Showing posts with label ሸንኮራ ዩሐንስ ጸበል;. Show all posts
Showing posts with label ሸንኮራ ዩሐንስ ጸበል;. Show all posts

Friday, July 8, 2016

የሸንኮራው ዮሐንስ ተነግሮ የማያልቀው ተአምር!!!!!!!!!



ሰውነቴ በለምጽ የተመታው ነፍስ ሳላውቅ በህጻንነቴ ነው የምትለዋ የጎንደርዋ አጸደ ማርያም ነፍስ ሳውቅ ማፈር ጀመርኩኝ ትምህርቴንም አቁዋርጩ ወደ መሐል ሐገር መጣው ሰው ቤት ለመግባት ማን ይቅጠረኝ ፊቴን ሲያዮ ይደነግጣሉ ከሰው ተጠግቼ በቆሎ መሸጥ ጀመርኩኝ የዛሬ አመት ክረምቱ ሲገባ አንዲት ሴት ልትገዛኝ መጥታ ስለ ሸንኮራ ነገረችኝ አቅም የለኝም ለመሄድ ስላት ጸበልና እምነቱን ሰጠችኝ ማታ ሰውነቴን ተቀብቼው አደርኩኝ አታምኑኝም ለድህነቴ ምክንያት ሁለቱም እጆቼ ጠዋት ስነሳ ሌላ መልክ አምጥተዋል ደነገጥኩኝ ሰው ሲያየኝ ደነገጠ ምን መድሐኒት ነው አሉኝ ጨርቄን ማቄን ሳልል ሸንኮራ መጣው መጥምቁ ምን ተስኖት ሰውነቴ በሙሉ ዳነ ከሰው እኩል አቆመኝ አዲስ አበባ ስመጣ የሚያውቁኝ ጠፋውባቸው መላ አካሌ በለምጽ ተመቶ ነበርና ስድን አዲስ ሌላ ከለር ሌላ ሰው ሆንኩኝ መጥምቅዬ ከጌታው አማልዶ ምንም የማላወቀውን በሸንኮራው የሰርክ ጉባኤ ትምህርት ለንስሐ ለስጋ ወደሙ በቃው እደጁ ያወቁኝ እናት በግል ሆቴላቸው ቀጥረውኝ ጥሩ ደሞዝ አገኛለው ከዝናብና ብርድ ዳንኩኝ ትላንት በበዓሉ ግቢው በእልልታ ስታቀልጥ ነበህ እህታችን እኔን የዳበሰ የዮሐንስ አምላክ ሁላችሁን ይዳብሳችሁ ትላለች አሜን

ተአምር በ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ከርስቲያን /ሽሬ/