Tuesday, August 19, 2014

ከእጇ ዘይት የሚፈልቅ የቅድስት ኤልሳቤጥ አስገራሚ ታሪክ

ወንድሞቼ እና እህቶቼ ይህንን ድንቅ ተአምር ስናገር እግዚአብሔር ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ እመቤታችንም ምን ያህል ክብርት እንደሆነች እያደነቅሁ ነዉ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነዉ ይህች የምትመለከቷት ቅድስት የድሮ ስሟ ሳሚያ ዮሴፍ ባሲሊዮስ ትባላለች፡፡ የቅርብ ጊዜ ቅድስት ናት ያረፈችውም 6 ወር በፊት ነዉ፡፡ ከእጇ ዘይት የሚፈልቅበት ምክንያቱ እንዲህ ነዉ፡፡ይህች ሴት በኃጥያት ትኖር ነበር(በሕይወቷ ቤተ ክርስትያን የሔደችዉ ልጇን ክርስትና ልታስነሳ ነበር) ሴት ልጇ ደግሞ ወደ ቤተክርስትያን ትሄዳለች ልጅቷ ስለእናቷ ወደ ቤተክርስትያን እንድትሔድላት ትጸልይ ነበር እናትየዋ በቀን 60 ሲጋራ ከማጨሷም በላይ ልጅቷን ልትመታት ትደርስ ነበር በቤቱ የአቡነ ሺኖዳ ስብከት ከተከፈተ ንዴቱ ይብስባት ነበር ዘፈን ከሆነ ግን ደስታውን አትችለውም፡፡ልጅቷ ግን መፀለይዋን አላቋረጠችም እንደውም ንስሐ አባቷን እያመጣች ልታስመክራት ስትሞክር ፈቃደኛ አልነበርችም፡፡ነገር ግን ንስሐ ተስፋ አልቆረጡም እንደውም በቅዳሴ ጊዜ ስሟን ጠርተዉ ስለፀለዩላት በሌላ ቀን ሲመጡ ተቀበለቻቸዉ ከመግባታቸዉ በፊት በሩ ላይ የመስቀል ምልክት አድርገዉ ነበር፡፡ከዚያ ለምን ወደ ቤተከርስትያን አትመጪም ሲሏት ቤተክርስትያን ያሉት ሰዎች ጥሩ አይደሉም ምክንያቱም ቅዱስ ቁርባን ተቀብለናል ብለዉ ግን ደግሞ ይተማማሉ አንዱ ላንዱ ጥሩ ጥሩ አይመኙም ብላ ለካህኑ ነገረቻቸዉ እርሳቸውም ልጄ ኃጥያተኛም እንዳለ ሁሉ ጻድቃንም አሉ ስለዚህ ጻድቃኖችንም ማየት ይኖርብናል ብለዉ ነገሯት ከዚያም ልጇ ከትምህርት ቤት ስትመጣ የእናቷን እና የካህኑን ውይይት ስታይ ደነገጠች ተደሰተችም ከዚያም ዓርብ ቤተክርስትያን እንድትሔድ ቃል አስገባቻት(ዓርብ ያለችበት ምክንያት ግብፅ ውስጥ ዓርብ በሙስሊሞቹ ምክንያት ሰለሚዘጋ እሁድ ደግሞ በክርስያኖቹ ምክንያት ስራ ዝግ ነዉ፡፡ቅዳሜ የስራ ቀን ነዉ፡፡

ከዚያም ዓርብ ደርሶ ቤተክርስትያ ሄዱ ቅዳሴዉ ሲጀመር እናትየዋ ማልቀስ ጀመረች ሙሉ ቅዳሴውን እስኪያልቅ ታለቅስ ነበር፡፡ካህኑ ቅዳሴውን በዓረብኛ ነበር የቀደሰዉ በኮፕት ቋንቋ ከቀደሰ ግን ቋንቋ ከቀደሰዉ ገና ከጅምሩ ላይገባት ስለሚችል ብሎ

የዘማሪ አለማየሁ ኡርጌ ምስክርነት- በፀበል ኃይል ከሞት መዳን

ዘማሪ አለማየሁ ኡርጌ ከአገልግሎት መልስ ባላወቀው ሁኔታ ከባድ ሕመም አጋጠመው::ያጋጠመው ሕመም ግን መፍትሔ እንደሌለው እና እግሩ መቆረጥ እንዳለበት ተነገረው:: በፀበል ኃይል እግዚያብሔር ያደረገለትን ድንቅ ተዓምር ከምስለ ወድምጹ ይከታተሉ::

