Tuesday, September 3, 2013

በገላን ጉራ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የተከሰተ ድንቅ ተአምር

//መስቀሉ ለህዝብ በይፋ የሚታይበት ግዜ ላልተወሰነ ግዜ ተላለፍዋል:: //

ከሰማይ ወረደ ስለ ተባለው መስቀል ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ የተገኝኘው መረጃ
 በአቃቂ ቃሊቲ በቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ፣ ነሐሴ ፳፫ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም በቀስተ ደመና፣ በመብረቅ እና በነጎድጓድ ታጅቦ ከሰማይ እንደወረደ የተነገረው መስቀል፣ በጳጳሳት የተጎበኘ ሲኾን፣ ከሁለት ሳምንት በኋላ ለሕዝብ እይታ እንደሚቀርብ ተገለጸ፡፡
መስቀሉን ከወረደበት ለማንሣት የሞከረ ወጣት ተስፈንጥሮ ከወደቀበት ለአራት ቀን ራሱን እንደሳተ የሚናገሩ የቤተ ክርስቲያኑ አገልጋይ፣ ከምሽቱ 9፡00 ከፍንዳታ ጋራ አካባቢው በብርሃን ተሞልቶ ስናይ የእሳት ቃጠሎ መስሎን ነበር ብለዋል፡፡ እያንጸባረቀ በኃይለኛ ግለት ያቃጥል ነበር የተባለው መስቀሉ፣ በጳጳሳት እና በማኅበረ ቅዱሳን መሪዎች የተጎበኘ ሲኾን የኢየሱስን ስቅለት የሚያሳይ ወርቃማ ቅርጽ ያለው ነው፡፡
ወደ አቃቂ ከተማ ከሚያስገባው ዋናው የአስፋልት መንገድ በስተግራ በ10 ኪሎ ሜትር ርቀት ገላን ጉራ በሚባለው ስፍራ የዛሬ አምስት ዓመት የተቋቋመው የቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነሐሴ ፳፫ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም [የቅድስት] ክርስቶስ ሠምራ ክብረ በዓል እየተከናወነ ሳለ ከሌሊቱ 9፡00 የኾነው ክሥተት ነው የዚህ ሁሉ መነሻ፡፡ ከባድ የፍንዳታ ድምፅ የሰሙና የቀስተ ደመና ቀለማትን የተላበሰ ብርሃን የተመለከቱ ነገሩን ከዝናባማው የአየሩ ኹኔታ ጋራ በማያያዝ ብዙም ትኩረት አልሰጡትም ነበር የሚሉት የደብሩ መጋቢ፣ ‹‹በነጎድጓድና በኢትዮጵያ ባንዴራ የታጀበ መስቀል ከሰማይ ሲወርድ አይቻለኹ፤›› ብለዋል፡፡ ከዚያን ጊዜ ወዲህ መስቀሉን ለማየት ወደ ቤተ ክርስቲያኑ የሚጎርፉ ምእመናን በርክተዋል፡፡
ባለፈው ኀሙስ ከአቃቂ ከተማ በማለዳ ተነሥተን ከሁለት ሰዓታት የእግር ጉዞ በኋላ ከቤተ ክርስቲያኑ ስንደርስ፣ ጥቂት ምእመናን በተገኙበት የዕለቱ ቅዳሴ እየተከናወነ ነበር፡፡ ከቆይታ በኋላ ቅጽሩ የመስቀሉን ታሪክ ሰምተው ከአቅጣጫው በሚመጡ ምእመናን ተሞላ፡፡ ‹‹መስቀሉ ከሰማይ ሲወርድ አይቻለኹ›› የሚሉት መጋቤ ሐዲስ ፍሥሓ፣ ስለ መስቀሉ አወራረድ ገለጻ ማድረግ የጀመሩት ከጸሎተ ቅዳሴው ፍጻሜ በኋላ ነው፡፡
በቅጽሩ ከሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ አጠገብ መስቀሉ ወርዶ ያረፈበትን ስፍራ እያመለከቱ ይናገራሉ፡- ቦታው በቆርቆሮ ታጥሮ ድንኳን ተተክሎበታል፡፡ መስቀሉ ዐርፎበታል ከተባለው ስፍራ ‹‹አፈር›› እየተቆነጠረ የሚቀርብላቸው ምእመናን፣ ‹‹አፈሩን›› እየተመለከቱ የመጋቤ ሐዲስን ገለጻ ያዳምጣሉ፡፡
ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዓል ነሐሴ ፳፫ ቀን የጸሎት ሥርዐት ከምሽቱ 5፡00 አካባቢ እንደተጀመረ የሚያስታውሱት መጋቤ ሐዲስ፣ ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ አካባቢው በቀስተ ደመና ብርሃን ደምቆ እንደነበር ይናገራሉ፡፡ ‹‹የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮችና ምእመናን ለዚህ ልዩ ክሥተት ብዙም ትኩረት አልሰጡትም ነበር፡፡ ከዝናባማው የአየር ጠባይ ጋራ አዛምደው አቅለለው ነው የተመለከቱት፤›› ብለዋል መጋቤ ሐዲስ ፍሥሓ፡፡ የቀስተ ደመናው ብርሃን አንዴ ሲደምቅ፣ አንዴ ሲደበዝዝ መቆየቱን መጋቤ ሐዲስ ጠቅሰው፣ ‹‹ከሌሊቱ 9፡00 ሰዓት ነፋስ ለማግኘት በካህናት መውጫ በር በኩል ስወጣ ግን ደብዛዛ የነበረው ብርሃን የበለጠ ደምቆ እንደ ቀን ብርሃን ወገግ ብሎ ታየኝ፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹አሻቅቤ ስመለከት ሰማዩ በነጭ ደመና ተከቦ ተመለከትኩ፡፡ አፍታም አልቆየ፣ በኢትዮጵያ ባንዴራ ቀለማት የተጠቀለለ አንዳች ነገር በዝግታ ከሰማይ እየተገለባበጠ ሲወርድ አየኹ፡፡››
ከቤተ ክርስቲያኑ ቤተ ልሔም አጠገብ ያለውን የአገር አቋራጭ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ መሥመር ተሸካሚ ማማ እያመለከቱ፣ ‹‹ከሰማይ እየተጠቀለለ የሚወርደው ነገር ከማማው አካባቢ ሲደርስ ነጎድጎዳማ ድምፅ ማሰማት ጀመረ›› የሚሉት መጋቤ ሐዲስ፣ ‹‹መሬት ላይ ሲያርፍ በከፍተኛ የፍንዳታ ድምፅ አካባቢው የእሳት ንዳድ የመሰለ ብርሃን ሞላው፤›› ይላሉ፡፡ ‹‹ቤተ ልሔሙ ተቃጠለ እያልኹ ብጮኽም ድምፄን የሰማ ሰው አልነበረም፤ ለደቂቃዎች ያህል ለሰዎች እንዳይሰማ ኾኖ ታፍኖ ነበር፡፡ ድምፄ መሰማት ሲችል ግን፣ ካህናቱ ጩኸቱን ሰምተው ተደናግጠው ወደ ውጭ ወጡ፤›› ብለዋል፡፡ አንዳች አደጋ ደርሶ እሳት ተቀጣጥሎ ሊኾን ይችላል በሚል ድንጋጤ ሁሉም እሳቱን ለማጥፋት እንደተሯሯጠ ጠቅሰው፣ ነገር ግን ከአካባቢው ብርሃን በቀር የእሳት ቃጠሎ ማግኘት አልተቻለም ብለዋል፡፡
‹‹አንድ የቤተ ክርስቲያናችን ወጣት አገልጋይ ወደ ደመቀው ብርሃን ተጠግቶ ለማየት ሞከረ፤ አንዳች ነገር ወደላይ አስፈንጥሮ መሬት ላይ ጣለው፤ ምእመናን ተደናገጡ፤ የኤሌክትሪክ መሥመር ተበጥሶ ኮንታክት ፈጥሮ ይኾናል የሚል ጥርጣሬ ነበር ያደረብን›› ሲሉም ተርከዋል፡፡ ‹‹የወደቀው ወጣት ምላሱ ተጎልጉሎ በወደቀበት ራሱን ስቶ ተዘርግቶ ነበር›› የሚሉት መጋቤ ሐዲስ ፍሥሓ፣ ከወደቀበት በጥንቃቄ አንሥተን ጠበልና ቅብዐ ቅዱስ ብናደርግበትም አልተሻለውም ብለዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ነው ካህናቱ እንደምንም ወደ ብርሃኑ ተጠግተው የተመለከቱት፡፡ እናም በብርሃን የታጀበ መስቀል መሬት ላይ ዐርፎ አዩ ብለዋል፡፡
ካህናቱና ምእመናኑ በአግራሞት ሲመለከቱ ቢቆዩም የእሳቱ ወላፈን ይፋጃል ያሉት መጋቤ ሐዲስ ፍሥሓ፣ በርቀት መጎናጸፊያ ተወርውሮበት እንዲለብስ እንደተደረገ ይገልጻሉ፡፡ የተቋረጠው ሥርዐተ ማሕሌት ከ10፡00 በኋላ የቀጠለ ሲኾን በካህናቱ ትእዛዝ መስቀሉ ወርዶ ካረፈበት ሥፍራ ላይ ማለዳ 12፡30 ድንኳን ተተከለ፤ ብፁዓን አባቶችም በስልክ እንዲያውቁ ተደረገ ብለዋል፡፡ ይኹን እንጂ በማግስቱ የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ክብረ በዓል ስለነበር ብዙዎቹ ጳጳሳት ወደ ደብረ ሊባኖስ፣ ቀሪዎቹም ወደ የአድባራቱ ሄደው ስለነበር በዕለቱ መምጣት አልቻሉም ብለዋል፡፡
‹‹ከበላይ አካላት በተነገረን መሠረት ለወረዳው ፖሊስ ካሳወቅን በኋላ የፖሊስ ኃይል አካባቢውን ተቆጣጠረ፤›› የሚሉት መጋቤ ሐዲስ ቅዳሜ ዕለት የማኅበረ ቅዱሳን አባላት መጥተው መመልከታቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚያው ዕለት ከሰዓት በኋላ ለመምጣት ቀጠሮ የሰጡ ጳጳሳት ግን ከአንድ ሰዓት በላይ በረዶ የቀላቀለ ዝናም በመጣሉና ጭቃው የማያስገባ በመኾኑ ከመንገድ ተመልሰዋል፡፡ በማግሥቱ እሑድም አክራሪነትን ለመቃወም ሰልፍ የሚካሄድበት ቀን በመኾኑ መምጣት አልቻሉም፡፡
ሰኞ ዕለት፣ ነሐሴ ፳፯ ቀን በርካታ ጳጳሳት በቦታው ተገኝተው፣ መስቀሉ ዐርፎ ከቆየበት ስፍራ ተነሥቶና በበርካታ ምእመናን ታጅቦ ወደ መቅደስ እንዲገባ መደረጉን መጋቤ ሐዲስ ፍሥሓ ተናግረዋል፡፡ በደረሰበት አደጋ ራሱን ስቶ የቆየው አገልጋይ፣ በአራተኛው ቀን መንቃቱንና በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ተነግሯል፡፡ ወጣቱ ሲጠየቅም፡- ሊያነሣው እጁን ሲሰነዝር ከኋላው አንዳች ሕፃን ልጅ የመሰለ ነገር ጎትቶ መሬት ላይ እንደጣለውና ከዚያ በኋላ የኾነውን እንደማያውቅ መግለጹን መጋቤ ሐዲስ ተናግረዋል፡፡
መስቀሉ ከወደቀበት መሬት ተነሥቶ ሲገባ ከፍተኛ ግለት እንደነበረውና [ያከበሩት] አባት ‹‹እያቃጠለኝ ነው›› እያሉ ሲናገሩ እንደነበር ተገልጧል፡፡ መስቀሉ የሰው ሥራ እንዳይኾን የተጠራጠሩ መኖራቸውን የጠቀሱት መጋቤ ሐዲስ ፍሥሓ፣ ‹‹መስቀሉ ከምን እንደመጣ የሚያውቀው ፈጣሪ ነው፤›› ብለዋል፡፡
አቶ እንግዳው የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ፣ መስቀሉ ከሰማይ ሲወርድ እንዳልተመለከቱ ጠቅሰው፣ ‹‹በጳጳሳቱ ካረፈበት ተነሥቶ ወደ መቅደስ ሲገባ ወርቃማ ብርሃን ነበረው›› ብለዋል፡፡ አንዳንድ የአካባቢው ሰዎችም ሌሊቱን ነጎድጓዳማ ድምፅ መስማታቸውንና በማግሥቱም ስለ ክሥተቱ ከቤተ ክርስቲያኑ ካህናት እንደተነገራቸው ገልጸዋል፡፡ ለአካባቢው ጸጥታ በማሰብ መስቀሉ በየዕለቱ ለምእመናን እንዳይታይ ከቤተ ክህነት ትእዛዝ እንደተላለፈ ጠቅሰው፣ መስከረም ፲፱ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም በቤተ ክርስቲያኑ ቅጽር መስቀሉን ለእይታ ለማወጣት ቀጠሮ መያዙን መጋቤ ሐዲስ አስታውቀዋል፡፡
ጉዞ ተአምሩን ለማየት  

