Wednesday, October 15, 2014
Tuesday, September 30, 2014
በልበሌቲ ጽጌ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን
በልበሌቲ ጽጌ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከአዲስ አበባ 418 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።
ቦታውም ለመድረስ ከአዲስ አበባ በናዝሬት፣ አሰበ ከዛም በበዴይሳ አድርገው ወደ ገለምሶ ይጓዛሉ በመጨረሻም
ቤተክርስቲያኑ የሚገኝበት በልበሌቲ መሻገር ይኖርቦታል። መንገዱ ለማንኛውም መኪና ምቹና ቤተ ክርስቲያኑም መንገድ
ዳር በመሆኑ ምንም እንግልትና የእግር ጉዞ የለውም።
ይህ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘው በምዕራብ ሐረርጌ ሐብሮ ወረዳ በልዩ ስሙ በልበሌቲ በመባል በሚታወቀው መንደር ሲሆን ለምዕራብ ሐረርጌ የመጀመሪያው ቤተክርስቲያን ነው። የተተከለውም በእምዬ ምንሊክ በፊታውራሪ ዘመንፈስ በ1870 ከአርሲ እያስገበሩ ሲመጡ በምዕራብ ሐረርጌ ሲያልፉ እንደተከሉት ይነገራል። ቤተ ክርስቲያኑ ሲዘዋወር አሁን ያለበት ቦታ ሰባተኛው ሲሆን እምዬ ምንሊክ ለቤተ ክርስቲያኑ የሰጡት ርስት 18 ጋሻ መሬት ቡሩሪ በሚባል ቦታ ህንጻውም ባለ ደርብ(under ground) የሆነ ነበር። በጣልያን ወረራ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ በመቃጠሉ ከተሰጠው ርስት በመነሳት በሽሽት ቀርጫ የሚባል ጫቃ ውስጥ ለ 5 ዓመት ስብሐተ እግዚአብሔር ሲደርስ ቆይቷል። በዚህ ወቅት ያ 18 ጋሻ መሬት የለውም እዛ ቦታ ላይ ሌሎች ሁለት ቤተ ክርስቲያን ታንጸው እሱ የሚገኘው ሌላ አዲስ በተመራው ቦታ ላይ ነው። በዚህ ቤተ ክርስቲያን የሚነግሱ ታቦታት ሶስት ሲሆኑ እነሱም ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚያዚያ 23ና ጥር 18፣ ኪዳነ ምህረት በየካቲት 16፣ ሩፋኤል በጷግሜ 3 ይነግሳሉ።
ደብሩን ምን ልዩ ያደርገዋል
ስለት ሰሚነቱ
በአገር ውስጥም ከአገር ውጪም ባሉ የአካባቢው ሰዎች የበልበሌቲው ጊዮርጊስ አንተው ስለቴን ፈጽምልኝ ብለው የተሳሉ ሁሉ ላመኑት ክርስቲያኖች ብቻ ሳይሆን ከክርስናው ውጪ ላሉትም ሰዎች እንኳ ሳይቀር ስለታቸው ደርሶላቸው በድብቅ (ሰው በመላክ) በግልጽም (ራሳቸው በመምጣት) ስለታቸውን ይልካሉ። በሐኪም እንደማይወልዱ የተነገራቸው፣ ትዳር ያጡ፣ በህመም የሚሰቃዩ፣ ውስብስብ ችግር የገጠማቸው፣ ብዙ ብር ጠፍቶባቸው የነበሩ ሌሎች ሌሎችም የህይወታቸው እንቆቅልሽ ተፈቶላቸው አምላከ
ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ?
የኢንተርኔት አገልግሎት ፈጣን ባልሆነበት ቦታ
በአማራጭነት ይህንን በጽሑፍ መልክ ያንብቡ:: ረጅም ትምሕርት ሲሆን በተቻለ መጠን በቂ መልክቱን በጽሑፍ
አቅርበናል:: የቃላት ግድፈት ካለ እያረሙ እንዲያነቡ እንጋብዛለን::
የጸሎት ቦታ እንዴት ላዘጋጅ?