 

ወንቅእሸት - ሙት አንሳው- ቅዱስ ገብርኤል ገዳም
ሸንኮራ ዩሐንስ ጸበል; አንጀት ካንሰር; ፍቅርተ; የእግር እብጠት

Wednesday, July 30, 2014

ድንቅ ተዓምር በሸንኮራ ቅዱስ ዩሐንስ ጸበል


የተወደዳችሁ የእግዚያብሔር ቤተሰቦች ዛሬ የምንመሰክራላችሁ ተዓምር ለወንድም አንተነሕ ኃይሌ የተደረገለት ሲሆን: ይህ ወንድም በ2005 ዓ.ም ታሞ ወደ ሕክምና ጣቢያ በመሔድ ምርመራ ያደርጋል:: ነገር ግን ውጤቱ አስደንጋጭ ብሎም ያልተጠበቀ ነበር:: የሕክምና ዶክተሩ የአንጀት ካንሰር እንዳለበት ይነግሩታል:: ይህ ብቻ አደለም ሌላ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ነገርም ነገሩት እርሱም በዚች አለም በህይወት ሊቆይ የሚችለው ቢበዛ ለ 3ወር ብቻ እንደሆነም ጭምር ያስረዱታል:: በዚህም አስደንጋጭ ዜና ተስፋ መቁረጥ ቢደርስበትም የተለያዩ ሆስፒታሎች ጋር በመሔድ የሕክምና እርዳታን ይሞክር ጀመር:: ለምሳሌ ኮርያ ሆስፒታል: ተክለሐይማኖት ሆስፒታል: ብሩክ ክሊኒክ ላንድ ማርክ እና ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከሔደባቸው የተወሱኑ የሕክምና ጣቢያዎች ሲሆኑ የተሻላ ነገርን ግን ማግኘት አልቻለም:: በስተመጨረሻ ላይ ግን ወደ እግዚያብሄር መፍትሔዎች አዳኝነት በመመለስ በሸንኮራ ዩሐንስ ጸበል በመጠጣት የእግዚያብሔር አዳኝነትን መጠባባቅ ያዘ:: በዚህ አመት ባደረገው ምርመራ በአሁኑ ግዜ በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ ሲሆን "የካንሰር ስፔሻሊስት" እና የቅዱስ ዩሐንስ ሸንኮራ ጸበል ረድተውኛል" ሲል ቃል በቃል ተናግሯል:: ከዚህ በታች በምታዩት ፎቶ ላይ ዶክመንቶቹን እያሳየ እንዳለ እናያለን::

"እግዚያብሄር በጻድቁ እንደተገለጠ እወቁ..":: መዝ 4:3




Friday, April 25, 2014

ከአፄ ዋሻ ማርያም ገዳም የተሰረቀው ታቦት ከጅቡቲ በተዓምራት ተመለሰ



የእስራኤልን አምላክ ታቦት ስደዱአት፤ እኛንና ሕዝባችንን እንዳትገድል በስፍራዋ  ትቀመጥ፡፡ /1ኛ ሳሙ. 5፤ 12/
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በደብረ ብርሃን አካባቢ ከአፄ ዋሻ ማርያም ገዳም የተሰረቀው የመድኀኔዓለም ታቦት ከጅቡቲ በተዓምራት ተመለሰ፡፡

ከአፄ ዋሻ ማርያም ገዳም የተሰረቀው የመድኀኔዓለም ታቦት ጅቡቲ ውስጥ ለ17 ዓመታት በአንድ ግለሰብ ቤት ተደብቆ ከቆየበት ተዓምራቱን በመግለጡ በተደናገጠው ቤተሰብ ጠቋሚነት፤ ጅቡቲ ለሚገኘው ለምሥራቀ ጸሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን  በማስረከብ ሚያዚያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ተመልሷል፡፡

“በ1938 ዓ.ም. የተቀረጸውና በአፄ ዋሻ ማርያም ገዳም የነበረው የመድኀኔዓለም ታቦት ሐምሌ 28 ቀን 1989 ዓ.ም. የቤተ ክርስቲያኑን በርና መስኮት ተሰብሮ  መሰረቁን ለወረዳው ቤተ ክህነትና ለፖሊስ በወቅቱ አሳውቀን ነበር፡፡ ለማፈላለግ ያደረግነው ጥረት ሁሉ መና ሆኖብን ቆይቷል፡፡ እግዚአብሔር በወደደ ጊዜ ወደ ቤቱ ይመለስ ዘንድ ፈቀደ፡፡” ይላሉ የገዳሙ አስተዳዳሪ ቄስ ኃይለ ጊዮርጊስ መኮንን፡፡

