Friday, March 25, 2016

የእመቤታችን መቃብርና ያረገችበት ጣራ - Tomb of The Virgin Mary

ትውልድ ሁሉ ብፅእት የሚላት በተለይ እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ነብሳችን የምንሳሳላት የእናታችንና የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ መካነ መቃብርና የተነሳችበት/ያረገችበት ቅዱስ ጣራ ከታች በፎቶ እንደምታዩት ይህን ይመስላል። የሚገኘውም እየሩሳሌም ውስጥ በቄድሮን ሸለቆ አካባቢ ነው።የእመቤታችን ምልጃና ፀሎት በረከትና ረድኤት ከኛ ከምንወዳት ልጆቿ ጋር ለዘላለም ይኑር! በረከቱ ለእናንተም ይድረስ። 


ድንግል በእውነት ተነስታለች ምስክሩም ይኸው ያረገችበት ቅዱስ ጣራ በቄድሮን ሸለቆ (Kidron Valley) ይህን ይመስላል። ይህንን ቅዱስና ድንቅ ቦታ ለሌሎች ሼር በማድረግ እናንተም የበረከቱ ተካፋዬች ሁኑ! እኛ የድንግል ልጆች ስለምናምነው ቀጥተኛና እውነተኛ የተዋህዶ ሀይማኖት ትክክለኛ መረጃና ከልብ ስለምንወዳት ድንግል ማርያም የማንጠራጠርበት ምክንያት አለን። በዚህ ለማያምኑትና አማላጂነቷን ለሚክዱ እመቤታችን ልቦናቸውን ትመልስልን!!! 



የቅድስት ድንግል ማርያም በዘይቱን መገለጽ - በአማርኛ ትርጉም


Monday, March 21, 2016

መልዐከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ከገጠመኛቸው

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፡፡
.
መልዐከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ከገጠመኛቸው አንዱን ሲናገሩ በሬድዮ አቢሲንያ ቁጥር 22 ካስተማሩት የተሰደ…
.
አንድ ቦታ ላይ አከራዩኝ ብየ ኪራዩ እንደ ጠያቂ ሆኜ ሄድኩኝ፡፡ ከገባሁ በኋላ ዕቃየን አጓጉዤ፡፡ አንድ መኪና ሙሉ አጓጌዤ ማለት በፒክ አፕ ገባሁና ቤት አገኘሁ ብየ ነው፡፡ ለዛዉም እኮ ደግሞ ደግሞ አንድ ክፍል ናት፡፡ በጣም አስቸጋሪ ናት ደግሞ በዛ ላይ ጥበትዋ፡፡ ግን ትበቃኛለች እኔ ምን አለኝ ገብቸ መዉጣት ነው፤ ጸሎት ማድረስ ነው ብየ መሬት አደላድየ አንጥፌ ምን ብየ ጥዋት ለአገልግሎት ልብሴን ለብሼ፤ መጸሐፌን በሻንጠየ ይዤ ስወጣ፡፡ የት ነው የሚሄዱት? አለችኝ ሴትየዋ፡፡ ወደ መሪ አቦ፡፡ እንዴ፤ እንዴ፤ እንዴ መሪ አቦ ሰው የሚያንጫጩት እርስዎ ነዎት? አለችኝ፡፡ አዎ ነው እናትየ፡፡ እኔ ደግሞ በቅን የምታይ መስሎኝ ነው፡፡ እ..ም… አለች፡፡
.
አረረረ..በቃ ሐበሻ እንዲህ ሲል ችግር አለ ማለት ነው፡፡ ሆዴን እየቆረጠኝ ነገሩን እየበላሁ እ..ም… የምትለዋን ቃል ይዤ መጓዝ ጀመርኩ፡፡ እንግዲህ እ..ም… ማከት በሐበሻ ነገር የመብላት ዋዜማ ወይም በልቡ ዉስጥ የቆረጠው ነገር በቅፅበት አለ ማለት ነው፡፡ ይህቺ ነገር ሳስተምር ሁሉ ሆዴን ትበላኛለች፡፡ ስመለስ መጡ እንኳን ደህና መጡ፡፡ ስጠብቆት ነበረ፡፡ ገና ምሳ ሳልበላ፤ አረፍ ሳልል ቤት ይፈልጉ፡፡ ልጄ ከአሜሪካ ትመጣለች ስልክ ተደዉሎልኛልና ሰሞኑን ቤቱን አፀዳድቼ፣ ቀለም ቀብቼ ልጄ ልጠብቃት ስለሆነ ዛሬዉኑ ቤት ይፈልጉና በሦስት ቀን ውስጥ እንዲወጡ እባክዎትን ይተባበሩን አሉና ቁጭ፡፡
.