መስቀሉ ያለበት ቦታ






በማሕበራዊ ግጽ ላይ ከቤተክርስቲያን ልጆች የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው ከሰማይ የወረደ መስቀል በቤተ ክርስቲያን መገኘቱን የሚያስረዳ ነው:: ይህም ታማኝ ከሆኑ ሰዎች የተነገረ ስለሆነ እናካፍላችሁ:: ወደፊት ዝርዝር መረጃውን የምናቀርብ ሲሆን ተአምሩን እንዳቀረቡት ይህን ይመስላል::

እነሆ 23/12/2005 . ሀሙስ ለአርብ አጥቢያ ከለሊቱ 900 ሰዓት አከባቢ ካህናት አባቶች እና ምእመናን የክርስቶስ ሳምራን የበአል ዋዜማ ማህሌት ቆመው ሳሉ ድንገተኛ ድምፅ ሲሰሙ ካህናትና የቤተክርስቲያን አስተዳደሩ ከቤተመቅደስ ወጥተው ሁኔታውን ሲመለከቱት ብርሀን ከሰማይ እንደወረደና አከባቢውን በብርሀን እንደሞላው ተመልክተው ሲያዩ የጌታ ስቅለት ያለበት መስቀል ከሰማይ እንደወረደ ተረዱ መስቀሉም በብርሃን ተሞልቶ ነበር እነሱም በመደናገጥ ከቦታው ለጊዜው እራቅ ብለው በመቆም ምህላ አደረሱ::

በቦታው የደረሱ አባት ብርሐኑ ካለፈ በሁዋላ በሞባይል ያነሱት ምስል 


ተአምሩን አሁንም በቦታው ላይ በመገኘት መመልከት ይችላሉ፡፡

አድራሻው ከአቦ ቤተክርስቲያን ወደ ቦሌ ቡልቡላ በሚወስደው መንገድ ዋሻ ተክለሀይማኖትን ካለፉ በኋላ በድልድዩ ላይ ቀጥ ብለው በመውጣት ያገኙታልአድራሻው ከአቦ ቤተክርስቲያን ወደ ቦሌ ቡልቡላ በሚወስደው መንገድ ዋሻ ተክለሀይማኖትን ካለፉ በኋላ በድልድዩ ላይ ቀጥ ብለው በመውጣት ያገኙታል::

ከሰማይ የወረደው ተአምረኛው መስቀል በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ አማካይነት በቀን 27/12/2005 . ተነስቶ ወደ መቅደሱ ገባ፡፡ ተዓምሩን እያሳየ ያለው ይህ መስቀል የገባበት አድራሻውም አቃቂ ቃሊቲ /ከተማ ወረዳ 10 ገላን ጉራ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሲሆን፡፡ ብፁዕ አቡነ እስጢፋስ መስቀሉን ወደ ቤተመቅደስ እንዳስገቡት መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ 

ባሕታዊ ሕጻነ ማርያም መስቀሉ ይዘውት ሑደት ሲያደርግ

ዝርዝር መረጃው ባይደርሰንም ይህን ተዓምር ያሳየን የቅዱሳን አምላክ ስሙ የተመሰገነ ይሁን፡፡ ‹‹ወወሀብኮሙ ትዕምርተ ለእለ ይፈርሑከ፤ ለሚፈሩሕና ለሚያከብሩህ ምልክትን ሰጠሀቸው›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት ከተሰጡን ምልክቶች አንዱ ቅዱስ መስቀል ነው፡፡ በዚህ ምልክትም ከጠላት ሰይጣን እጅ ልናመልጠበት አርማችንም ልናደርገው ማዕተባችንንም አጥብቀን ልናስር ይገባል፡፡ ይህንም እናደርግ ዘንድ የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይርዳን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

የሸንኮራ ቅዱስ ዮሃንስ ወልደ ነጎድጓድ ጸበል ታምር 

ተአምራት በ በአታ ለማርያም ታህሳስ 3/05

 


Thursday, August 15, 2013

መምህር ግርማ ወንድሙ ከ ለይፍ መጽሄት ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

ላይፍ፡- ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን የጥምቀትና የትምህርት አገልግሎት እንዳይሰጡ የታገዱበት ምክንያት ምንድነው?
መምህር ግርማ፡- ምክንያቱም ሰው በመዳኑ እና የዲያቢሎስ ሚስጥር በመጋለጡ እንዲሁም ህብረተሰቡ ለከፋ መንፈስ ግንዛቤው እየጨመረ መምጣቱ ነው፡፡ የሆነው ሆኖ እኔ እየሩሳሌም አገልግሎት ሄጄ እያለ የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ መልክአ ኃይል አባ ሚካኤል የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ነን በሚሉ ግለሰቦች አማካኝነት ቤተክርስቲያኑ ውስጥ ብዙ ወጪ ወጥቶበት ተገንብቶ የነበረውን መድረክ እና የምዕመና መቀመጫዎች በመንቀልና በመሰባበር ከጥቅም ውጪ አደረጉት፡፡ እነኚህ ሰዎች ያልተረዱት ቢረዱትም ግድ የማይሰጣቸው ያወደሙት ንብረት የእኔ ሳይሆን የእስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን መሆኑ ነበር ፤ በቤተክርስቲያን ዙሪያ በሰንበት ትምህር ቤት ብዙ ችግሮች ይሰማሉ፡፡ እነኚህ የሰንበት ትምህር ቤትን ምግባርና ስርዓት ሳይኖራው በስም ብቻ የተጠለሉ አንዳንዶቹ እንደ ክርስቲያን ሳይሆን የእርኩሳን አሰራር የሚፈጽሙ እንደነበር ብዙዎች አገልጋዮች ያውቃሉ፡፡በተጨማሪም ማታ ማታ በድራፍትና በመጠጥ ዙሪያ ሲንካኩና ሲጨፍሩ አምሽተው ጠዋት መጥተው ከበሮ የሚደበድቡ ናቸው፡፡ ጸጉራቸው እንኳን ምስክር ነው፡፡ የተንጨባረሩ ፍጹም ቦዘኔና ዘላን መልክና ገጽታ ያላቸው ናቸው፡፡ ለአባቶቻቸው ክብር የሌላቸው፡፡ ማዋረድ ስራቸው የሆነ ፤ የስነ ምግባር መንፈሳዊ ትምህርትን ከምንም ቦታ ያልያዙ እንደዚሁ የመደዴነት ባህሪ ያላቸው ናቸው፡፡ በእነዚህ ነው የቤተክርስቲያኗ መድረክና ንብረት ያወደሙት፡፡ girma wendimu ላይፍ፡- ከዚህ በፊት በማን ጥሪ መሰረት ነው እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አገልግሎት ሲሰጡ የነበረው ? መምህር ግርማ፡-  በደብሩ አስተዳዳሪ መላከ ሰላም አማካኝነት ነበር፡፡ ከዚያ በፊት ቦሌ አቦ ፤ ኪዳነምህረት ፤ ፉሪ ሥላሴ ፤ ጭቁኑ ሚካኤል ፤መገናኛ እግዚአብሔር አብ በጠቅላላው በከተማይቱና ወጣ ባሉ ያሉ ደብሮች አገልግያለሁ፡፡
ላይፍ፡- ለስንት ዓመት አገልግሎት ሰጥተዋል? መምህር ግርማ፡-ከ1993 ዓ.ም ጀምሮ እዚህ አዲስ አበባ ያልተቋረጠ አገልግሎት ሰጥቻለሁ፡፡
ላይፍ፡- በእነዚህ አገልግሎት ዘመናት ለቤተክርስቲያን ምን አስተዋጽ አበርክተዋል ? መምህር ግርማ፡-  በእስጢፋኖስ ደብር ጣሪያው ውሃ ያስገባበት ወቅት 3 ሚሊየን ብር ገቢ አሰባስቤ አድሳት አድጌአለሁ፡፡
ላይፍ፡- ለምን ያህል ህሙማን ከህመማቸው የመፈወስ እና ትምህርት አገልግሎት ሰጥተዋል..? መምህር ግርማ፡- ለ4 ሚሊየን ሰው የፈውስ አገልግሎት ሰጥቻለሁ፡፡
ላይፍ፡- በተለይ በምን አይነት ህመም ሲሰቃዩ የነበሩ ሰዎችን አድነዋል ? መምህር ግርማ፡-  አይናቸው የጠፋ ፤ ሰውታቸው አልታዘዝ ብሎ አልጋ ላይ ውለው የነበሩ ፤ እጅና እግራቸው ሽባ የነበሩ ሰዎችን ፈውሻለሁ፡፡
ላይፍ፡- ሁላችሁም የእግዚአብሔር ቃል  የእመቤታንን በረከት የምታስተምሩበት ቤተክርስቲያን ለምን እንዲህ አይነት መከፋፈል መጣ ብለው ያስባሉ ? መምህር ግርማ፡-  በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ እንክርዳድ በስንዴው መሀል እንደሚዘራው ሁሉ ያም በቤተክርስቲያን ውስጥ አለ፡፡ ገበሬው መልካም ስንዴን ዘራ የሚለው ከውጭ አይደለም፡፡ ዘሩ እዚያው ቤተክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ በቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ህይወትና በልቦና ውስጥ መጀመርና በስጋ ህይወት መጀመር ልዩነት አለው፡፡ አምኖ መጀመርና ሳያምኑ መጀመር የእዚያን ያህል ነው፡፡ ሰሞኑን ወደ ቤተክርስቲያን ገብተው የሚኖሩ በጣም ብዙ ናቸው፡፡ እነዚህ ከተለያዩ የአስማት ስራ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ሲጠጉ ብዙ መልካም ነገር አይጠበቅባቸውምና ይህንን የሚመለከት ‹‹በማለዳ መያዝ›› የሚለው መጽሀፌ ላይ ሰፋ ባለ መልኩ አስቀምጬዋለሁ፡፡ ንጹህ የአምልኮት ፍላጎትና እንዲሁ ደግሞ በደብዛዛው በሚመላለሱ ሰዎች መካከል ዲያቦሎስ በደንብ ይሰራል፡፡ በተለይ ኦርቶዶክስ እምነት ላይ ሰይጣን ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል፡፡ ከታሪክ እውነታም አንጻር እነዚህ ሰዎች ህይወት ውስጥ የተለየ እድል አለ፡፡ ገብቶ ይቀመጥና በጎው መጥላት መልካሙን እንደክፉ ማየት ማሳደድ ያለው መናፍቆች ላይ ሳይሆን እኛ ጋር ነው ያለው፡፡ ይህ ደግሞ የሃይማኖቱ አንዱ በረከት ነው፡፡ ለምን ፈሪሳውያንን ክርስቶስ በመጣ ጊዜ እምነቱን ተራ ወግና ተራ የሆነ የይስሙላ አድርገውት ነበር፡፡ ያ ሂደት ደግሞ እንደዚሁ በቆየን ቁጥር የአዲስ ኪዳንንም ህይወት እንደዚያ ነው የሚሆነው፡፡ ወደ ፈሪሳውያን ጠላት ይሄዳል፡፡ በዚህ ጊዜ እውነቱ እየጠፋ በቤተክርስቲያን ውስጥ  ጣልቃ ይገባሉና ያንን ለመለየት የመንፈስ ቅዱስ ስራም የአጋንንት የቅንነትም ስራ ስለሚያስፈልግ ዛሬ ያ ቅንነቱ እና በጎነቱ በክፋት በተንኮል በምቀኝነት የተሞላ ስለሆነ ያ ሂደት ሊያደርገን አልቻለም፡፡
ላይፍ፡- ብዙ ሰባኪያን ወደ እርስዎ ፕሮግራም የማይመጡት ለምንድነው? መምህር ግርማ፡-  ይህንን የፈውስ ሂደት ስላለመዱት ልክ እንደ መተት እንደ ጠንቋይ አሰራር አድርገው እስከዛሬ ድረስ ሲያወሩ እንደቆዩ ያው የተለመደ ነገር ነው፡፡ስላልተለመደ እንግዳ ነገር ነው የሆነው፡፡ በተለይ በግለሰብ ጸጋ አልተለመደም፡፡ ይህንን ያልተለመደ ነገር እንዲህ ሲወጣ ሁሉም እየተረባረበ ማጨለም ነው የሚፈልገው፡፡ የእግዚአብሔር ስራ ደግሞ ስለማይጨልም ሂደቱን ጠብቆ ይበራል፡፡ ከዚህም በፊትም የተደረጉብኝ ዘመቻዎች ብዙ ናቸው ይህ ብቻ አይደለም፡፡ ይህ እንዲያውም የመጨረሻው ደካማ ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ሰዎች መንፈሳዊ አንድነታቸው በክፉ ሰዎች መንፈስ ተመቷል፡፡ በራስ እይታም ተመቷል፡፡ የምቀኝነት መንፈስ አጠናክረው በመያዛቸው ምክንያት የእግዚአብሔር ጸጋ በረከት መለያ መንፈስ አጥተዋል፡፡ አንድነትና ተስማምቶ መዝለቅን በዚህ ዘመን ውስጥ የምንጠብቀው ጉዳይ አይደለም፡፡ ግን እውነት ዞሮ ዞሮ ደረጃዋን ጠብቃ ስለምትወጣ ያን ያህል አስጊ አይደለም ማለቴ ነው፡፡
ላይፍ፡- ከአስተዳዳሪው ጋር የነበራችሁ አለመግባባት ከየት የመጣ ነው? መምህር ግርማ፡-   አስተዳዳሪው መልአከ ኃይል አባ ሚካኤል በአንድ ላይ ቁጭ ብለን በተካፈልንበት ጉባኤ ላይ ሁለት ክፍል ያለው ኮንዶሚኒየም ገዝቼ እንድሰጣቸው ጥያቄ አቅርበውልኛል፡፡
ላይፍ፡-ለቤተክርስቲያን የሚገባውን ሙዳይ ምጽዋት ይካፈላሉ ? መምህር ግርማ፡-  ኧረ በጭራሽ ምጽዋቱ ለቤተክርስቲያን ነው የሚሆነው፡፡
ላይፍ ፡- ታዲያ ከየትኛው ገቢዎ ላይ ነው አስተዳዳሪው ኮንዶሚኒየም ገዝተው እንዲሰጧቸው የጠየቁዎት ? መምህር ግርማ፡-እንዲያው ለትራንስፖርት ፤ ለምንም ወይም ሲዲ ወይም መቁጠሪያ የምሸጠው አለ፡፡ ከእሱ እንደምንም አቻችልና ግዛልኝ ፡፡ አለበለዚያ ደግሞ ሕዝቡን አስተባብረህ የበረከቱ ነገር ወደ እኔ አዙረው ነው ያሉት ሰውየው፡፡
ላይፍ፡- እኛ ከዚህ በፊት ስለዚህ ኮንዶሚኒየም ግዙልኝ ብለው ጠይቀው እንደሆነ ጠይቀናቸው በጭራሽ አልጠየኩም በማለት መልስ ሰጥተው ነበር ? መምህር ግርማ፡- እውነት በቃል ማስተባበር ይቻል ይሆን ?  ከህሊና እና ከእግዚአብሔር መሰወር ግን እንዴት ይቻላል ?
ላይፍ፡- ታዲያ ምን ምላሽ ሰጠዋቸው ? መምህር ግርማ፡-በወቅቱ ያንን ማድረግ አቅሙ ስለሌለኝ ጥያቄያቸውን እንደማልቀበል ገልጬላቸዋለሁ፡፡
ላይፍ፡- ምላሽዎ በግሳጼ ወይስ ሌላ ገጽታ ነበረው…? መምህር ግርማ፡-  በግሳጼ መልኩ አልመለስኩም፡፡ ለምን ያው የሕዝቡ ችግር ስለማውቅ ሁኔታዎችን ስጠብቅ በራሱ ጊዜ ገነፈለና የሰውየው ኃይል ወጣ፡፡ እኔ መገሰጽ አልፈለኩም፡፡ ምክንያቱም ችግሩን አውቃለሁ፡፡ እንዲህ የተወሳሰበ የሙስና አሰራሮች ከመጀመሪያው ጀምሮ በየደረጃው ስር ሰደዱ ናቸው፡፡ በአንድ ዘመን ሳይሆን እየተንከባለሉ የመጡ ችግሮች ናቸው፡፡ ሰውየው ወደ ማዕረጉ እና ወደ አስተዳደሩ ሲመጡ 60 ሺህ ብር ከፍለው ነው ለዚህ የበቃሁት ይላሉ ፤ ያንን በተለያዩ መንገዶች ማቻቻል አለብኝ ማለት ነው፡፡