ጅቡቲ እንዴት እንደተወሰደ እስካሁን በግልጽ የታወቀ ነገር እንደሌለ የሚገልጹት የጅቡቲ ምሥራቀ ጸሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስስቲያን አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ዮናስ መልከ ጼዲቅ “ታቦቱ በግለሰቡ ቤት ታላቅ ተዓምራትን ነው ያደረገው፡፡ በቤቱ ውስጥ ደብቆ ያስቀመጠው ግለስብ ሚስት ስታብድ ልጁ ሞቶበታል፡፡ በዚህ የተደናገጠው ሌላው የሰውየው ልጅ በቤታቸው ውስጥ ታቦት እንዳለና ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲወሰድ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ጉዳዩን በመከታተል ከጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲና ከሌሎችም ጋር መረጃ በመለዋወጥ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ችለናል” ብለዋል፡፡

ምንጭ

Wednesday, April 23, 2014

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ድንቅ ተአምር በግብጽ ቤ/ክ

     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የተደረገ ተአምር ይህ ነው::

ለዓይኖቻችን በጣም አስፈላጊ የሆነው ክፍል የእይታ ድራብ ረቲና የሚባለው ነው:: እይታ ድራብ የሌለው ሰው አንዳችም ነገር ማየት አይችልም:: በመሆኑም ዓይነ ስውር ሆኖ ተወለደ ማለት ነው:: እንዲህ አይነቱ አብሮ የሚወለድ በሽታ ሊድን አይችልም:: ማሪና ከተወለደች ከጥቂት ቀናት በኋላ ወላጆቿ ወደ እርሷ ሲቀርቡ ትደናገጥና ማልቀስ ትጀምራለች:: አንድ ቦታ ላይ አትኩራ አለመመልከቷንና ዓይኖችዋ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴን አለመከተላቸውን ወላጆቿ ይገነዘባሉ:: በአጠቃላይ ዓይኖቿ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የላቸውም::

     አራት ወር ሲሞላት ወደ ሕክምና ተቋም ትወሰዳለች:: የምርመራውም ውጤትም በዓይኖቿ ውስጥ የ እይታ ድራብ ስለሌለ ዓይነ ስውር ሆኖ መቀጠል እንዳለባት ያረጋግጣል:: የማሪና ወላጆች ከሌሎች ብዛት ያላቸው የሕክምና ባለሙያዎች ጋር ለንደን ድረስ ሔደው በመገናኘት ቢያስመረምሯትም እይታ ደራብ ስለሌላት ልትድን አለመቻሏን ደግመው ያረጋግጡላቸዋል::

   ከአማላጂቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ቅርርብ ያላቸው የማሪና ወንድ አያት በዚህ ጉዳይ ክፉኛ ያዝናሉ:: ከዚያም ዘይቱን ውስጥ ወደሚገኘው ወደ እመቤታችን ቤተ ክርስቲያን በቀጥታ በመሄድ በስዕሏ ፊት ተንበርክከው በእናቱ አማላጅነት ተደግፈው እግዚያብሔር የልጅ ልጃቸውን ዓይኖች ያበራ ዘንድ በጸሎት ይማጸኑታል:: በጸሎታቸው "የብርሃን እናት ሆይ: ልጅሽ ማሪና ይህን ብርሃን ሳትመለከት እንድትኖር አታደርጊያትም" ይሉ ነበር:: በዚህ ጊዜ አንዲት እማሆይ ትከሻቸውን ነካ ካደረገቻቸው በኋላ በርኅራሄ ቃል "ልቅሶህ ይብቃ! ማሪናን ያዝና ወደ ሴቶች ገዳም ሂድ" ትላቸውና ከዓይናቸው ትሰወራለች::

    ከዚህ በኋላ የማሪና አያት ድንቅ የሆነ የሰላም ስሜት ሲያድርባቸው ይታወቃቸዋል:: አስቀድመው ይህ ገዳም መኖሩን ፈጽሞ ሰምተው ስለማያውቁ ወደዚያ ያቀኑት አቅጣጫውን እየጠየቁ ነበር;; ከቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በመውጣትም ላይ ሳሉም ወደ