ጉድ ፈላ፡፡ ይህ ሁሉ ታድያ ይቺ ቀሚሴ አይደለች ጉድ ያፈላች አልኩና ቀሚሴ ላይ አፈጠጥኩ ሳቅ…፡፡ ወይ ቀሚሴ አልኩ በቃ፡፡ ወይ ይቺ የቤተክርስትያን ቀሚስ ይገርማል አልኩና፡፡ ከዛ ደግሞ ስሜ ነው አንዱ ችግሩ ደግሞ የሚያንጫጫው ከተማውን የሚለው ደግሞ የተለመደ ነው እስከ ቅርብ ግዜ ድረስ፡፡ እንደዉም የሚያሳዝነኝ እስካ አሁን ድረስ በጣም አሁንም የምያሳዝነኝ እንዲህ አይነት ጭዋታ፤ እንዲህ አይነት የእርግማን መንፈስን የሚያስፋፉ በቤተ ክርስትያን ያሉ ጉብል ሰባኪዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ጉብልዎቹ፡፡ አዳዲስ ጉብልዎቹ ሰባኪዎች እስካ አሁን ድረስ አሁን አሉ መጸሓፍ መውጣቱን እንኳ አላወቁም፡፡ መጥተው የዳነዉን ህዝብ፤ የዳነዉን ህዝብ አይጠይቁም፡፡ አሁን በያዙት ቦታና በተመደቡበት ቦታ ላይ እስካሁን ድረስ እኔን እያሳደዱ ነው፡፡ ለምሳሌ በሳሊተ ምህረት ሲኤምሲ ይሰብካሉ፤ በጥንት የነበረው በጣም የታወቀው ቦታ ላይ የካ ሚካኤል ይሰብካሉ፡፡ ግርማ የሚባል አስማተኛ ከተማ በጠበጠው እያሉ ሰሙኑን ሁሉ ይሰብካሉ፡፡ የካ ሚካኤል ትልልቅ ሰው ባለበት፤ አባቶች የሚባሉ ባሉበት በዛ ቦታ ላይ ትልልቅ ደህንነት፤ ዓይነ ስዉር በበራበት ቦታ ላይ ሲያሽካኩ መድረኩን ሲጫወቱበት ይዉላሉ፡፡ ህዝቡ አይ የምታውቁት ነገር የለም ዝም በሉ እስኪላቸው ድረስ የሚያሳፍር ነው በጣም፡፡ እና የሚያሳፍሩ ናቸው፡፡
.
እና እነዚህ አዳዲሶቹ ጉብልዎች የፈጠሩት ችግርና በዓውደ ነገስቱ ዓለም ይኖሩ የነበሩት አባቶች የንስሐ ልጆቻቸውን እያወገዙ እርሱ ጋር ከሄዳችሁ የተረገማችሁ ናችሁ፤ እርሱ ጋር ከሄዳችሁ ውጉዝ ከመ አርዮስ እያሉ ህዝበ ክርስትያኑን ብጥብጥ አድርገው ትልልቅ የሆኑ ውርደቶችን እያስተላለፉ ከቤተ እግዚአብሔር ያሉት አባቶች ናቸው፡፡ እነርሱ ባደረጉት ትግባርና በቀሰቀሱት ቅስቀሳ መኖርያ ቤት እምከራየው ቤት እስከማጣ ድረስ፡፡ ከዛ በኋላ በኋላ ሴትየዋ አጣደፈችኝ፡፡ በሦስት ቀን እለቅሎታለው አልኩኝ፡፡ አሁንም ፍለጋ ጀመርኩ፡፡ ስንፈልግ፤ ስንፈልግ እኔን ከሚያውቁኝ ደላላዎች ጋር ስንፈልግ እባካችሁ ጉባኤ ላይ ተናገርኩ እባካችሁ የቤት ደላላዎች የላችሁም ብየ ሰው ፊት ተናገርኩ፡፡ መጡ እኔ አውቃለሁ አለ፡፡ ከዛ በኋላ እስኪ ቤት ፈልግልኝ አልኩ፡፡ አሁንም ስንፈልግ ሄድን አሁንም አንድ ቦታ ተገኘ አለ፡፡ ትልቁ ቤት