Wednesday, February 1, 2017

የእመቤታችን ድንቅ ተአምር

ከዚህ በታች የምታነቡትን ድንቅ ተአምር ያደረገችው የእመቤታችን ስዕለ አድህኖ በሀገራችን በኢትዮጵያ ሰበታ ቤተ ደናገል ጠባባት አንድነት ገደም (ጌቴሰማኔ ማርያም) የሚገኝ ሲሆን ምስለ ስእሏን በ ፎቶም ሆነ በቪድዮ ማንሳት ለክብሯ ሲባል የተከለከለ ነው፡፡ ይህ የምታዩት ግን እዛው ሰበታ መድኃኒአለም ቤተክርስትያን ውስጥ ይገኛል፡፡ ይህችን ተአምረኛ ምስለ ስእል እንዴትና ማን እንዳመጣት እንዲሁም የሰራችውን ተአምር እዛው ሄደው እንዲሰሙና እንዲያዩት እጋብዛለሁ፡፡
(በድጋሜ ፨ እባካችሁ አንተ ታዲያ ፎቶውን እንዴት አነሳኽው ለምትሉ፤ ይሄኛው ሌላ ነው አሳሳሉ ግን ይሄን ታሪክ መሰረት አድርጎ ነው። ተአምረኛዋ ምስለ ስዕል ግን አንድ አጥማቂ አባት (ቡኃላ አቡነ የተባሉ) በቦርሳቸው ይዘዋት ይዞሩ የነበሩ የጣሊያን ጦር ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጥይት ያልጎዳት መጽሐፍ ቅዱስ ነው ምታክለው። ገዳማውያን እናቶች አክብረው አስቀምጠዋታል)

ተአምሪሃ ለእግዝዕትነ ቅድስት ድንግል በ ፪ኤ ማርያም ወላዲተ አምላክ ጸሎታ ወበረከታ የሃሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን ልመናዋ ክብሯ በእኛ ለዘላለም በውነት ይደርብንና አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች ክብርት እመቤታችን ያደረገችው ተዓምር ይህ ነው። አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች ክብርት እመቤታችን በሥዕሏ አድራ ያደረገችውን ተዓምር ስሙ ።
ከአፍርንጊያ አገር ( ከአፍሪካ )ማለት ነው በከበረ ልብስና በወርቅ በብርም እጅግ የከበረ አንድ ነጋዴ ነበር ። ያም ሰው ሥጋ የለበሰች የምትመስለውን አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች የክብርት እመቤታችንን ሥዕል ዜና በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው ። ገንዘቡን ሁሉና ንግዱንም ትቶ ደኃ መስሎ ወደ ጼዴንያ አገር ሄደ ሥዕሏንም ሠርቆ ወደ አገሩ አፍርንጊያ (አፍሪካ) ይወስዳት ዘንድ ይህንን ምክኒያት አደረገ ሥዕሊቱንም አግኝቶ ወደ አገሩ ይወስዳት ዘንድ የተጠረገ መንገድን ሊያገኝ ደጅ እየጠና በጼዴንያ የተሠራች የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ዓመት ያህል ሲያገለግል ኖረ ። እመምኔቲቱ ግን የመነኮሳቱን በር በፍፁም ትጋት ትጠብቅ ነበርና ሥዕሊቱን ይወስዳት ዘንድ እንዳልተቻለው ባወቀ ጊዜ ሾተልን ይዞ እጁን በመስኮት አዝልቆ ከሥዕሊቱ የሥጋ ቁራጭን ያህል ቆረጠ ያን ጊዜም ከሥዕሊቱ ደም ወጣ ። እርሱም የሥጋ ቁራጭን ያህል ይዞ ወጥቶ ተሠወረ ። ያን ጊዜም ሰዎች አውቀው በጭንቅ ፈልገው አግኝተው ያዙት ይገድሉትም ዘንድ ወደዱ ። ያን ጊዜም ከሥዕሊቱ እንዲህ የሚል ቃል ተነገረ "" እኔን ስለ መውደዱ ክብር ሊሆነው ወስዷል እንጂ ይህንንስ በክፋት አላደረገውምና ተዉት አትግደሉት ነገር ግን የተቆረጠውን ሥጋ ከእርሱ ወስዳችሁ ከተቆረጠበት ቦታ ግጠሙት "" ያን ጊዜም እንዲሁ አድርገው አኖሩትና ሥጋው ተጣብቆ ቀድሞ እንደነበረ ሆነ ነገር ግን የደምና የሾተሉ ፍለጋ ምልክቱ እስከዛሬም ድረስ ታውቆ ታይቶ ይኖራል ። በአርያም ለሚመሰገን አምላክን በወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ በፀናች በክብርት እመቤታችን አማላጅነትም ይህንን ተዓምር ለገለጸ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል ። ልመናዋ ክብሯ አማላጅነትዋ የልጅዋ የወዳጅዋም ቸርነት በእኛ ለዘለዓለም በውነት ይደርብን ። አሜን