ላይፍ፡- የኮንዶሚኒየም ግዢ ይህን ያል ያወጣል ብለው ግምቱን ነግርዎት ነበር ? መምህር ግርማ፡-  በቃ ሁለት ክፍል ያለው ኮንዶሚኒም ነው ይገዛልኝ ያሉት ፡፡ ግምቱንም ያውቁታል፡፡
ላይፍ፡-  እርስዎ አለኝ የሚሉት የፈውስ ጸጋ ከየት የመጣ ነው ይላሉ ? መምህር ግርማ፡- ይህ እኮ አንድና ሁለት  ነው እንደሚባለው አይነት ፎርሙላ ወጥ አድርገህ የምታሳየው ነገር አይደለም፡፡ ይህ በጸሎት በስግደት በቅዱስ ቁርባን በመመጽወት ከሰማይ የሚለቀቁት እንጂ ከማንኛውም ሰው የምትገዛው ወይም የምትለውጠው ትርፍ ያለው ነገር አይደለም፡፡ ይህ ከሰማይ የሚሰጥ እንጂ በስጋዊ ጥበብባ ዘዴ ወይም ምርምር ወደ ላብራቶሪ የሚመጣና የሚገኝ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሔር አሰራር ነው፡፡ የእግዚአብሔር አሰራር ደግሞ አለምም ሆነ ስጋውያን አያውቁትም፡፡ መንፈሳውያንም ተቸግረዋል፡፡ በዚህ ዘመን ያሉ የገዛ አባቶቼ እንኳን  ሳይቀሩ ይህንን መንፈሳዊ ጸጋ ለመቀበል በጣም ይቸገራሉ፡፡ ምክንያቱም ከእኛ በኩል ካፈሰሰ ነው እኮ አሁን ችግሩ፡፡ ከእኔ በኩል ካልፈሰሰ እንዴት በዚህ ዘመን ከእግዚአብሔር ይመጣል ፤ የሚል ዋጋ ቢስ እና ተስፋ አስቆራጭ የመንፈሳዊ ህይወት ጉዞን የለመዱት ባህሪ ለማንጸባረቅ ሲሞክሩ ነው አሁን ነገሮች ወደዚህ አይነት አጣብቂኝ ውስጥ የሚገቡት፡፡
ላይፍ፡- እርስዎ ተሰጥቶኛል የሚሉት የመንፈስ ጸጋ ስያሜ ሰጥተውታል ? መምህር ግርማ፡- እንደዚህ ያለ ነገር የለም እንጂ ምን ስሜ ይሰጠዋል ? ክፉ መናፍስን የሚቃወም የእግዚአብሔር መንፈስ ነው፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስና ክፉ መንፈስ ደግሞ አይገናኙም፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ስጦታ ደግሞ ክፉውን መለየት ፤ ክፉው ማስወገድ ነው፡፡ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ አጋንንትን አወጡ ይል የለም እንዴ? በአሁኑ ዘመን አጋንት አስገባ ቢባል ሁሉም ይወደኛል፡፡ አጋንንት ማስወጣት እኮ ነው የተለየ ጠንቋይ ያደረገኝ፡፡
ላይፍ፡-አለኝ የሚሉት የመንፈስ ጸጋ ወደ ሌላ ሰው ማስተላለፍ ይችላሉ ? ወይስ እርስዎ ጋር ነው ሊቀር የሚችለው ? መምህር ግርማ፡- የኤልያስ መንፈስ በኤልሳ እንዳደረ ሁሉ የፈለገው ሁሉ ያገኛል፡፡ እኔም የማስተምረው እኮ ክርስቲያኑ ራሱን ችሎ እንዲቆም ነው፡፡ ጠላቱን እንዲጋፈጥ ፤ ክፉ መንፈስ እንዲያሸንፍ ፤ የዲያቢሎስ ትውልድ መሆኑ እንዲቆም ፤ ከዚያም በላይ የመንፈስ ቅዱስ ስራ የእግዚአብሔር ክብርና ኃይል እየጨመረ እንዲመጣ ፤ የአለም ጥበብ ከእግዚአብሐየር መላዕክ አሰራር ጋር ክርስቲያኖች በረከት ውስጥ እንዲገቡ ነው፡፡፡ አሁን ለምሳሌ በአሜሪካ በስልክ የሚሸኝላቸው ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ በእጄ ማስረጃ አለኝ፡፡ በስልክ የሚሸኝላቸው ራዲዮ አቢሲኒያ ላይ ከቁትር 1 ጀምሮ እስከ 34 ድረስ ያለውን ትምህርት በመከታተል እየጸለዩ እየሰገዱ በመቁጠሪያ እየቀጠቀጡ መንፈሱን ያዳክሙታል፡፡ ከዚያ በኋላ መንፈሱ ራሱ እኔ አይ ጥላ ነኝ ፤ ቡዳ ነኝ ፤ አብሬ ነው የተወለድኩት እያለይነግራቸዋል፡፡ በመጨረሻ ከተዳከመ በኋላ አንዳዴ ራሱ ‹‹ሸኙኝ›› ብሎ ይደውላል፡፡ በእጄ የቀረጽኳቸው ከ200 በላይ በስልክ የሸኝሁላቸው ሰዎች አሉ፡፡ አሁን አባቶች ይህ ነገር ሲሰሙ ይደነግጣሉ፡፡ ምክንያም እንዴት በስልክ ሰይጣን ይወጣል  ብለው አንድ ወቅት ላይ አቅርበው ጠይቀውኛል፡፡ ስለዚህ ጸጋው የቤተክርስቲያን እንጂ የእኔ አይደለም፡፡ መቁጠሪያው የቤተክርስቲያን ነው፡፡ ውዳሴው የቤተክርስቲያን ነው፡፡ መላከ ትግሉ የቤተክርስቲያን ነው፡፡ ከዚህ ውጪ የእኔ የያዝኳቸው የምትሀት አሰራር የለም፡፡ ስለዚህም ሁሉም ህዝብ በውጭ አለም ያለው በተለይ ከክፉ መንፈስ ጋር ያለውን ፍልሚያ በሚገባ ስለተገነዘበ እያንዳንዱ ራሱ በመቁጠሪያ እየተጠቀመ የሸኝውም አለ፡፡
ላይፍ፡- አባቶች እርስዎ የሚሰጡት መንፈሳዊ ጉባኤ ተገኝተው በረከት ይሰጡ ነበር ወይ ? መምህር ግርማ፡- እኔ በማገለግለው ላለመገኝት ብዙዎች ይሸሻሉ ተሰልፈው ዝቅ ብለው የህዝብን ችግር ለማየት እስከ አሁን በጎ ህሊና አላገኝሁም፡፡ ሃገር እንደ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማው ኃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አይነቱ በተደጋጋሚ የህዝቡን ችግር ተረድተው በተደጋጋሚ ወደዚያ እየሄድኩ ሳገለግል መንፈሳዊ ድጋፋቸውን ለህዝቡ ካለው ችግር ለልማቱም ከማሰብ ቢርሌ የሰጡት ቦታና ስራ አለ፡፡
  ላይፍ፡- አባቶች እርስዎ የሚሰጡት መንፈሳዊ አገልግሎት አስተያየታቸው ምንድነው ? መምህር ግርማ፡- ብዙዎች ይህንን መንፈሳዊ ድርሻ ለመወጣት በማደርጋቸው ጥረቶች ላይ በጎ ድጋፍ የላቸውም፡፡ ከተለያዩ አይነት መንገድ ለመዳንም ይሰጣሉ፡፡ ነገር ግን አንዳዶች እንዲያውም የሸናሻም መተት ይህን ያደርጋል፡፡ የሸናሻም አስማት ይህንን ይሰራል እያሉ ለአስት አሰራር ትልቅ ድጋፍና የሰይጣን አሰራር ትልቅ ሞራል ሲሰጡ ነው የሚሰማው፡፡
ላይፍ፡- ይህንን እርስዎ የሚያደርጉትን መንፈሳዊ አገልግሎት ሌሎች አባቶች ያምኑበታል ? መምህር ግርማ፡- እኔም በጣም ግራ የሚገባኝ ዲያቢሎስ የሚያደርገው ጥቃት በመጽሀፍ ቅዱስ በረጅሙ እና በስፋት ጥልቀት ባለው ሁኔታ ገልጿል፡፡ ሐዋርያት አጋንንትን እያወጡ የሰዎችን ደህንነት ሲያበለጽጉ ይታያል፡፡ በቤተክርስያንም እደዚሁ በመንፈሳዊ አገልግሎት በመንፈስ ቅዱስ ስራ እንደሚሰራ ይታወቃል፡፡ እንግዲህ ሰዎች በክፉ መንፈስ አሰራር  ወይም አያምኑም አልያም በእዚአብሔር አሰራር አያምኑም፡፡ በዚህ መንታ መንገድ ላይ መታየት አሁን አይቻልም፡፡ ምክንያም የእግዚአብሔር ሕዝብ በዲያቢሎስ ተጠቅቷል፡፡  ወይ ዲያቢሎስ እንዲበላ ማድረግ ነው አልያም በቤተክርስቲያን መንፈስና ጸጋ ህዝቡ ችግር ውስጥ ገብቶ ችግሩን ማየት ነው፡፡ ገለልተኛ ሆኖ መኖር አሁን አሁን ጊዜው አይደለም፡፡ ስለዚህ ያምናሉ አያምኑም የሚለው ነገር እርሳው እኔን ቢረዱኝ ደስ ባለኝ፡፡ በተሰጣቸው ጸጋ ክፉ መንፈስ ነው ካሉ የእኔን መንፈስ ማወጣት መቻል፡፡ ሁሉም ቢተባበሩኝ መልእክት አስላልፋለሁ ፡፡ እንዲያውም በቤተክርስቲያን ይኖር የነበረ አስማተኛ መንፈሱን አስወጣንለት ብለው ለአለም ዜና ቢያቀርቡ ደስ ባለኝ ነበር፡፡
ላይፍ፡- ቤተክርስቲያኗ ወታደርና ነጋዴ የቤተክርስቲያን አገልጋይ አይሆንም የሚል ሕገ ደንብ አላት፡፡ እርስዎ ግን መንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ከመግባትዎ በፊት ወታደር እንደነበሩና እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አገልግሎት መስጠት ከጀመሩ በኋላ 1.5 ሚሊየን የሚገመት ቤት ገዝተው እየኖሩ ነው ይባላል በዚህ ላይ ምን ይላሉ ? መምህር ግርማ፡-ዛሬ ሰማዕቱ ሀገር ጠባቂ የምንለው ቅዱስ ጊዮርጊስም የመቶ አለቃ ወታደር ነበር፡፡ ግብጽ ውስጥ ያሉ ብዙ ታላላቅ አባቶችም እንደዚያው ናቸው፡፡ በአሁንም ዘመን ያሉ ብዙ መነኮሳቱ እስከ ጳጳሳቱ ወታደር የነበሩ ናቸው፡፡  ወታደር ማለት የእግዚአብሔርን ስራ አይሰራም ማለት አይደለም ፡፡ እኔ ደግሞ ልቀድስ ላቁርብ አላላኩም ፤ በተሰጠኝ ጸጋ ላገልግል ነው  ያልኩት፡፡ ቤት ምናምን የሚሉት ቤቱን የገዛልኝ የተፈወሰ ሰው ነው፡፡ ቤቱን የገዛልኝ እግዚአብሔር በሰው በኩል ነው ፡፡ ቤቱን የገዙልኝ ሰው በተጨባጭ ከጎኔ አሉ፡፡ ይህንን እንደ አንድ እንደ ትልቅ ነገር ማንሳት በራሱ ምንን ያመለክታል ፤ ምቀኝነትን ነው ፤ ያው ከደማችን ውስጥ የተለመደ ምቀኝነት ስላለ እንጂ ከነዚህ ሁኔታዎች በሙሉ እንዳሰራ የሚያደርጉ አይደሉም፡፡
ላይፍ፡- እርስዎን አስማተኛ እና ጠንቋይ ናቸው የሚሉዎት ሰዎች ምላሽ ምንድነው ? መምህር ግርማ፡- እኔ አስማተኛ ከሆንኩ እኔ ጋር መጥተው አስማቱን ማውጣት ነው፡፡ እኔ ጋር መጥተው አስማቴ የት ጋር እንደተቀበረ ፈልገው ማውጣት ነው፡፡ ክንዴ ላይ ወይም እግሬ ላይ ወይም ጭንቅላቴ ላይ እንዳለ ደንበኛ ራጅ ይዘው መጥተው ፈልገው ማውጣት፡፡ ወይም መንፈስ ከሆነ ያስወጡልኝ፡፡ ቢረዱኝ እኮ ለእኔም ደስ ይለኛል፡፡ ግልግል ነበር፡፡ እስቲ አስማቴን ኑ እና አስወጡልኝ እባካችሁ ስለ እግዚአብሔር ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ብዬ እለምናችኋለሁ፡፡