ላይ ሳሎን አለ፡፡ ከሳሎኑ ኋላ ያለቹው ጓሮ ነው ያከራየው፡፡ አሷም ደግሞ 500 ብር አለችኝ፡፡ እሺ ጥሩ ችግር ለም አልኩ፡፡ ያኔ ምንም የለንም፡፡ በጣም ተወዶብኛል፡፡ ሆኖም ከቤተሰብ ጋራ ማለት ነው፡፡ ደሞዝ የለም ምን የለም፡፡ እሺ በ 500 ብር ተስማማሁ ወዴት ልሂድ ታድያ ለመሪ ቅርብ ነው፡፡ ከዛ በኋላ ሄድንና ሰዉየው ሲያዩኝ ምነው የሚከብዱ ይመስላሉ?፡፡ እንዴት?፡፡ ሳዮት ከበድበድ ያሉ ነዎት ለኛ ቤት አይመጥንም፡፡ እንዴ ለመኖርያ ቤትዎ ለዚህ ለሚያከራዩኝ?፡፡ አይ ማለቴ የኛ ቤት ለርስዎ የሚሆኖት መስሎ አልታየኝም፡፡ ተለቅ ያሉ ሰው ነዎት ማለቴ ነው፡፡ አረ እኔ የምታዩኝ ምን ለራሴ ኩርማም ጭባጥ እማልሞላ፡፡ አይይ ግድ የሎትም የኛ ቤት አይመጥንዎትም ለፊቴ ደግሞ እርስዎ ከብደዉኛል አለና ቁጭ፡፡ ከሸፈ ይሄም ከሸፈ፡፡
.
በኋላ አንዱ ጉባኤ ላይ አረ እባካችሁ በመኖርያ ምክንያት ለቅቄ ልሄድ ነው እንዴ አዲስ አበባ ትቻቹ ልሄድ ነው ስል፡፡ አይ የኔ እናት ታማለች በዛው እገዛ እያደረግክልን ትቀመጣለህ አለኝ እና አንድ ወንድም፡፡ እዛ ቤት ገባሁ፡፡ ከዉስጧ የተከፈለች ነች፡፡ በከፊል ደግሞ ለሌላ የጸሎት መገልገያ የምትሆን ቦታ አደረግኩና ቁጭ አልኩ፡፡
.
በነሱ ላይ የመተተችባቸው ሴት ደግሞ በጓሮ በኩል አለች፡፡ በዛ ስወጣ ስገባ መተተኛ መጥፎ ደሮ ትላለች ደሮዋን እያየች እኮ ነው፡፡ ኮቴሸን መስበር ነበረ እያለች የገዛ ደሮዋን በኔ እያሳበበች አኔን ትራገማለች፡፡ ልክ መውጭያ ሳዓቴን ታውቃለች የታባትዋ ይህችን ደሮ እዚህ ከገባች ጀምሮ እንዲሁ አታክልቱ መሬቱን ቦታው ሁሉ ተግማማኮ ትላለች፡፡ እኔ ጸሎት ሳደርስ እንግዲህ ዕጣኑ እየሸተታት ነው መሰለኝ፡፡
.
እንደገና በሌላው ቀን ደግሞ ቆይ አንቺን ከዚህ ሳላጠፋ ይህቺን ደሮ የሚያርድልኝ እንደዉም ምንም ሰውና ቢላዋ ላጣ ነው ትላለች፡፡ የፈረደባት ደሮ ግን ደሮዋ የለችም፡፡ እኔ ነው ደሮው ሳቅ ሳቅ…፡፡ የሚገርም ነው እንዲህ ያለች እያለች ደግሞ ከቤት ውስጥ ደግሞ አንድ መንፈስ ያለባት ልጅ አለች፡፡ ለሷ መንፈስ ነፃ እንድወጣ ስታገል ደግሞ የሷ መንፈስ እሷን ገለበጠና ደግሞ እሷ ከጎኔ ነበረች፡፡ ግድግዳዉን ትደበድባለች፡፡ የታባቱ ይሄ ሰዉየ ከዚህ ካተነቀለ የአባቴን ቤት ይዞ፤ የአባቴን ቦታ፤ ይዞ እናቴን እያስቸገረ እያለ ደግሞ እሱ ደግሞ ሌሊት ከእንቅልፍ ይከለክለኛል፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ አይጦቹ ይንጋጋሉ፡፡ በመጨረሻ አንድ አይጥ ጣቴን ስጋ ያገኘ መስሎት ቦድሶ ለቀቀው፡፡ አባቶች አይጥ ሲነክስህ ያሰብከው ይሳካል ይላሉ፡፡ ዎው አልኩና ቢቸግረኝ በጣም ተስፋ አደረግኩኝ ሳቅ ሳቅ…፡፡ ምክንያቱማ አይጥ ሲበዛ በረከት ይመጣል ይባላልና የቀደሙ አባቶች የሚናገሩት ነው፡፡ አይጥ ምቀኛ ነው፡፡ ምቀኛ ሲበዛ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ሆኖ በረከት ይሰጣል እንደ ማለት ነው ትርጉሙ፡፡ ጎሽ እንግዲህ አባቶች የተናገሩት የአይጥዋ ድርሻ በእጄ ላይ ስላረፈ እግዚአብሔር አንድ ነገር ያደርጋል ብየ ጠበቅኩኝ፡፡ እዛው ቤት እንዲሁ መንከራተት፤ መንከራተት በአንድ በኩል ሌባውም ደጅ ሲጠና፡፡ አንዳንድ ዕቃዎችን ደግሞ ከዛ አሽሼ ዘግቼ ወደ ዝዋይ ወደ ቤተሰብ ሄጀ ስመለስ፤ መጣ እንዲህ ይቺ መጥፎ ደሮ ስባል ምን በቃ እንግዳው ሲመጣ ደሮ እንግዲህ ይግበሰበሱ ጀመር እነዚህ ግብስብሶች መምጫቸው መሄዳቸው የማይታወቅ ድራሻቸው ይጥፋ ስንባል፡፡ ልክ እንግዳው ሲመጣ ያቺ መታችዋ በጎረቤት በኩል ትጮሃለች ኡ ኡ ነው የምትለው፡፡ እንግዳው ሲመጣ ትራገማለች፤ ትታገላለች፡፡ ይሄ መተተኛ ደብተራ ትላለች፡፡ ከዛ እንግዶች ሁሉ፡፡
.
በጣም የሚያሳዝነኝ ደግሞ ሞራሌን የነካው፡፡ አንድ ሴት አሜሪካ ቪሲዲዉን ተለቆ ነበር ያን ግዜ ደግሞ፡፡ አይታ ልጅዋን ልታድን ወደኔ ትመጣለች፡፡ ደህና ሰው ተብሎ እንግዲህ የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦለት ተብሎ በሷ አስተሳሰብ እንግዲህ በጣም የተሻለ ቤት፣ የተሻለ ኑሮ ብላ ነው የምትጠብቀው፡፡ ከዛ መጣች ሳጥን ሰጠኋት መቀመጫ፡፡ ወንበር የለኝም፡፡ እኔ እዚህ የምጸልይበት ቦታ መሬት አለች እዛች ላይ ቁጭ አልኩኝ፡፡ ልጇን ይዛ መጣች፡፡ ቤቱን ታያለች፡፡ እንዲህ እንዲህ ብላ ወደ ላይ ጣራዉን ታያለች፤ ግድግዳው ታያለች፡፡ ግድግዳው ጭቃ ነው በአንድ በኩል ከኋላ በኩል ደግሞ ጭቃው ተገርስሶ አፉ ከፍተዋል፡፡ አንዳንዴ ዝናብ ሲመጣ በዛ በኩል ይመጣል፡፡ ከነካሁት ሊፈርስ ነው፡፡ ይወድቅና እንደገና ደግሞ ኦና ሊሆን ነው፡፡ እና ዝም ብየዋለው ምን ላድርግ ሲወድቅ ድረስ፡፡ ከዛ ግድግዳዉን ከአሁን ከአሁን አትውደቅ እያልኩ እቀመጣለውና መጥታ ሳጥን ላይ ቁጭ አለች፡፡
.
