Showing posts with label ረቲና የተፈጠረላት ማሪና. Show all posts
Showing posts with label ረቲና የተፈጠረላት ማሪና. Show all posts

Wednesday, April 23, 2014

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ድንቅ ተአምር በግብጽ ቤ/ክ

     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የተደረገ ተአምር ይህ ነው::

ለዓይኖቻችን በጣም አስፈላጊ የሆነው ክፍል የእይታ ድራብ ረቲና የሚባለው ነው:: እይታ ድራብ የሌለው ሰው አንዳችም ነገር ማየት አይችልም:: በመሆኑም ዓይነ ስውር ሆኖ ተወለደ ማለት ነው:: እንዲህ አይነቱ አብሮ የሚወለድ በሽታ ሊድን አይችልም:: ማሪና ከተወለደች ከጥቂት ቀናት በኋላ ወላጆቿ ወደ እርሷ ሲቀርቡ ትደናገጥና ማልቀስ ትጀምራለች:: አንድ ቦታ ላይ አትኩራ አለመመልከቷንና ዓይኖችዋ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴን አለመከተላቸውን ወላጆቿ ይገነዘባሉ:: በአጠቃላይ ዓይኖቿ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የላቸውም::

     አራት ወር ሲሞላት ወደ ሕክምና ተቋም ትወሰዳለች:: የምርመራውም ውጤትም በዓይኖቿ ውስጥ የ እይታ ድራብ ስለሌለ ዓይነ ስውር ሆኖ መቀጠል እንዳለባት ያረጋግጣል:: የማሪና ወላጆች ከሌሎች ብዛት ያላቸው የሕክምና ባለሙያዎች ጋር ለንደን ድረስ ሔደው በመገናኘት ቢያስመረምሯትም እይታ ደራብ ስለሌላት ልትድን አለመቻሏን ደግመው ያረጋግጡላቸዋል::

   ከአማላጂቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ቅርርብ ያላቸው የማሪና ወንድ አያት በዚህ ጉዳይ ክፉኛ ያዝናሉ:: ከዚያም ዘይቱን ውስጥ ወደሚገኘው ወደ እመቤታችን ቤተ ክርስቲያን በቀጥታ በመሄድ በስዕሏ ፊት ተንበርክከው በእናቱ አማላጅነት ተደግፈው እግዚያብሔር የልጅ ልጃቸውን ዓይኖች ያበራ ዘንድ በጸሎት ይማጸኑታል:: በጸሎታቸው "የብርሃን እናት ሆይ: ልጅሽ ማሪና ይህን ብርሃን ሳትመለከት እንድትኖር አታደርጊያትም" ይሉ ነበር:: በዚህ ጊዜ አንዲት እማሆይ ትከሻቸውን ነካ ካደረገቻቸው በኋላ በርኅራሄ ቃል "ልቅሶህ ይብቃ! ማሪናን ያዝና ወደ ሴቶች ገዳም ሂድ" ትላቸውና ከዓይናቸው ትሰወራለች::

    ከዚህ በኋላ የማሪና አያት ድንቅ የሆነ የሰላም ስሜት ሲያድርባቸው ይታወቃቸዋል:: አስቀድመው ይህ ገዳም መኖሩን ፈጽሞ ሰምተው ስለማያውቁ ወደዚያ ያቀኑት አቅጣጫውን እየጠየቁ ነበር;; ከቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በመውጣትም ላይ ሳሉም ወደ