የእመቤታችን መቃብርና ያረገችበት ጣራ - Tomb of The Virgin Mary

"የጎጆዋ አርሴማ" - ድንቅ ነገር


☞ እንሆ በአዲስ አበባ በቦሌ ቡኒ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነ ድንቅ ነገር !!!!!! እንዲህ ሆነ በ ጥር 10 2009 ዓ ም የጥምቀት በዓለ ክብር ከተራውን ፈጽመን እንሆ በ 13 የቅዱስ እግዚአብሄር አብ , ቅድስት ኪዳነምህረት ,ተክልዬ, አና አርሴምዬን አጅበን ወደ መንበረ ክብሩ ደረስን ስርአተ ቤተክርስቲያኑን አከናውነን በእግዚአብሔር ፈቃድ እና በአባቶች ራዕይ ጽላቷ የመጣችው ቅድስት አርሴማ በድጋሚ ከገዳማውያን አባቶች የተነገሩትን መልእክት በአውደ ምህረት ተናገሩ እንዲህ አሉ "ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ጥንታዊ ለዛ ያለው ጎጆ ቤተክርስቲያን ሰርታችሁ በዛ አስገቡኝ " ብላለች ብለው ራዕዩን ተናገሩ ፡፡





ከዚህ በኀላ ማሳረጊያ ጸሎት ተደርጎ ታቦታቱ ወደመንበረ ክብራቸው ሲገቡ የቅድስት አርሴማን ያከበሩት አባት ተፍገመሙ ምን አልባት እረጅም መንገድ ስለተጓዙ ይሆናል በሚል ሌላ ካህን ተቀየሩ እንዲሁ እኒህ አባት ተንቀጠቀጡ በዚህ ጊዜ ምዕመናን በለቅሶ በዋይታ ተንበርክከው ማልቀስ ጀመሩ በዚህ ጊዜ ካህኑ ወደ ኀላ መልሳቸው እኛም ታቦቱን በማጀብ በእግዞታ ተከተልን በቅጽረ ቤተክርስቲያኑ ውስጥ በስተ ምስራቅ በኩል በጣም ቆንጆና ደልዳላ ቦታ ላይ ስትደርስ ካህኑን አቆመቻቸው በዚያች ቦታ ጸሎት ተደርጎ መሰረት ተጣለ ፡፡ ከዚህ በኀላ በነባሩ ቤተክርስቲያን በረንዳ ላይ ድንኳን ተጥሎ ታቦቷ በዛ አደረች እስካሁን በዛው ትገኛለች ፡ በአለቱ በተገኘው ገቢ እና በበጎ አድራጊዎች ታግዞ ጎጆ ቤትዋ በመሰራት ላይ ትገኛለች እንግዲህ በሰማዕቷ መልካም ፈቃድ በቀን 28/05/09 ዓም ጸሎተ ምህላ አድርሰን ቅዳሴ ቤቷን ለማክበር በዝግጅት ላይ እንገኛለን የሰማዕቷ ወዳጅ የሆነ ሁሉ በቤቷ እንድትገኙ ጥሪዋን ታስተላልፋለች ፡፡ታዋቂው እና ፈዋሹ የሰማዕቷ የማር ጸበል እንዳያመልጣችሁ ይህም ከመቅደሳ የተገኘ ነው ፡፡እንዲሁም ሀብተ ፈውስ ባላቸው አባት በመምህር አብርሃም የጸበል አገልግሎት ይሰጣል ፡፡ አድራሻ ከጎሮ ወደ ቱሉዲምቱ በሚወስደው መንገድ ላይ ሁለተኛውንና ትልቁን ድልድይ ሳይሻገሩ አስፋልቱ ዳር ላይ ይገኛል እግዚአብሔር አብ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ፡፡ለበለጠ መረጃ 0913511802 ወይም 0936451511ይደውሉ፡፡ በተጨማሪ ☞መንፈሳዊ ጉዞ የምታዘጋጁ መንፈሳዊ ማህበራት አና የቤተክርስቲያን ልጆች ወር በገባ በ 6 ወደዚህች የበረከት ደብር በሆነች ምዕመናንን እንድታስጎበኙልን እና ምዕመናንን የበረከቱ ተካፋይ ታደርጓቸው ዘንድ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች ቤተክርስቲያናም ማንኛውንም መንፈሳዊ ተግባራት ታከናውናለች ፡፡የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ በረከት ይደርብን አሜን፡፡
ጸሐፊ ዲ/ን ኤርምያስ ግርማ


