Friday, April 15, 2016

ወንጌላዊው ሉቃስ የሣላት ሥዕለ ማርያም ተአምራት

ጼዴንያ በምትባል ሀገር ውስጥ የነበረች ማርታ የምትባል የከበረችና የተመረጠች አንዲት ሴት ነበረች። ከዕለታት አንደ ቀንም የሷ ገንዘብ እንደ ሰው ገንዘብ ሁሉ እንደሚጠፋና ከንቱ እንደሆነ በማሰብ ሰፊ የእንግዳ ማረፊያ በማዘጋጀት እንግዶች መቀበል ጀመረች። አብልታ አጠጥታ ከጨረሰች በኋላ ስለመለኮትና ስለቀደሙት አባቶች ትጠይቅ ነበረ። ከእለታት አንድ ቀንም  አብልታ አጠጥታ ከጨረሰች በኋላ ለእርሷ የሚጠቅማትን ነገር እንግዶችን ስትጠይቅ በኢየሩሳሌም ሀገር ውስጥ የእመቤታችንን ሥዕል የሚሥሉ እንዳሉ ያቺም ሥዕል የለመኑትን ሁሉ እንደምታደርግላቸው ነገሯት።
ይህንንም ነገር ሰምታ በድንግል ማርያም ፍቅር ልቧ ተነካ። ሰለሥዕሉ የነገሯትንም ሰዎች ‹‹ገንዘብንና ወርቅን ሰጥቼው ከሚሥሉት ሰዎች የድንግል ማርያም ሥዕልን ይገዛልኝ ዘንድ ከእናንት ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድ አለን?››  ብላ ጠየቀቻቸው። አንድ መነኩሴም ያቺ ሴት ድንግል ማርያምን የመውደዷን ነገር ሰምቶ ‹‹አኔ እሄደለው በራሴው ወርቅም ገዝቼልሽ እመጣለው በተመለስኩ ጊዜም የገዛሁበትን ወርቅ ያህል ካንቺ እቀበላለው›› አላት።
ማልዶም ተነሥቶ ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ በደረሰ ጊዜም ያቺን ሴት ይገዛላት ዘንድ ያማጸነችውን በዚያ አሰበ። አስቦም አልቀረም መልኳ ያማረ ሥዕል ገዛ።
ቅድስት ድንግል ማርያም ከተወደደው ልጇ ጋር (አቡነ የምዓታ ገዳም የሚገኝ ሥዕል ?15 ኛው መ.ክ.ዘ.)
ይህችውም ሥዕል ወንጌላዊው ሉቃስ የሣላት ናት ትባላለች። ያም መነኩሴ ሥዕሏን በደረቱ ታቅፎ ወደ ጸዴኔያ በሚወስደው መንገድ ሔደ።  እየሄደ ሳለም አንበሳ ይገድለው ዘንድ እየጮኸ በጠላትነት ተነሣበት። ያ መነኩሴ አንበሳውን ከመፍራቱ የተነሳ ደነገጠ ተንቀጠቀጠ። ደንግጦ ቁሞ ሳለም ያቺ ሥዕል ከአንበሳው ጩኸት ሰባት እጅ በሚበልጥ በፍጹም መፍራት ጮሀ ተናገረች። ያን ጊዜም ፈረሰኛ ተከትሎ ለሞት እንዳደረሰው ያ አንበሳ ደንግጦ ፈጥኖ ሸሸ። ያም መነኩሴ የሥዕሊቱን ድምጽ ከመስማቱ የተነሣ እያደነቀ ሄደ።
ሁለተኛም መቀማት መግደል ልማዳቸው የሚሆን ወንበዴዎች በከበቡት ጊዜ አስቀድመን እንደተናገርን ያች ሥዕል እንደመብረቅ ባለ በታላቅ ቃል አሰምታ ተናገረች። ከመፍራትም ብዛት የተነሳ እነዚያ ወንበዴዎች ያ ጩኸት  ከየት እንደመጣ (እንደተደረገ) ሳያውቁ ሸሹ። ያም መነኩሴ እነዚህን የሚያስደንቁ ተአምራት በሰማና ባየ ጊዜ አሰበ። ረዳት ትሆነኝ ዘንድ ወደ አገሬ ኢትዮጵያ ይዣት እሄዳለውም አለ።
