Showing posts with label ሸጎሌ [ሚዳቋ] ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን. Show all posts
Showing posts with label ሸጎሌ [ሚዳቋ] ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን. Show all posts

Monday, May 25, 2015

ሸጎሌ [ሚዳቋ] ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አህዱ አምላክ አሜን!
(ሸጎሌ [ሚዳቋ] ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን፤ አድራሻ አዲስ አበባ፤ ከአዲሱ ገበያ -» ጽዮን ሆቴል -»ሽጎሌ ኪዳነምሕረት/ድልበር -»15 ደቂቃ )
" የፃድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል"
መዝ 111:6
የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም ያስራት ያደራ ልጆች የፃድቃን ሰማእታት ባለሟሎች በወደደን እንስከሞት ድረስ ባፈቀረን በ አንድያ ልጁ በእየሱስ ክርስቶስ ፍፁም ፍቅር በሆነ ሰላምታ እንደምን ቆያችሁ
ምስጋና የባህሪውን የሆነ ያባቶቻችን አምላክ ዛሬ በእኛ አንደበት ነገም በፍጥረታት ሁሉ የተመሰገነ የከበረ ይሁን። የ ሀዲስ ኪዳን ኪሩብ እናትና ድንግልናን አስተባብራ የያዘች ቤዛይት አለም የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም ልመናና ፅሎቷ አይለያችሁ አሜን አሜን አሜን።

እኔ በስፍራው በነበርኩበት 2006 አመት ምህረት ላይ ድንቅ ተአምር በእኔና በሎሎች ምእመናን ላይ ሲደረግ አይቻለው የተደረገላቸው ምስክርነት ሲሰጡ ሰምቻለው አጋንንት ሲቃጠሉ ከተለያየ ሀገር የመጡ ሰዋች ከሆዳቸው የተለያየ ነገር ሲወጣ የእግዚአብሔርን ድንቅ ተአምር ሲገለጥ ማየት የተለመደበት ሰፍራ ነው የ ሰማእቷን ተአምረኛ እምነት ተቀብተው ከነበረባቸው ደዌ ሲፈቱ እንዲሁም በህይወታቸው የተለያየ ጥያቄ እና አስቸጋሪ ፈተና የገጠማቸው ደጇ መተው አርምሞ /ብቻቸውን እየፆሙ እየሰገዱ እየፅለዩ እና በቀን 1 ጊዜ ብቻ እየበሉ/ መልሳቸው ተመልሶላቸው ጭንቀታቸውን በደስታ ተቀይሮላቸው ሲሄዱ ተመልክቻለው ።

እናም የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እግዚአብሔር ለምህረት በተለያየ መንገድ ይጠራናል እናም ሄደን ንስሀ ገብተን ፅበሏን ጠጥተን እምነቷን ተቀብተን ከነበረብን ደዌ ተፈተን የአለም ጭንቀታችንን እረስተን የሰማእቷን በረከት እንድትካፈሉ በልኡል እግዚአብሔር ስም እጠይቃለው። በሰው አገር ያላችሁ እንደኔ ቤተሰቦቻችሁን ልካችሁ እምነት ፅበል አስመጥታችሁ ተጠቀሙ
የሰማእቷ በረከት አሁንም እኔ ባለውበት እምነቷ ለብዙ ጓደኞቼ ፍትሁን መድሀኒት እየሆነ ተአምር እየሰራነው። እንዲሁም ቦታው ከተመሰረተ ብዙ የቆየ ባይሆንም የልማት ስራው ግን እንደምታዩት በ መሳርያና በ ገንዘብ እጦት ቆሟል እናም ይህን የበረከት ስፍራ መንከባከብና እና ማገዝ ስላለብን ሁላችንም እንድንሳተፍ በልኡል እግዚአብሔር ስም እጠይቃለው።

ዛሬ እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ አንድ ድንቅ ተአምረኛ የፅበል ስፍራ ብዙ ያልተጠቀምንበት የሰማእቷ የቅድስት አርሴማ....የ ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ...የመጥምቁ ዬሐንስ.....እንዲሁም የእመቤታችን የቅድስት ኪዳነምህረት....ፅበሎች በአንድነት የሚገኙበት ለአጋንንት ምድራዊ ሲኦል የሆነ ድንቅና ተአምረኛ ሰፍራ ነው።

በፅበሉ ሰፍራ የምትገኝ ሚዳቆ ከፅበሉ ቦታ የማትጠፋው                           የፀበሉ መሄጃ መንገድ እጅግ ተአምረኛ ስፍራ















አድራሻ
አዲስ አበባ የ ጉጃም በር በመባል የሚታወቀው ሱሉልታ መንገድ
 
ላይ አዲሱ ገበያ{ፁዬን ሆቴል } ከዛ በታክሲ በመያዝ አዲስ የተሰራ ያለው መለስ ፓርክ በሩላይ ወይም ባለታክሲውን አርሴማ ፅበል በሩላይ አውርደኝ ብትሉት በሩ ላይ ይጥላችሀል።

ለበለጠ መረጃ በቦታ የሚገኙት የሚያገለግሉ ካህን አባ ኪደነ ማርያም +251920225390 በቫይበር ማግኝት ትችላላችሁ

"እግዚአብሔር ፃድቃንን ይወዳል እግዚአብሔር ስደተኞችን ይጠብቃል"  መዝ.145፤6