ቤቱን ታያለች፤ ታያለች፤ ታያለች ይሄው የመጣሽበት ጉዳይ እንግዲህ ልጅሽ ነው ጸሎት እናድርስ ስል፡፡ እየፈፋት ነው ቤቱ እሷ ከአሜሪካ ነው የመጣችው፡፡ በማቴርያልም ጭምር ያመልካሉ፡፡ እንግዲህ ይሄ በዓለም የታወቀ ሰዉየ ይዚህ ቆሻሻ መንደር ውስጥ ምን ያደርጋል ብላ ነው እሷ፡፡ ስለዚህ የመጣሁት ወደ ጠንቋይ ሰው ነው ብላ ነው የገመተቹው በቃ፡፡ ያው ቤቱ ደግሞ የጸሎት ዕጣን ስለሚደረስበት እሷ የምታውቀው አይነት ባይሆንም ዕጣን ዕጣን ይሸታል፡፡ አሃ ብላ በስጋት ዓይን ታየኛለች፡፡ ከዛ ልጅቱ ላይ ያለው መንፈስ ተያዘ፡፡ ቡዳ፣ መተትና ዓይነ ጥላ ነበረ፡፡ ይሄ መያዙ አላስገረማትም፡፡ ያስገረማት የምኖርበት ቤት የቀፈፈው መሆኑ ነው፡፡ እና አላስደሰታትም፡፡ ከዛ ይሄው ይሄው ተያዘልሽ አልኩኝ፡፡ ቅር እያላት ሳይ በኋላ እየጸለይኩ ከመንፈሱ ጋር እየታገልኩ በስዕሉ መስታዎት ሳያት ላይ ጣራ ጣራዉን ታያለች፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ አይጥ በላይ በጣራው በኩል ስትመጣ በርግጋለች፡፡ ዘንዶ የተቀመጠ መስሏታል፡፡ ይሄው በቃ ተይዘዋል ስላት፡፡ ተያዘ እንዴ? ይሄ ነበረ ችግርዋ አለችና እግዚአብሔር ይስጥለኝም አላለችም ቀስ ባላ ሹልክ ብላ ስትሄድ እንዴ ገረመኝ፡፡ ምን መሆኗ ነው የሷ ደንብሮ ነው እንዴ ብየ በኋላ ሳስተዉለው ቤቱ ቀፏት ነው፡፡ የምኖርበት ቤት ቀፏት ነው፡፡ በስልክም ያለችው ነገር የለም፡፡ እኔ ታግየ ብቻ ከልጂቱ ጭንቀትና ችግር ጋር ተካፍየ ነው ሂጂ በቃ እና ነገ ትመለሻለሽ፡፡ እንግዲህ ተመልከት ስትቀር ስጠብቃት ስልክ ስደዉል ዝግት ታደርገዋለች፡፡ ለልጂትዋ አስቤ እናትየዋ እንግዲህ ለልጂትዋ ማሰብ አቅትዋት ነው፡፡ ያንን የመሰለ ዉርደት፣ ያን የመሰለ ክፉ መንፈስ ለዘመናት ያደቀቃት ልጂቱን የጎዳት እንዳታገባ ዓይነጥላው አለ፤ እንዳትወልድ ዓይነጥላው አለ፤ ሥራው እንዳትሰራ መተቱ አለ፡፡ እቤት ጉልት ልጅ ይዛ መንፈሱ ተጋልጦ በዛች ኮሳሳ ቤት ምክንያት ቀረች፡፡
.
ከዛ በኋላ እሷ ላመጣች እናት ስደዉልላት ምን አይነት ፍንጭ ሰጠችኝ፡፡ የሚኖሩበት ቤት ዓይን የማይገባ ነው፡፡ እንደተባለው ሰዉየው አስማተኛ ሳይሆኑ አይቀሩም አለችና ቁጭ፡፡ ብላለች የሚለው መልዕክትን እንደገና፡፡ በቃ በቃ አልኩ ይህን ለተናገረችው ሴት ስልኩም አጠፋሁ የሷንም ይዚህችኛዉም አጠፋሁና፡፡ ወይ ጉድ ብየ ጸሎቴን ጸልየ፤ ለእግዚአብሔር ተናግሬ የዛን ቀን ያለምኩት ህልም ምን ግዜም የማይረሳኝ ነው፡፡ በደንብ ለአምላኬ ተናገርኩና መቼ ነው ከኢኮኖሚ ነጻ የምታወጣኝ፡፡ ከኢኮኖሚ ባርነት ከዚህ ከቤት ክፉ አገዛዝ፤ ከመኖርያ ቤት፤ ከእርግማን መቼ ነው የምታወጣኝ፡፡ ጠንቋዩና ቃልቻው እዚህ ባለ ሦስትና ባለ አራት ፎቅ ሆኖ የአዲስ አበባ፡፡ የአዲስ አበባ ህዝብ ለጠንቋይና ለቃልቻ ቤት የሚሰራ፡፡ ለመተተኛና ለሟርተኛ ህንፃ የሚገነባ ህዝብ ለኔ አንድ ንፁህ የምከራይበት ቤት አጣሁ ብየ ለእግዚአብሔር ተናገርኩኝና፡፡ ከሌሊቱ አስር ሰዓት ተኩል ለጸሎት ልነቃ ስል የተለየ የጸሎት ቤት ቦታ ያለው፡፡ እጅግ ሰፋ ያለ ብዙ ክፍሎች ያለት እና እጅግ በጣም ብዙ የበረከት ምንጭ ያለው ቤት የሚመስል ራዕይ አየሁና ብንን አልኩ፡፡ በጣም ደስ አለኝ፡፡ በቃ ራዕየይ አመንኩት፡፡ እግዚአብሔር ተናገረ፡፡ ትላንት ባለቀስኩት ዛሬ መልስ ሰጠኝ ብየ እንደገና ጸሎቴን አድርሼ ወደ ቦሌ መድኃኔ ዓለም ሄጄ ተሳልሜ ዙርያዉን ዞሬ ክብርህ፣ ደስታህ፣ ኃይልህ ከኔ ጋር ይን ብየ ደስ ብሎኝ ስጠብቅ፡፡
.