Saturday, April 19, 2014

ትንሳኤን በተመለከተ መልክት ከ መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ

 መምሕር ግርማ በሙኒክ የበራቸው ኣገልግሎት እና ውጣ ውረዶች
ከሙኒክ  ደ/ብ/ ቅዱስ ገብርኤል ሰበካ ጉባኤ የተሰጠ መግለጫ



























 የኣዘጋጅ ኮሚቴው ምላሽ




24.10.2014 በ ሙኒክ የተደርገ የብሶት ሰልፍ


የመምህር ግርማ ወንድሙ መልክት በራዲዩ አቢሲኒያ




Sunday, March 30, 2014

ባሕታዊ አባ ገብረ ጊዮርጊስ

ባሕታዊ አባ ገብረ ጊዮርጊስ በቦሌ አየር ማረፊያ ደ/ፀ/ቅ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የተደረጉ የስብከት እና የፈውስ አገልግሎት

Holy water at Entoto Kidane Mihret Church የ እንጦጦ ኪዳነምህረት ጸበል

Thursday, March 20, 2014

ሰበር ዜና - ሕገ ወጥ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን "መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ" በሚል ስያሜ የተበተነው ደብዳቤ ሕገ ወጥ በመሆኑ የሚመለከተው ሁሉ ይህን ግንዛቤ እንዲወስድ አሳሰበች፡፡
በሚል ከዚህ ጋር ተያይዞ የወጣውን እና የተሰራጨውን ደብዳቤ አስነብበናል:: አሁን ከ ከ ቅዱስ ፓትሪያሪኩ  http://www.eotc-patriarch.org/#
 ድኅረ ገጽ በወጣው መግለጫ ደብዳቤው ጥንቃቄ እንዲደረግበት ማሳሰቢያ ተሰጥቷል:: ደብዳቤው ከታች እንደምትመለከቱት ነው::
የቀድሞውን ደብዳቤ በተመለከተ መምህር ግርማ በሬድዮ አቢሲኒያም ሆነ ተከታታይ በወጡት VCD 26 እና 27 ላይ የተናገሩት ነገር የለም:: ደብዳቤውም ወጣ የተባለበት ከአመት በላይ ያለፈው ግዜ 05/19/2005 በዚህ ጉዳይ ላይ መምህር ግርማ ያረጋገጡልን ነገር የለም:: ስለዚህ ይህን አይነት ድርጊት እየሰራ የመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙን ስም ለማበላሸት የሚጥሩ ስላሉ እርሳቸውን ተጠያቂ ከማድረግ እንድንቆጠብ እናሳስባለን:: ሰሞኑን የርሳቸው ቭኢዲዮ ከነድረገጹ ሁሉ በማጥፋት የ እግዚያብሔር ስራ እንዳይተላለፍ እንቅፋት የሆኑ እንዳሉ የምናውቀው ነው:: ከ ሁለት ደርዘን በላይ ምስሎች አሁን በ ንቁ ተአምረ ጽዩን ማየት የሚቻለው የተወሰኑንት ብቻ ነው::

ይህ ድረ ገጽ የተሳሳተ መረጃ በማቅረብ አላስፈላጊ መደነጋገር ውስጥ ስለከተትን ይቅርታ እንጠይቃልን::  የመምህር ግርማ አገልግሎት መስፋፋት እና የሕዝቡን መዳን ስለምንወድ አገልግሎታችንን ከበፊቱ ይልቅ የተጠናከረ እንዲሆን እንተጋለን:: 

መዝ 119: 121 "ፍርድንና ጽድቅን ሠራሁ፤ ለሚያስጨንቁኝ አሳልፈህ አትስጠኝ።"

Thursday, February 27, 2014

መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ ተሰጣቸው

ከዚህ በፊት መምህር ግርማ ወንድሙ ከ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አገልግሎት መታገድ በተያያዘ የቀድሞው የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አስተዳዳሪ መላከ ሰላም ዘላለም እሰይ ስለ መምህር ግርማ ምን ይላሉ? በሚል አገልግሎታቸው የተቋረጠበትን መልካም ያልሆነ ድርጊት እና የመምህር ግርማ ወንድሙን እውነተኛ ማንነት የሚያስረዳ ቃለምልልስ አስደምጠን ነበር:: ከታች በተያያዘው ደብዳቤ ላይ መላከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ የተሰጣቸው መሆኑን ያሳያል::
ደብዳቤው እንደሚከተለው ይነበባል
ቀን 26/12/2005
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ የወንጌል አገልግሎትና እንዲሁም የሕሙማን ሐብተ ፈውስ እንዲሰጡ ከብጹዕ ወቅዱስ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልካም ፍቃድ የተፈቀደልዎት ሲሆን ይህን አውቀው በፍቅር በሰላም እንዲያገለግሉ እናስታውቃለን::
በክርስቶስ ሰላም
ተጨማሪ መረጃ
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13144
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ማናቸው?