የቅድስት አርሴማ አዲስ ፀበል


Wednesday, January 4, 2017

የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፀበል

ይህ የምታዩት የተአምረኛው የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፀበል ነው። ይህ ፀበል ብዙ ድውያንን ከተለያዩ ሀገራት ዝናውን ታሪኩን በመስማት እየመጡ ከበሽታቸው ፀበሉን በመጠመቅ፣በመጠጣት ብዛት ያላቸው ሰወች ከስቃያቸው ተፈውሰዋል።

ፀበሉ የሚገኝበት አካባቢ በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን  በቋራ ወረዳ በበርሚል ቀበሌ ይገኛል። ሽር በማድረግ በሰማዕቱ ስም ይተባበሩን የሰማዕቱ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።

Tuesday, December 27, 2016

በሻሌ ንቡ ቅ/ሚካኤል - Video

ዋካ ቅድስ ጊዮርጊስ ገዳም

በ15ክ/ዘመን የተመሰረተው አብነ ጵጥሮስ የቀደሱበት የባረኩት በደመና የመጣ ታቦት ቀድሞ ከ15ክ/ዘመን በፊት/ መንዝ ዋካየአብይ ገብረመንፈስቅድስ ገዳም/ ሲሆን 15ክ/ዘመን ላይ ዋካ ቅድስ ጊዮርጊስ ገዳም ተብላል፡፡በጣም ስለት ሰሚ ነው፡ጣልያን በወረረን ግዜ ቦንብ ጥለው ቤተክርስቲያኑን ሊያቃጥሉ ቢወረወሩ ቤተክርስቲያኑ አልቃጠል ሲላቸው ሰውን ፡ካህኑን እየገደሉ ቤተክርስቲያኑ አልቃጠል ሲላቸው የታቦቱን መጎናጸፍፊያ ለብሰው ሲሂድ ከዋካ ከቦታ አልፈው ሂደው ጉርሙኝ ቆላውየ4ሰዓት መንገድ ልብሱን ለብሶ ለብሰው ጣሊያኖቹ ሲሂድየአካባቢው ሰው /አቶ ተገኝ/የሚባሉ ሰው ይህ በምታዩት ጋሻ በመከት ጣሊያኖቹን በመግደልና ገደል በመክተት የጊዮርጊስ መጎናጸፊያ አስመልሰው መጎናጸፊያው(ልብሱ ):በዋካ ጊዮርጊስ ይገኝል፡፡

 




አቶ ተገኝ ጀግና ተብለው የደጃዝማች መሀረግ ሲሰጣቸው ቁረብ ሰጋወ ደሙ ተቀበሉ ሲላቸው በመንዝ አካበቢ ጀግና ሲሞት ቀረርቶ ;ይሸለላል;ይፎከራል ይህ ሳይደረግ ጀግና አይቀበርም፡፡እና አቶ ተገኝ ቁረብ ሲባሉ እኔን ጊዮርጊሰ ጀግና አርጎ ጠላቱን ገድይ ልብሱን አስመልሻለሁ እና ቁርባኑን ሰጋ ደሙን ጊዮርጊሰ ያቀዋል፡ሳይሸለልልኝ ሳይፋከርልኝ ብለው በ110አመታቸው ሞቱ፡፡ የሚገርሙአባት ናቸው በጀግና አሟሟትየተፋከረ፡እየተሸለለ በጀግና አቀባበር በ110አመታቸው አርፈዋል፡፡ስለት ሰሚው ዋካ ጊዮርጊስ የዱሮው ቤተክርስቲያንሳይፈርስ ሌላ ቤተክርስቲያን በመሰራት ላይ ሲሆን መርዳት ለእግዚአብሔር ማበደር ሲሆን ስለት ሰሚውን ዋካን በምንችለው አቅም እንርዳ የቤተክርስቲያኗ መሰረቱ በመሠራት በመውጣት ላይ ነው፡፡በረከቱ በያለንበት ከጊዮርጊሰ ይደርብን፡፡አሜን
ቦታው-+መንዝ ዘብር ገብርኤል ከአ/አ 260ኪሜ ሲሆን ከዘብር የ4ሰዓት መንገድ ሲሆን 4wdመኪና ቦታው ድረስ ይገባል ሜዳ ቀላል መንገድ ነው፡፡