Thursday, May 9, 2013

መላከ ሰላም ዘላለም እሰይ ስለ መምህር ግርማ ምን ይላሉ?

የቅዱስ እስጢፋኖስ አስተዳዳሬ አቶ ሚካኤል ታደሰ የሃሰት የምልኩስና ስሙ ኃይለ ኢየሱስ/ ከአርባምንጭ የተባረረበት ደብዳቤ





የመምህር ግርማ ወንድሙ እገዳ በተመለከተ የቀድሞው የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አስተዳዳሪ መላከ ሰላም ዘላለም እሰይ የሰጡት  አስተያየት እና ከ እገዳው ጀርባ ያሉ  እውነቶች




 የ እገዳ ደብዳቤውን ከቤተ ክርስቲያኑ ሰንበት ትምህርት ቤት የፌስ ቡክ ገጽ ይመልከቱ

Who is priest/Exorcist Memeher Girma Wondimu?


Wednesday, April 17, 2013

የሸንኮራ ቅዱስ ዮሃንስ ወልደ ነጎድጓድ ጸበል ታምር


Memihir Girma Miracles: Nequ part 14:The story of Fikrte Tibebu 

Memehir Girma' s message to the Ethiopian Orthodox Christian Diaspora - Part 6-7-8

  "እርሱም። ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ሕግና በነቢያት በመዝሙራትም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው አላቸው። በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤ " የሉቃስ ወንጌል ፥ ምዕራፍ 24 ቁጥር

Memihir Girma exposing protestants : Nequ(VCD) Part Three

 

Monday, April 2, 2012

Miracles of Legedadi Saint Mary Church

This miracle happened in Legedadi Saint Mary church. In a cave the arc of Saint Mary along with fossils of holy fathers are found. Usually, during celebration on 16 Feb,2004(EC) the arc is taken out of the cave. But on that particular day, the arc refused to return to the cave and saint Mary told the priests through the arc that she needs to be honored. The video tells you the rest of this amazing miracle. SEE the link below to read more about what happened.
More and Source: Dekik Nabute
Related Miracles
Collection of miracles of Saint Mary, Saint Gabriel
Saint Mary Miracles in Ethiopia
Saint Gebriel Miracles in Ethiopia
Add caption


Sunday, March 25, 2012

Memehir Girma´s Interview with Radio Abisinia



Memehir Girma has a strong message for the generation. He teaches ways to identify evil spirit possession, fight and remove the evil spirit.He bursts into tears each time he talks about the current divided reality of the Ethiopian Orthodox church. He gives detail instructions on how to set up a prayer room, start growing in spiritual life and fight the evil spirit. In this 3hr audio he teaches very essential and life changing real life based Christianity. He also gives his mobile number but with preconditions that MUST be fulfilled first by Ethiopians living abroad.This is nothing but to fight the spirit by yourself first before contacting him. How? He will give you detail instructions in this audio.


