Sunday, August 27, 2017

122 አመት የሆነው ታቦተ አቡነ አረጋዊ በተኣምር ተገኘ

ሰላም እንደምን አላችሁ፡ 21/12/2009ዓ.ም በ ሎዛ ማርያም ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን(ብርጭቆ ማርያም) ለአገልግሎት ነው የሄድኩት ቅዳሴ ካለቀ በኀላ ተአምረ ማርያም ተነቦ በአውደ ምህረት አንድ አባት ፦ ነሀሴ 7ቀን በቤተልሔሙ ጋር ብርሀን አይቻለው አንድ ነገር ይኖራል ስለዚህ ቆፍረን ማየት አለብን ብለው ለ አለቃው ይነግሯቸዋል እሳቸውም እሺ በማለት ከ አባቶች, ዲያቆናትና ምእመን ባለበት ሲቆፈር የ ብረት ሳጥን በ ፎቶ እንደምታዩት ብዙ መስቀል ፡ ጽና፡ ማዕጠንት፡ እናም ታቦተ አቡነ አረጋዊ እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ሆኖ በ አልባስ ሆኖ ተገኘ፡፡ ሳጥኑ ላይ በ1878 ዓ.ም ተብሎ ተጽፎበታል ማለትም ወደ 122 አመት የሆነው ነው፡ እግዚአብሄር ይመስገን በ ህይወቴ ለመጀመሪያ ግዜ እንዲህ ሲገጥመኝ፡፡ ተመስገን ተመስገን ተመስገን
በረከታቸው ይደርብን አሜን፡፡












No comments:

Post a Comment