዓይኗ ወደ ቄሱ እያፈጠጠ
እያጓራ አንተላይ ወጥቼ ልምጣ እያለ መፎከር ጀመረ መሪጌታ ቀሲስ ትህትና፡ የእሷን ሰላም ማግኘት
እንጂ የአጋንንቱ ዛቻ አላስፈራቸዉም፤ግድ የለም
በእግዚአብሔር ቃል አሸንፍካለው ና!እያሉ ያናዝዙታል
ዳዊታቸውን ትራስጌዋ ላይ አድርገውላት 4ሰዓት ተኩል ላይ አረፍ ትበል ብለው ወደ ባለቤታቸው
ሱቅ ሄዱ፡፡
ከሱቃቸው ጎን ካለው ሻይ ቤት አረፍ እንዳሉ ኬት
መጣ ሳይባል ትልቅ እባብ ይጠመጠምባቸዋል
እስቲ ለአንድ አፍታ እግራችሁን አስቡት ለዛውም መርዘኛ እባብ ግማሽ አካሉ መሬት ሆኖ የተጠመጠመው አንገቱ ጉልበታቸው ላይ ደርሷል፡፡
" እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንደሚል" ያ ልጅቷ ላይ ሆኖ የፎከረዉ አጋንንት ለካ ተከትሏቸዋል፡፡
"እነሆ እባብና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኃለሁ የሚጎዳችሁም ምንም የለም" (ሉቃ 10፥19)
እንዲህ ስገልጽላቹ ቀላል ይመስላል ቀሲስ እንደ ሰዉ ደካማ ናቸውና እየዘለሉ ለማስለቀቅ ብዙ ታግለው ከሳቸው ለቆ ወደ ሚስታቸው ሱቅ እንደተላከ ህፃን የተሳበ ሲገባ አንድ የሻይ ቤቱ ባለቤት ሙስሊም በዱላ ጨፍጭፎ ገደለው፡፡
ወድያው ለሙስሊሞቹ ተነገራቸው በስልክ
(ማሽ አላህ ማሽ አላህ) ተመስገን ለፈጣሪ ምስጋና ይገባው እያሉ የቄሱን እምነት አደነቁ
እኔም ይህ ተአምር ከተከሰተ ከ3ቀን በኋላ ለቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በዓል እዛ ከተማ ተገኝቼ ስለነበር ሁሉንም ታሪክ ከሙስሊሞቹ ሰምቻለሁ፡፡
አንደበቷ የተከፈተውንም አውርቻታለው የምታዩትን ፎቶ አነሽቻታለው በመስቀል በቅባ ቅዱስ ቀሲስ እየጸለዩላት፡፡
ባለፈው የፉጡማ ጂብሪል አዲስ የኦርቶዶክስ እንግዳ ብያቹ ነበር፤ ልክ ነኝ
፨አሚራ የምትባለው ከSISI ነፍሰ በላዎችን መርጣ ወደ ሞት መንገድ ሄደች(ተቀላቀለች)ልብ ይስጥልን፤
፨ፋጡማ ጂብሪል ደግሞ በጥምቀት ወደ ዘላለም ህይወት ሰላምን መርጣ የሥላሴ ልጅነት አገኘች ህይወት የሆነውን የኢየሱስ የክርስቶስን አማናዊ ቅዱስ ስጋውንና አማናዊ ክቡር ደሙን ተቀበለች ዛሬ ማንም የማይቀማትን በጎ እድልን መርጣለችና ለእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ ሆነች፡፡በፎቶ ላይ እንዳያችሁት በሰንበት ትምህርት ቤት መዘመር ጀምራለች፡፡ ሁለቱ ወንድምና እህቶችም ከፉጡማ
ቀደም ብለው ወደ ክርስትናው ገብተዋል፦እንድሪስ መሐመድና አይሻ መሐመድ ናቸው፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን ቀጣይ አንግዶቼ ይሆናሉ፡፡
የፋጡማ አዲስ ስሞ" ናርዶስ ጂብሪል"
"ስመ ክርስትናዋ ወለተ ሰማዕት"
ምስጋና ፦በአገልግሎት አብረውኝ የነበሩ ቀሲስ ታምራት
መ/ር ኤርምያስ አሰፉ፡ መ/ር መላኩ፣ለሰበካ ጉባኤ
ለሰንበት ትምህር ቤተ መዘምራን ለማህበረ ቅዱሳን፣
ለግርማና ለኡካ ነዋሪዎች ይሁን፡፡አሜን!!!
share በማድረግ ሐይማኖቶን ይመስክሩ፡፡
ለማንኛውም መረጃ ወይም አስተያየት በ Viber- what'sup ቁጥር 0911652083 መልእክት ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡ቸር እንሰንብት,,,,

No comments:

Post a Comment