የኢንተርኔት አገልግሎት ፈጣን ባልሆነበት ቦታ በአማራጭነት ይህንን በጽሑፍ መልክ ያንብቡ:: ረጅም ትምሕርት ሲሆን በተቻለ መጠን በቂ መልክቱን በጽሑፍ አቅርበናል:: የቃላት ግድፈት ካለ እያረሙ እንዲያነቡ እንጋብዛለን::
የጸሎት ቦታ እንዴት ላዘጋጅ?

ክፉንና ደጉን ለመለየት አምልኮ ያስፈልጋል:: አምልኮ የሌለበት ህይወት አለም ላይ የወደቀ ነው ስለዚህም የአምልኮት ራእይ አንድ ክርስቲያን ሊኖረው ይገባል:: ማምለክ ማለት እግዚያብሔርን ከልብ መውደድ: ቃሉን በልቦና ማኖር: እና መጠበቅ: እርሱን ተስፋ ጉልበታችንን ማድረግ ነው:: በተግባር ደግሞ ኑሮን ጠባይን ለእግዚያብሔር መስጠት: ውስጣዊ ህይወታችንን ለክብሩ የተዘጋጀ ማድረግ :: ስለ ሐጢአታችን ንሰሐ ገብተን ሥጋውና ደሙን መውሰድ: እለት እለት ስለበደላችን ስለሐጢአታችን ለእግዚያብሔር መንገር:: እለት እለት እግዚያብሔርን የምናመሰግንበትን ግዜ ካገኘን የአምልኮት ሕይወት ገበና አለን ማለት ነው:: ሰብአ ሰገል ክርስቶስን በፍቅር ፈልገው እንደመጡ አንድ ክርስቲያንም ክርስቶስን ፈልጎ መምጣት አለበት:: በአምልኮት ባሕርይ ሔሮድስን ማለፍ ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ነው:: ሔሮድስ ማለት የዚህ አለም ነገሮች ናቸው እነዚህም :የአለምን ሰዎች እውቀት: ሳይንስ እግዚያብርሔን የሚከለክል : የድንግል ማርያም ልጅ ክርስቶስን የሚከለክል ነው:: ሔሮድስ ማለት ሐብት : ስልጣን: ማዕረግ የመሳሰሉት እነዚህ ሁሉ የሔሮድስ መንገድ ጠቋሚ ናቸው:: ሰዎች የጥፋት ሞት ውስጥ የሚገቡት የአምልኮት ሕይወት በማጣት ነው:: እግዚያብሔርን የሚፈልጉ ሰዎች ሔሮድስ ጋር መቅረት የለባቸውም:: ኮከቡን ማየት አለባቸው ኮከቡም ያለው በሰማይ ነው::

ብዙ ክርቲያኖች ወደ እግዚያብሔር ቤት አይሔዱም ወይም ወደ ሰማይ ቀና አይሉም:: በዚህም ወደ ልባቸው የሚሔድባቸው መጣባቸው:: ሰይጣን ወደ ቤታቸው ወደ ኑሮአቸው ወደ ሕይወታቸው መጣ:: በዚህ ዓለም ገለልተኛ ሆኖ መኖር አይቻልም:: በዚህ አለም ሁለት ነገር ነው ያለው:: ጽድቅና ኩነኔ: ጨለማና ብርሃን: ሓጢአትና ጽድቅ: ሰላምና ጦርነት::ከፈለክ ወደ ብርሃን ካልፈለክ ወደ ጨላማ: ከፈለክ  እውነት ካልፈለክ ሐሰት: እንዲህ በጥንድ የተያያዘ ነው:: የእግዚያብሔርን በቅድምያ ከሰማን የእግዚያብሔር ጽድቅ ይገለጥልናል: የሰዎችን ከሰማን ሁል ግዜ እንደተደናገግርን ተስፋችንን በአልሆነ አቅጣጫ እየጠበቅን እንኖራለን:: ሔሮድስ ክፉ መሆኑን የምናውቀው ስናመልክ ነው::

የጸሎት ቦታ
የጸሎት አቅጣጫ ምስራቅን የተመለከተ መሆን አለበት:: በመንበርከክ በግንባር ልክ የእመቤታችን የቅዱስ ሚካኤል የቅዱስ እና የቅዱስ ገብርኤል በግራና ቀኝ : በመቆም ልክ የስላሴ የመድኃኔአለም ስእል ይደረጋል:: ከስእሉ ራቅ የሚባለው ክፍተቱ የመጽሐፍ መግለጫ ያህል ነው:: ስእሎቹ ተጸልዮባቸው ቅባ ቅዱስ ይቀባሉ ቢቻል ቤተ ክርስቶያን ተባርካው በቅዳሴ ግዜ ቅባ ቅዱስ ተቀብተው መሆን አለበት:: ስእሎቹ በጥሩ ፍሬም የተሰሩ ስእሎች መሆን አለባቸው:: ከስራቸው የጸሎት ወሃ : እጣን: እምነት:የወይራ ዘይት: የመጽሀፍ ማስቀመጫ: የምንጠቀምባቸው እንደ ሽቶ ዎች ካሉ አጠገብ መሆን አለባቸው:: ሽቶ የሚወዱ ዛሮች አሉ:: ተጸልዮበት ሽቶ ብንጠቀም ሽቶ የሚወዱ ዛሮችን መከላከል ይቻላል : የመንበርከኪያ ቦታ ደረቅ ያለ የጥጥ ፍራሽ ቢሆን ይመረጣል:: ግልበት በሚሰግድበት ግዜ መመቻቸት አለበት ነገር ግን በጣም የሚመች ሥፕንጅ መሆን የለበትም: ስንፍና እንዳይሰማው: የሚሞቅ ነገር መሆን የለበትም መቀዝቀዝም የለበትም:: በሚሰግድበት ግዜ በስእሎቹ ፊትለፊት  መስገድ ሲጀምር የሚከተሉትን ምልክቶች ያያል:- መዛል:መድከም መልፈስፈስ :: በሚጸልይበት ግዜ ከስእሎቹ የሚወጣ መንፈሳዊ እሳት አለ:: በሰውነቱ ላይ ከስእሎቹ ተጠግቶ ሲጸልይ መውረር መቅበጥበጥ:ማቃጠል የሚታይበት ይሆናል:: አንዳንዱም መንፈሱ ወዲያው መገለጥ ጠባይ አለው:: መንፈሱ ጸሎት በከፍተኛ ሁኔታ ጸሎት እየከለክለው የሚያጠቃው ከሆነ የቅዱስ ሚካኤልን ስእል በፍሬም በጥሩ ሁኔታ ሰርቶ  መሬቱ ላይ አድርጎ እጁ ላይ እና ሰይፉ ላይ በሚሰግድበት ግዜ መንፈሱ ሊጥለው ይችላል:: በዚህ ግዜ መቁጠርያ ያስፈልጋል::ጸጥ በል በጌታየ በየሱስ ክርስቶስ ስም ብሎ ሲመታው ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እሰርልኝ ሲለው  በስእሉ ፊት ያለው ሐይል እየተገለጠ ቅዱስ ሚካኤል ሊያስርለት ይችላል:: ሰውየው እየሰማም እያወቀም መንፈሱን ሊያስርለት ይችላል:: በዚህ ግዜ ፕሮግራም ይዞ ወድ  እኔ ደውሎ አንዳንድ መረጃ እንለዋወጣለን:: የሚደክም ከሆነ ይደክማል የሚሸኝም ከሆነ ይሸኛል:: ሆኖም ግን  እነዚህን ልምምዶች በቀላሉ የሚመጡ  አደሉም:: ሰውየው በጥሩ የበረከት መንፈሳዊ ህይወት ለማለፍ እራሱን ማዘጋጀት አለበት:: ጸሎትን እንደ ደስታ አምላክን እንደማማረርያ ጎዳና ሳይሆን "ሁል ግዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ:ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ::ገርነታችሁ ለሰው ሁሉ ይታወቅ::" እንዲል ገራገር መሆን አለበት:: "ጌታ ቅርብ ነው::በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ::" ፊልጵስዮስ 4:4-6