እሱ ግን ይህችን ሥዕል በፍጹም  ልቦናዋ ከምትወዳት ሴት ጋር ትኖር ዘንድ በራሷ ፈቃድ እንደመጣች አላወቀም። ነገር ግን ለነጋዶች እንደሚሸጧቸው እንደሌሎች ገንዘቦች ያለ ፈቃዷ በገንዘቡ ዋጅቶ ያመጣት መስሎት ነበር። ስለዚህች ነገር ለዚህች ሴት እንዳልሰጣት ባገሬ መንገድ እሄዳለው እንጂ በቤቷ መንገድ አልሄድም አለ። እንዲህም ሲያስብ በልቦናውም ሲመክር ከባህር ዳርቻ ደረሰ። ብዙ መርከቦች ነበሩ ወደ ወደብ በማናቸው መንገድ ትወጣለችሁ አላቸው። አንዱ ወደ ጸዴንያ አለው፣ተወው። አንዱ ግን በሌላ ቦታ ወደ ኢትዮጵያ አገር እወጣለው አለው።
በዚያች መርከብም ሄደ ነገር ግን ግማሽ( ከባህር መካከል) ሲደርስ ጥቅል ነፋስ ተነስቶ ያለፈቃዱ ጼዴንያ ወደሚያወጣ ወደብ ወሰደው። በዚያች መንገድ ወጥቶ በልቡ “ሥዕል እገዛላት ዘንድ ያመጸነች እኔ እንደሆንሁ በወዴት ታውቀኛለች ብሎ ወደ ማርታ ቤት ሄደ ወደ ቤቷ ገብቶም ከመንገደኞች ጋር አደረ።
ሲነጋ ከሳቸው ጋር ወደ ውጭ ወጥቶ መንገዱን ይሔድ ዘንድ ወዶ  ከእንግዶች ጋር ወደ ቅጽር በር ደረሰ እነሱም ወጡ። ይህ መነኩሴ ግን ወጥቶ መሄድ ተሳነው በእመቤታችን በድንግል ተአምር መዝጊያው በፊቱ ተዘግቶበታል። የቅጽሩ በር ግን ከፊቱ ለሌሎቹ አለተለወጠም ለሚገቡ ለሚወጡም የተከፈተ ነበር። የማርታም ልማድ ስንቅ ለሌላቸው ለመንገድ የሚያሻቸውን እየሰጠች ወደ ቅጽሩ በር እንግዶችን ዘወትር መሸኘት ነበር።
ያንም መነኩሴ በዚያ ለመውጣት ሲተጋ ሳይቻለው ባየች ጊዜ አባቴ ሆይ በታመመ ሰው አምሳል አይሃለሁ እደር ነገ ትሄዳለህ ቤቴም ለእንግዶች ማደሪያ የተሠራ ነውና አለችው እሱም እሺ አላት። በነጋውም ሁለተኛ ይሔድ ዘንድ በወደደ ጊዜ እንደ ትናንት መሔድ ተሳነው። እሷም ሁለተኛ ጊዜ አሳደረችው። ዳግመኛም በሶስተኛው ቀን ይወጣ ዘንድ ሲሞክር ልማድ አልተወውም መውጣትንም አልቻለም።
ማርታም ሦስት ቀን እንደዚህ ሆኖ እንደ በሽተኛ ሳይተኛ እንደ ደህና ሳይሄድ ባየችው ጊዜ ‹‹አባቴ ሆይ ይህ ባንተ ላይ ያለነገር ምንድን ነው ተናገር›› አለችው። ያም መነኩሴም በማፈር መናገር ጀመረ። ‹‹ወደ ኢየሩሳሌም በሔድሁ ጊዜ የእመቤታችን ድንግል ማርያም ሥዕል አመጣልሽ ዘንድ ያማጸንሽኝ እኔ እንደሆንሁ አላወቅሽምን?›› አላት። ከቤቴ የሚገቡና የሚወጡ ብዙዎች ናቸውና በምን አውቅሃለሁ አለቸው። ከዚህም በኋላ የተደረገውን ተአምራት ሁሉ ነገራት።
ይህንንም ተናገሮ ያችን ሥዕል ከክንዱ አውጥቶ ሁለንተናዋ ድንቅ የሚሆን ያችን ሥዕል እነሆ ለማርታ ሰጣት። ማርታም ይህን ነገር ሰምታ ድንግልን ስለወደደች ከእግሩ በታች ሰገደች። ሥዕሉን ከእጁ ተቀብላ በታላቅ ምስጋና አመሰገነች ሰገደችም። ሰለሞን ለታቦተ ጽዮን ማደሪያ ቤተመቅደስን እንዲሠራ ያመረ ቤትን አሠራችላት። እሷንም የሚቻላትን ያህል አክብራ አኖረቻት። ከሥዕሏም እንባና ወዝ ይወጣ ነበር። ከወዟም የተቀቡት ከሚያስጨንቅ ደዌያቸው ይፈወሱ ነበር። በዓሏም መስከረም 10 ቀን ነው። ማርታም በፊቷ እጅ ትነሣና ትሰግድ እንደነበረ በተአምረ ማርያም ላይ 8 ተአምር ላይ ተገልጿል።