Sunday, November 27, 2016

በራእይ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደሚገኝ የታየው ታቦት ተገኘ

ቅ/ሚካኤል ሚዛንና ሰይፍ ይዞ በዩኒቨርሲቲው ፩ኛ በር በኩል እየወሰደ ያሳየኛል፡፡”
/ታቦቱ መኖሩን የጠቆሙት ባለራእዩ ባሕታዊ በለጠ ዘነበ/
*                    *                    *
aau-st-michael-ark
 
(አዲስ አድማስ፤ ዓለማየሁ አንበሴ፤ ቅጽ ፲፮ ቁጥር ፭፻፹፤ ቅዳሜ፣ ኅዳር ፲፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም.)
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ ሙዝየም ውስጥ፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረ ታቦት የተገኘ ሲኾን፤ ታቦቱ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንደተመለሰ ታውቋል፡፡
በዩኒቨርሲቲው ግቢ ታቦት ስለመኖሩ፣ “ራእይ ታይቶኛል” የሚሉ ባሕታዊ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ባስታወቁት መሠረት፣ ጥናት ተደርጎ መኖሩ በመረጋገጡ፤ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ብዙ ድርድር ከተደረገ በኋላ፣ ኅዳር 10 ቀን 2009 ዓ.ም.፣ ታቦቱ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት መመለሱን በጉዳዩ ተሳታፊ የነበሩት መጋቤ ምሥጢር ቡሩክ አሣመረአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
“ታቦቱ በዐፄ ኃይለ ሥላሴ ጥያቄ እንደተቀረፀና የቅዱስ ሚካኤል ታቦት መኾኑን የሚገልጽ ማስታወሻ ተገኝቷል፡፡ ታቦቱ ከ68 ዓመት በላይ ዕድሜ እንዳለውም ታውቋል፤” ብለዋል – መጋቤ ምሥጢር ቡሩክ፡፡
ታቦቱ በዩኒቨርሲቲው ስለመኖሩ፣ ባሕታዊ በለጠ ዘነበ የተባሉ በራእይ ታይቶኛል በሚል በተደጋጋሚ ሲናገሩ እንደነበር የጠቆሙት መጋቤ ምሥጢር ቡሩክ፤ “ቅዱስ ሚካኤል ሚዛንና ሰይፍ ይዞ በዩኒቨርሲቲው ካምፓስ አንደኛ በር በኩል እየወሰደ ያሳየኛል፤” እያሉ ይናገሩ እንደነበርና፣ ይህንንም በ2003 ዓ.ም. አካባቢ ለፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ መግለጻቸውን፤ ነገር ግን ትኩረት የሚሰጣቸው ሳያገኙ መቅረታቸውን ያስታውሳሉ፡፡