ራእይን ምሪቱን ለማግኘት ደግሞ የጸሎት ቦታችን ላይ ለባልና ሚስት የመኝታ ያህል መኖር አለበት: ቤተሰብ ካለው ከሌለው መኝታውን እዚያ ያደርጋል: ልብሶቹ አንሶላዎቹ እዚያው መሆን አለባቸው:: የሚለብሰው ልብስ ላይ መስገድ አለበት ምክኒያቱም ብርድ ልብሱን ከሌላ መኝታ ቤት ሲያመጣ መንፈሱ ከብርድልብሱ ጋር ይመጣና ተንኮለኛው መንፈስ ራእዩን ይከለክለዋል:: እዚያው ከጸለየበት ከሰገደበት ግን መንፈሱን ያጠቃዋል:: የእግዚያብሔር የምስጋናው የጸሎቱ እሳት መንፈሱን ያቃጥለዋል:: ሊቋቋመው ስለማይችል ራእዩን አያጨልምበትም: ክፉና ደጉን የሚያውቅበት  ያገኛል:: የራእይን ተግባራዊነት ለመረዳት በመጽሐፍ ቅዱስ ኦሪት ዘፍጥረት  49 የሮቤልን ነገድ ታሪክ ያንብቡ:: ራእይን ለማግኘት በአምልኮት ስግደት ውስጥ ይቅርታን እንለምናለን : ምስጋና ለአብ ምስጋና ለወልድ ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስ የምንልበትን ህይወት ስንጀምር ምስጋና ለአለም: ለመጠጥ: ለመድሐኒት:ሃይል ለሚሰጥ መድኃኒት.....ማለቱን እናቋርጣለን:: ለእግዚያብሔር መለኮታዎ ስልጣን መገዛት ስንጀምር እርሱም ይወደናል:: መውደዱን ያውቅበታል "እናንተ ደካሞች" ያለኮ ጌታ ነው:: ድካማችንን ሁሉ ያውቃል::" እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ" ማቴ 11:28 ያለ አምላክ ገር ነው:: የገርነት ድምጾቹን በስጋ ተገልጦ አሳይቶናል መክሮናል ገስጾናል ወደ ቅዱሳን ሕይወት እንድመጣ ረድቷል:: በረከቱን በሁሉም ጎን ለመስጠት ሕይወታችንን ጎብኝቷል:: የራእዩ አይነት ይለያያል: የተባረከ ልጅ ማግኘት የሚፈልግ ከዚያ ጽሎት ቤት ውስጥ ለምኖ ያገኛል:: በቤት ውስጥ መጸልይ ከቤተ ክርስቲያን በተጨማሪ ብዙ ጥቅም አለው:: "ኢያሱም ሕዝቡን፦ ነገ እግዚአብሔር በመካከላችሁ ድንቅ ነገር ያደርጋልና ተቀደሱ አለ። " መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 3:5 ቤተ ክርስቲያን መቀደሻ ናት: ቤት ደግሞ መባረኪያ እና ማምለኪያ ነው:: ይህ መገናኘት አለበት:: እቤትህ ሳታመልከው ቤተ ክርስቲያን አመልካለሁ ማለት እና እቤት አለመጸለይ ክርስቲያናዊ ህይወትን ጎዶሎ ማድረግ ነው:: እቤታችን ሰርቀን ነው የተኛነው:: የጸሎት ቦታ ከሌለ ሰውየውም ሌባ እንጀራውን ቤቱም ሌባ ከሆነ በዛ መኝታ የተጸነሰው ትውልድ ተስፋ የሌለው ጤናው የተጓደለ አገር አጥፊ ተስፋው የተቋረጠ...ቢሆን ምን የሚያሳዝን ነገር አለ?  አምልኮ ሕይወት የሌለበት ቤትና ሕይወት ግዜና ገንዘብ ምን ዋጋ አለው?  አንዳንዶች የሚኖሩበት ቦታ በልክፍት መንፈስ የተለከፉ ልጆች እንዲወለዱ አድርጓል:: ጉዳዩ ከተቀመጡበት ቦታ ያለው የመናፍስት ጥቃት ነው:: ለዚህ ነው የጸሎት ቤት መኖር ያለበት:: ሰዎች ብቻ አደሉም በሽተኞች ቦታውም ጭምር መሆኑ ሊገባን ይገባል:: ልጆችም ከዚያ ተወልደው አባታቸው ሲሰግድ ካዩ እነርሱም ሲያድጉ ሲጎለምሱ እና ለሌላው በረከት የመሆን ራእይ አላቸው:: እኛ እንግዲህ ከባዶ ቤት ተወልደናል ባዶነታችንን ልናምንበት ይገባል:: ስለዚህ የጽሎት ቦታ ያለው ቤት ከፍተኛ ትርጉም ያለው ነው:: የጸሎት ቦታ ያስፈልገናል::ከቤቱ አንዱ ክፍል የምስጋና ቦታ መሆን አለበት:: ለቴሌቭዥን ለሶፋ...አልፎም ለጫት ቦታ አለን ለአምላክ ግን ቦታ የለንም:: የእግዚያብሔር ምሕረት በየት በኩል መጥቶ ነው የሚባረከው? የእግዚያብሔር ራእይ በየት መጥቶ ነው ክፉና ደጉን የሚለየው? በቤት ክራይ እንኳን የመጣው ቀላል አደለም:: ተከራዮች ቤት ሲቀይሩ ጸልየው: እጣን አጢሰው: የምስጋና ጸሎት ጸልየው: እግዚያብሔር እለት እለት ያንን ቦታ እንዲባርክ ለምነው: ዲያብሎስን አባረው መሆን አለበት::ከዚያ የሚወለዱ ልጆች የተባረኩ:ለምስጋና የተዘጋጁ: ለሰላማቸው ምክኒያት የሆኑ ልጆች ይወለዳሉ:: የአምልኮ ሕይወት የገባ ትውልድ መሰረታዊ ምልክቶች እነዚህ ናቸው:: እዛው ቦታ ላይ ሰግደው ጸልየው እዛው ሲተኙ እራይ ያገኛሉ:: ራእይ ስናገኝ ጥንቃቄ ማድረግ አለብን:: ራእዩ ያንተ ነው ወይ? ሲባል ሁለተኛ መልክት ይመጣል:: ከርሱም መሆኑ ተኝተን እንኳ ውስጣዊ ሰላም ይመጣል:: ሲነጋም  በረከቱ ይታያል: ሰላም እና ጸጥታው: ይመጣል:: ይህ ከጸሎት የሚመጣ በራእዩ እግዚያብሄር የሚሰጠው የመንፈስ ቅዱስ ክብር ነው:: ከጸሎት የሚመጣ ጸጋ:ክብር ነው:: እግዚያብሔር ለያንዳንዱ ክርስቲያናዊ ህይወት ላይ መልስ አለው::