ያው ከአሜሪካ አንድ ታላቅ በሃገሩ መንግስት የታወቀ ፕሮፌሰርና ሳይንቲስት ወደ ኢትዮጵያ መጣ፡፡ በስድስት ወር ውስጥ እኮ ነው፡፡ ከዛች ቤት በነገራችን ላይ ከአንድ ከተወሰነ ወራት በኋላ ወጣሁኝ፡፡ ለሦስት ዓመት አራት ወር የቀረው ኖሬበታለሁኝ ማለት ነው እዛች ቦታ ደሳሳ ጭቃው ሁሉ እየገባ፤ ዉሃ እየተከላከልን ዙርያዉን እየገደልን ዉሃው ሲመጣ አንዳንዴ ውሃ እንዳይስደን እየተጠነቀቅን ቦይ እያወጣንለት እዛ ቆየን፡፡ ይህንን በማድረጋቸው እግዚአብሔር ይስጣቸው፡፡ እነርሱም ታላቅ ውለታ ነው እንጂ አዲስ አበባ ለቅቄ ለመውጣት ሞክሬ ነበረ፡፡ በዚች ሃገር ውስጥ የተለየ አስማተኛ እንደሆንኩ ተደርጎ የሚነገረው የንስሐ አባቶች ድምፅ በከፍተኛ ትንቅንቅ ነበር፡፡ ዲያብሎስ የተዋጋኝ በነሱ በኩል ነበር፡፡
.
ያው ዛሬ በአያት ምድር ላይ አሉ ከሚባሉ አንዱ ቤት ውስጥ እገኛለው፡፡ ያ ሳይንቲስትና ባለቤቱ ቤቱን ገዝተዉልኝ ደስ ብሎኝ እግዚአብሔር ይመስገን ከመንከራተት ድኜ እግዚአብሔር ስሙ የተመስገን ይሁን፡፡ ጸሎቴን በአንድ ቀን ውስጥ ምላሽ ሰጠ እግዚአብሔር፡፡ እዚህ ያለው ህዝብ እንዲህ ሲያደርገኝ ለኔ የሚግዘኝን ከዉጪ አመጣኝ፡፡ ዛሬም የሚለወጡት እዚህ ያሉት በብዛት አይደሉም፡፡ ከዉጪ ያሉት ናቸው የሚለወጡት፡፡ እግዚአብሔር መባረክ ጀመረው የውስጡ ሳይሆን የዉጩዉን ነውና እግዚአብሔር አምላክ ለዘልዓለም ስሙ የተመስገን ይሁን፡፡ ይህንን የሚመስል ብዙ የተንከራተተ ህይወት አሳልፍያለው፡፡ ዘፋኝ ብሆን እኮ እሸለም ነበረ፡፡ ሬድዮ ጣብያዉም፤ ቴሌቪዥኑም፤ ካድሬዉም ትልልቁም ትንንሹም ያጨበጭብልኝ ነበር፡፡ ግን እግዚአብሔር በተረገመበት፤ እግዚአብሔር የለም በተባለበት ሃገር ውስጥ እግዚአብሔር አለ የሚል ከሆነ፤ እግዚአብሔር ቅዱስ ነው የሚል ከሆነ አንተ እርኩስ ነህ የሚለው ነው የሚበዛውና እውነታው ይሄ ነው፡፡ ይሄን የሚመስል ሁኔታ ውስጥ ነው ያሳለፍነው፡፡ አልጋ በአልጋ የሆነ መንፈሳዊ ህይወት የለም፡፡ አልጋ በአልጋ የሚሆነው ለአርቲስቶች ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔር ማስተዋሉን ይስጠን፡፡