ክፉንና
ደጉን ለመለየት አምልኮ ያስፈልጋል:: አምልኮ የሌለበት ህይወት አለም ላይ የወደቀ ነው ስለዚህም የአምልኮት ራእይ
አንድ ክርስቲያን ሊኖረው ይገባል:: ማምለክ ማለት እግዚያብሔርን ከልብ መውደድ: ቃሉን በልቦና ማኖር: እና መጠበቅ:
እርሱን ተስፋ ጉልበታችንን ማድረግ ነው:: በተግባር ደግሞ ኑሮን ጠባይን ለእግዚያብሔር መስጠት: ውስጣዊ ህይወታችንን
ለክብሩ የተዘጋጀ ማድረግ :: ስለ ሐጢአታችን ንሰሐ ገብተን ሥጋውና ደሙን መውሰድ: እለት እለት ስለበደላችን
ስለሐጢአታችን ለእግዚያብሔር መንገር:: እለት እለት እግዚያብሔርን የምናመሰግንበትን ግዜ ካገኘን የአምልኮት
ሕይወት ገበና አለን ማለት ነው:: ሰብአ ሰገል ክርስቶስን በፍቅር ፈልገው እንደመጡ አንድ ክርስቲያንም ክርስቶስን
ፈልጎ መምጣት አለበት:: በአምልኮት ባሕርይ ሔሮድስን ማለፍ ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ነው:: ሔሮድስ ማለት የዚህ
አለም ነገሮች ናቸው እነዚህም :የአለምን ሰዎች እውቀት: ሳይንስ እግዚያብርሔን የሚከለክል : የድንግል ማርያም ልጅ ክርስቶስን
የሚከለክል ነው:: ሔሮድስ ማለት ሐብት : ስልጣን: ማዕረግ የመሳሰሉት እነዚህ ሁሉ የሔሮድስ መንገድ ጠቋሚ
ናቸው:: ሰዎች የጥፋት ሞት ውስጥ የሚገቡት የአምልኮት ሕይወት በማጣት ነው:: እግዚያብሔርን የሚፈልጉ ሰዎች ሔሮድስ
ጋር መቅረት የለባቸውም:: ኮከቡን ማየት አለባቸው ኮከቡም ያለው በሰማይ ነው::
ብዙ
ክርቲያኖች ወደ እግዚያብሔር ቤት አይሔዱም ወይም ወደ ሰማይ ቀና አይሉም:: በዚህም ወደ ልባቸው የሚሔድባቸው
መጣባቸው:: ሰይጣን ወደ ቤታቸው ወደ ኑሮአቸው ወደ ሕይወታቸው መጣ:: በዚህ ዓለም ገለልተኛ ሆኖ መኖር አይቻልም:: በዚህ
አለም ሁለት ነገር ነው ያለው:: ጽድቅና ኩነኔ: ጨለማና ብርሃን: ሓጢአትና ጽድቅ: ሰላምና ጦርነት::ከፈለክ ወደ
ብርሃን ካልፈለክ ወደ ጨላማ: ከፈለክ እውነት ካልፈለክ ሐሰት: እንዲህ በጥንድ የተያያዘ ነው:: የእግዚያብሔርን
በቅድምያ ከሰማን የእግዚያብሔር ጽድቅ ይገለጥልናል: የሰዎችን ከሰማን ሁል ግዜ እንደተደናገግርን ተስፋችንን
በአልሆነ አቅጣጫ እየጠበቅን እንኖራለን:: ሔሮድስ ክፉ መሆኑን የምናውቀው ስናመልክ ነው::
የጸሎት ቦታ

ራእይን
ምሪቱን ለማግኘት ደግሞ የጸሎት ቦታችን ላይ ለባልና ሚስት የመኝታ ያህል መኖር አለበት: ቤተሰብ ካለው ከሌለው
Tuesday, September 2, 2014
Subscribe to:
Posts (Atom)