VDC part 26 ወጥቷል::

የቀድሞው የእገዳ ደብዳቤ

በሮም ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የተላከ ደብዳቤ 25/09/2006



Friday, February 21, 2014

ተዓምረኛው ንቡ ሚካኤል ቤተክርስቲያን


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

“የእግዚአብሔርን ሥራ በምድር ያደረገውን ታምራት እንድታዩ ኑ” መዝ. 45፡8
በንብ መንጋ የተከበበው የበሻሌ (ንቡ) ቅ/ሚካኤል፣ ቅ/እስጢፋኖስ እና ወአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ቤተክርስቲያን አመሰራረትና ገቢረ ተዓምራት አጭር መግለጫ

ቤተክርስቲያኑ ከመመስረቱ በፊት በቦታው ላይ ሲከናወኑ የነበሩ ልዩ ልዩ ታምራት፡-
1. ለብዙ ዓመታት ከተለያየ ቦታ ተጣልተው የነበሩ ምዕመናን ቦታው ላይ እየመጡ እርቀ ሰላም ሲፈጽሙበት ኖረዋል፤
2. ቤተክርስቲያኑ ከተተከለበት ቦታ ትልቅ የጽድ ዛፍ ላይ የሚወጣው ሙጫ እንደ እጣን ጢስ ሽታ ለብዙ ዓመታት አካባቢውን መዓዛው (ሽታው) ያውድ ነበር፡፡



3. በዚሁ ቦታ ላይ ሌሊት ሌሊት የመላዕክት ዝማሬ (ጣዕመ ዜማ) የከበሮ ድምጽ ይሰማ እንደነበረ በዕድሜ የገፉ የአካባቢው አዛውንቶች ተናግረዋል፡፡
4. በአካባቢው ከሚኖሩ ምዕመናን መካከል በመልካም ስራቸው የታወቁና ከ90 ዓመት በላይ ዕድሜ የነበራቸው እናት የቅዱስ ሚካኤል ታቦት (ጽላት) እንደሚተከል በተደጋጋሚ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ይናገሩ ነበር፡፡
5. ቀደም ሲል በእነ አብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት አካባቢ ጀምሮ ከተለያየ አካባቢ የሞቱ አባቶች አስከሬናቸው እየመጣ ሥርዓተ ቀብር ሲፈጸምበት የቆየ እና በተለያየ ጊዜ የቀስተ ደመና ብርሃን በመቃብሩ ላይ ይታይ እንደነበር በአካባቢው የሚኖሩ በዕድሜ የገፉ አዛውንቶች በግልጽ መስክረዋል፡፡ ዛሬም መቃብሩ በግልጽ ይታያል፡፡ ይህ ሁሉ ታሪክ ሲከናወን ከቆየ በኋላ እግዚአብሔር የፈቀደው ጊዜ ሲደርስ በአካባቢው ከሚኖሩ በዕድሜ ከገፉ አዛውንቶች መካከል በአንድ አርሶ አደር ምዕመን አማካኝነት በእግዚአብሔር ፈቃድ በተደጋጋሚ ራዕይ ተገልጾላቸው ያርሱበት የነበረውን ይዞታቸውን መሬት ለዚህ ታቦት መትከያ ቤተክርስቲያን እንዲሰራ መሬት በመስጠት አሁን በሚገኘው መቃኞ ቤተክርስቲያን ግንቦት 12 ቀን 2001 ዓ.ም ታቦቱ ሊገባ ችሏል፡፡
በቤተመቅደሱ ስለሚገኘው የንብ መንጋ አገባብ (አመጣጥ)

Saturday, January 4, 2014

Aba Sahle Mariam, a 110years old Ethiopian monk who died while he was praying in a cave.

Aba Sahle Mariam, an Ethiopian monk who died while he was praying in a cave. His body estimated to be 110years old is still intact having well recognizable features. He was kneeling down praying the moment he passed away.