Tuesday, July 26, 2016

ድንቅ ተአምር በሽንቁሩ ቅድስ ሚካኤል

ዛሬ ኪዳነ ምህረት በእለተ ቀኗ በሽንቁሩ ቅድስ ሚካኤል ፅበል ስፍራ የተደረገ ድንቅ ተአምር .
የእግዚአብሔር ድንቅ ተአምር ለዓለም ይመስክሩ..!!!

እንደምን ከረማችሁ ወዳጆቼ ባለፈው የራሴን ታምር መስክሬላችሁ ነበር አሁን ደሞ እኔ ከተከራየሁበት ቤት አጠገብ የምትጠመቅ በ አለም ስሙዋ ወይዘሮ ማሬ የተባለች የ ቅዱስ ሚካኤል ወዳጅ በ ሽንቁሩ ደብረ መድሀኒት ቅዱስ ሚካኤል ፀበል የተደረገላትን ድንቅ ታምር እንደዚ ትናገራለች ለዘመናት እግሩዋን እያስነከሰ በጣም ያሳምማት ነበር የምትሰራው የምግብ ስራ ስለነበር እሱዋ ግን እረጅም ሰአት የምትቆምበት ነበር የመሰላት ነገሩ ግን ወዲህ ነው በ ቅርብ በጓደኞችዋ የተሰራባት መተት ነበር ቆማ እንዳትሰራ እና እንደልብ እንዳትራመድ ነበር የተፈለገው ታድያ በ ቅዱስ ሚካኤል ምልጃ ፀበሉን ለ 4 ወር ስትጠመቅ ቆይታ ዛሬ በ16/11/2008 ዓ.ም ከ ቀኝ እግሩዋ ላይ አንድ ባለ ኮፍያ ሚስማር በ ስስ ላስቲክ ተጠቅልሎ ወጥቶላታል። የሚደንቀው ነገር ሚስማሩ ሲወጣ ምንም የህመም ስሜት አልነበረውም ደምም አልነበረውም እኔን የፈወሰ መላኩ ቅዱስ ሚካኤል እናንተንም ይርዳ ትላለች።
ወ/ሮ ማሬን ማግኘት እና መርዳት ለምትፈልጉ
+251920 34 3349 ደውለው ማረጋገጥ ይችላሉ።
የቅዱስ ሚካኤል አምላክ ይክብር ይመስገን።
ይህን ድንቅ ተአምር ለአለም ይመስክሩ ዘንድ በቅዱስ ሚካኤል ስም እጠይቃለው።
Source: Memher Pawlos Melkea Selasie

No comments:

Post a Comment