ባሕታዊው፣ በ2007 ዓ.ም. ይህንኑ ራእይ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ማሳወቃቸውንና የሚመለከታቸው የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የሥራ ሓላፊዎች ጉዳዩ እንዲጠና ማዘዛቸውን መጋቤ ምሥጢር ቡሩክ አውስተው፣ በጥናቱም ጽላቱ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ መኖሩ መረጋገጡን ገልጸዋል፡፡ ይህን ተከትሎም ታቦቱ ለቤተ ክርስቲያንዋ እንዲመለስ ከዩኒቨርስቲው ጋር በርካታ የደብዳቤ ልውወጦች ተደርገዋል፡፡
መጀመሪያ ላይ ዩኒቨርሲቲው የጥናትና ምርምር ተቋም እንደመኾኑ፣ ቅርሶችን ተከባክቦ የመያዝና ለትውልድ የማስተላለፍ ሓላፊነት እንዳለበት በመግለጽ፣ ታቦቱን ለቤተ ክርስቲያንዋ ለመመለስ በእጅጉ ተቸግሮ ነበር፤ ይላሉ መጋቤ ምሥጢር ቡሩክ፡፡ ኾኖም ጽላት ለቱሪስቶች(ለጉብኝት) ክፍት ኾኖ መታየት የሌለበት የሥርዓተ አምልኮ መፈጸሚያና  መግለጫ በመኾኑ፣ በዩኒቨርሲቲው ሙዝየም ውስጥ ቢቀመጥ ትርጉም እንደሌለው ስምምነት ላይ በመደረሱ፣ የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን በአደራ ተረክቦ እንዲያስቀምጥ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ታቦቱ፣ አልተረስቶን በሚል ስያሜ፣ በመዝገብ ቁጥር 1761 ተመዝግቦ የተገኘ ሲኾን፣ ሚስተር ስቴፈን ራይት በተባለ ሰው፣ እ.አ.አ ሰኔ 12 ቀን 1961 ወደ ሙዝየም መግባቱን መጋቤ ምሥጢር ይናገራሉ፡፡ ነገሥታት ታቦት አስቀርፀው በቤተ መንግሥታቸው በሚገኙ አብያተ ጸሎታት(ሥዕል ቤቶች) የማስቀመጥ ልምድ እንደነበራቸው የጠቀሱት መጋቤ ምሥጢር ቡሩክ፤ ምናልባትም ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ይህን የቅዱስ ሚካኤል ታቦት ሳያስቀርፁት እንዳልቀረ ግምት መኖሩን አመልክተዋል፡፡ “ታቦቱ በዩኒቨርሲቲው ሙዝየም 3ኛ ምድር ቤት ውስጥ ለብቻው በተሠራ ቤት ውስጥ ተደብቆ ነው የተገኘው፤ የሙዝየሙ ሠራተኞች እንኳን ታቦት መኖሩን አያውቁም ነበር፤” ብለዋል መጋቤ ምሥጢሩ፡፡
ከሰኔ 12 ቀን ጀምሮ፣ ከመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ጋር ይገናኙ እንደነበር የገለጹት ባለራእዩ ባሕታዊ በለጠ ዘነበ፣ በተደጋጋሚ ወደ ፓትርያርኩ ጽ/ቤት እየሔዱ ቢናገሩም ትኩረት አለማግኘታቸውን ጠቅሰው፣ በኋላ የቤተ ክርስቲያኒቱ የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽንና የቤተ መዛግብትና ቅርስ ክፍል ሓላፊዎች ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት ታቦቱን ከዩኒቨርስቲው ለመረከብ መቻሉን ለአዲስ አድማስ አስረድተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ምሁር የኾኑትን ፕ/ር አሕመድ ዘካርያን ስለ ጉዳዩ ጠይቀናቸው ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይኾኑ ቀርተዋል – “አኹን ብዙም የምገልጸው ነገር የለም፤” በማለት፡፡
the-imperial-genete-leul-palace-and-menbere-leul-st-mark-church
የቀድሞው ገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት(የአኹኑ የአ.አ.ዩ. የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም – በግራ) 
እና የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን(በቀኝ)
በዩኒቨርሲቲው ሙዝየም የተገኘውን የቅዱስ ሚካኤል ታቦት አስመልክቶ፣ ለብዙኃን መገናኛ እና ለሕዝብ ይፋ ለማድረግ፣ ለጥር 8 ቀን 2009 ዓ.ም. መርሐ ግብር መያዙን መጋቤ ምሥጢር ቡሩክ አስታውቀዋል፡፡
አኹን በ6 ኪሎ የሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ፣ የግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት የነበረ ሲኾን፣ ታቦቱን በአደራ የተረከበው የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንም፣ የንጉሠ ነገሥቱና ቤተሰቦቻቸው ሥዕል ቤት(ጸሎት ቤት) ኾኖ ያገለገለ ነው፡፡ የ1953 ዓ.ም. መፈንቅለ መንግሥት ተከትሎ የንጉሡ ቤተ መንግሥት ወደ ኢዮቤልዩ በመዛወሩ፣ የገነተ ልዑል ቤተ መንግሥትን ለትምህርት ተቋምነት በስጦታ አበርክተዋል፤ ጸሎት ቤት የነበረው የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንም ለሕዝብ አገልግሎት የሚሰጥ ኾኗል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ: ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረ ታቦተ ቅዱስ ሚካኤል ተገኘ

የቅዱስ ገብርኤል ጽላት በአንድ አባት ራእይ ተገኘ