ንብ በሚያረባ ሰው ላይ የተደረገ ተአምር

Friday, April 1, 2016

ምድር ውስጥ ያለችው የታች ጋይንቷ ሰጎዳ ማርያም

አርብ ገበያ ነን፡፡ አርብ ገበያ የታች ጋይንት ወረዳ ዋና ከተማ ናት፤ አዲስ አበባ ከአርብ ገበያ 775 ኪሎ ሜትር ትርቃለች፡፡ የታች ጋይንት ብዙው የአየር ንብረት ወይና ደጋማ ነው፡፡ እንደ ቤተ ልሔም ያሉ ጥንታዊ መንፈሳዊ ስፍራዎች የሚገኙባት ወረዳ ከልዳ ጊዮርጊስ እስከ ደቃ ቂርቆስ አስደናቂ የሆኑ መንፈሳዊ መዳረሻዎች ቢኖሩባትም ብዙም አትታወቅም፡፡ ከራሷ ተሻግሮ የሀገር ልጅ ሊኮራበት የሚገባውን ቀደምት ቅርስ ፍለጋ መጥተናል፡፡ 
ሰጎዳ ማርያም ከአርብ ገበያ 11 ኪሎ ሜትሮች ያክል ትርቃለች፡፡ የደብሯ የጽሑፍ ሰነዶችና የሀገሬው ቃል ጥንታዊነቷን ይገልጻል፡፡ የተተከለችው በአብርሐ አጽበሐ ሲሆን የሰነዶቹ ምስክርነት በ330 ዓ.ም. እንደተሰራች ያትታል፡፡ አቡነ ሙሴ የተባሉ ከግብጽ የመጡ ቅዱስ አባት የተከሏት እንደሆነች ታሪኳ የሚያስረዳው ሰጎዳ ማርያም አስገራሚ በሚባል አሰራር የታነጸችና ከመሬት ተገናኝታ በልዩ ሁኔታ የተፈጠረች ደብር ናት፡፡
ዘመኗን ወደ ኋላ ቆጥሮ ከ 1600 ዓመታት በፊት ይህንን ትሰራ የነበረች ሀገር ለሰራቸው የምትሰጠው ቦታ ምን እንደሆነ ከሚያሳብቁ የሀገራችን መስህቦች አንዷ ናት፡፡ የተነጠፈ ዐለት ድንቅ ቤተ ክርስቲያን የሆነባት ሰጎዳ ማርያም ውስጧ በማህሌትና በመቅደስ የተከፋፈለ ነው፡፡


ምድር ውስጥ ብትሆንም ቀደምት ጥበበኞች የኪነ ህንጻ ጥበበኛነታቸውን ዘመን አሻግረው ማሳየት የቻሉበት አሰራርን ተላብሷል፡፡ ከአናትና በጎን በኩልና በላይኛው ክፍል ለብርሃን ማስገቢያ የተተው መስኮቶች አሉ፡፡ የእነኚህ መስኮቶች አቀማመጥና አቅጣጫ ትክክል መሆኑን በውስጠኛው ክፍል ያለውን በቂ ብርሃን በመመልከት ይደመሙበታል፡፡
የውስጥ ስዕሎቿ ከዐለቱ ህንጻ እኩል ዘመን ባይኖራቸውም እድሜ ያስቆጠሩ ናቸው፡፡ በርካታ ጥንታዊ ቅርሶች የሚገኙባት ሰጎዳ ማርያም የሚበልጠው መገለጫዋ ምንፍስና በመሆኑ ከነገስታት ስጦታዎች ይልቅ የቀደሙት የበቁ አባቶቿ መገልገያ ቁሳቁሶች በክብር ተይዘው የሚጠበቁባት ታሪካዊና መንፈሳዊ ስፍራ ናት፡፡



የኪዳነ ምሕረት ተዓምር 

በደሴ ቁስቋም ማርያም የተደረገ እጅግ ድንቅ ተአምር