ጸሎት ስናደርግ የመንፈሱ ባሕርያት

መሥገድ እና መጸለይ ሲጀምር በቤቱ ወይም በሕይወቱ ያለው መንፈሱ ይታገለዋል:: ለግዜው እንዲጨነቅ ያደርጋዋል:: በመቁጠርያ እየገረፈ  ጭንቀትህን አቁም ይላል የእግዚያብሄርን እርዳታ ይጠይቃል:: አምልኮቱን እየሰጠ ይቀጥላል:: ሐጢአትን እና ክፉ ሐሳቦችን ይቃወማል:: የሚሰራው እና በአለም ያለ የሚያየው ነገር የተባረከ እንዲሆን ጸልዮ ይወጣል:: እግዚያብሔር ካላበረታኝ እያሉ ማሳበብ መኖር የለበትም:: መንፈሱ መኖሩ ምልክቱ ለግዜው ራእይ ይከለክላል: መደንገጥ: ቅዥት የበዛበት ይሆናል: በሚተኛበት ቦታ ላይ መሯሯጥ:ቶሎ ቶሎ መባነን: ከእጅም ከእግርም አካባቢ መደንገጥ:: በጸሎት ቦታ በሚተኛበት ግዜ መንፈሱ ከሰው ጋር ተዋህዶ ስለሆነ አዲስ ነገር እየመጣበት ስለሆነ መንቀጥቀጥ: አውሬ ማየት :እንደ አይጥ መስሎ ሽርር ማለት በሰውነት አካባቢ ወይም በሚተኛበት ቦታ መራራጥ ናቸው::  በዚህ ግዜ መገሰጫ መንገዱ ሲነጋ ጸሎት ቦታ ላይ በሚቀመጥ በመቁጠርያ እንዲህ አይነት ራእይ አቁም አውቄአለሁ:: በክርስቶስ ስም አስሬሃለሁ:: የአንተን የጥፋትና የሞት ራእይ አልፈልግም! በድንግል ማርያም ስም አዝዤሃለሁ ብሎ ማታ ቀጥቅጦት ከተኛ ይህን አይነት ራእዩ ቀጥ ይላል:: እንዲህ አድርጎ ሲመታው ራእዩን መከልከል አይችልም:: "ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤" ዩሐ. 1:12 ነው የሚለው የግድ ቄስ ጳጳስ መሆን የለበትም:: ክርስቶስን በስጋና ደሙ ለተቀበሉት: በሰማያ አምባ ተስፋ አድርገው በቅድስና እንጀራ ለተባረኩት በስሙ ለሚያምኑት ስልጣንን ሰጣቸው:: በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በተባረኩበት ስም አቁም ማለት አለበት:: ደዌም ወይም ከፍተኛ የራስ ምታትም/ማይግሬን/ ከሆነ በመቁጠርያ ሲመታው 5ት ምልክቶችን ያሳያል እነርሱም:- መውረር: መብላት: ማቃጠል: በሰውነት ውስጥ መሄድ እና በሚመታበት ግዜ እንደ ድንጋይ መሰማት የመንፈሱ መኖር ምልክት ነው:: እግዚኦ ማረነ ክርስቶስ: በእነተ ማርያም ማረነ ክርስቶስ : ኪርያላይሶን ክርስቶስ : በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም; በድንግል ማርያም ስም: ሰይጣንን በሰበረው በቅዱስ ሚካኤል ስም: በቅዱስ ገብሬል ስም: ውስጤ የተደበክ ጠላቴ ነርቭ የሆንከው: በሽታ የሆንከው: ቅዥት የሆንከው ተስፋ መቁረጥ የሆንከው መንፈስ እገስጽሃለሁ ብሎ ሲመታው ያልኳቸው ምልክቶች ይታያሉ:: ከዚያም በድንግል ማርያም ስም ወደ ግንባር ውጣ ሲለው ከሰውነቴ እንደሚንቀሳቀስ ነገር ወደ ግንባር ይወጣል:: ግንባር ላይ መታሰሩ በሌሎች ሰውነት ክፍሎች ላይ በአእምሮ በልብ ላይ ገዢ እንዳይሆንና :እየሰገደ ስለሚያዳክመው ነው: ሰግዶ የማያውቅ መንፈስ እየሰገደ ሲያሳየው በቀላሉ ይሸናፋል:: በሚሰግድ ግዜ ግንባሩን የሚያሳርፍበት የመስገጃ ስዕል ያስፈልገዋል:: ይህም የጌታችን : የስላሴ ስዕል ወይም የድንግል ማርያም ወይም መጽሐፍ ቅዱስ ወይም ድርሳናት ግንባሩን የሚያሳርፍበት መኖር አለበት:: ግንባሩን ማሳረፍ ልዩ መልክት አለው:: አምላኬ አንተን እወዳለሁ እገዛለሁ ፈጣርየ ነህ ማለት ነው:: "የሚያከብሩኝን አከብራለሁ" እንዲል:: 
ሌላው ደግሞ በኑሮየ በስልጣኔ በእድሌ ላይ አዛዥ አትሆንም ይህ ስልጣንህ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተሽሯል እያለ ሊነግረው ይገባል:: ክርስቲያን ከሆንክ ክርስትናህን ለማስተው ሰይጣን መታገል አለበት:: ከዘር የሚመጣ መንፈስ ነጻ አትሆንም:: ሰይጣን የራሱን ልጆች አሳድጓል: የእግዚያብሔር ልጆች ለመሆን የአምልኮት ሕይወት ሊኖረን ይገባል::  ጠላታችን በውስጡ መኖሩን እያንዳንዱ ማመን መቻል አለበት:: ባልና ሚስት ሁለቱም አብረው መጸለይ አለባቸው:: አንዱ አንዱን በልቶ:ልጆቻቸውን በልተው ስለሚሆን: የጸሎት ቦታ ሲኖር ልባቸው ሲሰበር አንድ የሚሆኑበትን መንፈስ ሲያገኙ ወደ እኔ ይደውላሉ: ራእያቸውን ይገልጹልኛል: ወደ በረከት እና ሰላም ይመጣሉ:: 

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ?


ሙሉ ትምሕርቱን ከ
Radio Abisinia Interview archive

ያልሰገደ ትውልድ ራዕይ የለውም! ለሚሰግዱ ሠዎች፥ እግዚአብሔር መንገድ አለው።
የጸሎት ሥነ-ሥርዓት፦
፩ኛ፤ በመንፈቀ ሌሊት
፪ኛ፤ በነግህ ጊዜ ፲፩ ሠዓት (5:00 AM በፈረንጆች) ዌዳሴ ማርያም፣ ሰይፈ መለኮት፣ ሠይፈ ሥላሴ ወይም ከቅዱሳን አንዱ፤
፫ኛ፤ በ፫ ሠዓት (9:00 AM በፈረንጆች) አርጋኖን፣ መልክአ ገብርኤል፤
፬ኛ፤ በ፮ ሠዓት (12:00 PM በፈረንጆች) መልክአ ስላሴ፣ መልክአ ሚካኤል፤
፭ኛ፤ በ፱ ሠዓት (3:00 PM በፈረንጆች) መልክአ መድኃኒዓለም፣ መልከአ ኡራኤል፤
፮ኛ፤ በ፲፩ ሠዓት
፯ኛ፤ ማታ ከመኝታ በፊት በ፫ ሠዓት (9:00 PM በፈረንጆች) መልክአ ሩፋኤል፣ አርጋኖን፤
በተጨማሪ፦ በነዚህም በሰባቱ የጸሎት ጊዜያት፥ እግዚኦታ ፲፪ ጊዜ፣ በእንተ ማርያም ፲፪ ጊዜ፣ ኦ አምላክ ፲፪ ጊዜ፣ ኦ ክርስቶስ ፲፪ ጊዜ፣ ያድኅነነ እመዓቱ ፲፪ ጊዜ፣ ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከን ፲፪ ጊዜ፤ ማድረስና ከቀዳሚትና ከእሑድ እንዲሁም ከታላላቅ በዓላቶችና ሥጋ ወደሙ ከተቀበሉበት ዕለት በስተቀር ሰባት ሰባት ጊዜ መስገድ ይገባል።
ልዩ ማሳሰቢያ፦ ሥራና ጸሎት ጐን ለጐን የሚጓዙ (በሥራ መስክም እያሉ ጸሎትን አብሮ ማዋሕድ ስለሚችሉ) ስለሆነ፤ የሥራን ሠዓት ሳይሻሙ እግዚአብሔርን በአጭር ጸሎት አነጋግሮ (ጸልዮ) ወደ ሥራ መሰማራት ይቻላል።
በ፮ ሠዓት ጸሎት (12:00 PM በፈረንጆች) መልከአ ሚካኤል ማንበብ፦
* ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እርዳኝ፣ የአጋንንትን ኃይል ገስፅልኝ፣ ርኩሳን መናፍስትን አስወግድልኝ፣ ታላቅ የኾነውን ቅዱስ የኾነው ሰይፍህን በክፉ መናፍስት ላይ ጣለው፣ ቆራርጠው፣ የበረከትህን ተስፋና ኃይል ለእኔም ስጠኝ፣ ከጎኔ ተሰለፍ፣ ኃይሌን አጠናክር፣ ውስጣዊ ሕይወቴን በመንፈስህና በፀጋህ አስበኝ፣ በምስጋና ስፍራ ኹሉ፤ በጸሎትህ እርዳኝ። አባታችን ሆይ ........
የዘወትር የአምልኮ ስግደት፦ (መቅረት የሌለበት)
* ለአብ እሰግዳለሁ፣ ለወልድ እሰግዳለሁ፣ ለመንፈስ ቅዱስ እሰግዳለሁ፣ ምስጋና ይሁን ለአብ፣ ምስጋና ይሁን ለወልድ፣ ምስጋና ይሁን ለመንፈስ ቅዱስ፣ በረከቱን ለሰጠን፣ ኃይሉን ላበዛልን፣ በዚህ ሠዓት ላቆመን፣ በቸርነቱ መንገድ ለመራን፣ በዚህ ሠዓት በፀጋ ለጠበቀን፣ በብርሃኑ ኃይል ለመራኸን፣ ላንተ፥ ክብር ምስጋና ይግባኽ፤ ሃሌ ሉያ ለአብ፣ ሃሌ ሉያ ለወልድ፣ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ፤ ቅዱስ እግዚአብሔር፣ ቅዱስ ኃያል፣ ቅዱስ ሕያው፣ ቅዱስ ኤልሻዳይ፣ ቅዱስ አዶናይ፣ ቅዱስ ያህዌ፣ ቅዱስ ጸባኦት፣ ቅዱስ ኢየሱስ፣ ቅዱስ ክርስቶስ፣ ቅዱስ አማኑኤል፣ የድንግል ማርያም ልጅ፤ ክብር ምስጋና ይግባው!።
የንስሐ ስግደት፦
* ኪርያ ላይሶን ኢየሱስ፣ ኪርያ ላይሶን ክርስቶስ፣ ኪርያ ላይሶን አማኑኤል፣ አቤቱ ክርስቶስ ሆይ ማረን፣ አቤቱ አምላክ ሆይ ማረን፣ አቤቱ መድኃኒዓለም ሆይ ማረን፣ አቤቱ የድንግል ማርያም ልጅ ሆይ ማረን!።
ክብረ በዓል ከሆነ፦
* ስብሐት ለአብ፣ ስብሐት ለወልድ፣ ስብአት ለመንፈስ ቅዱስ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር፣ ቅዱስ ኃያል፣ ቅዱስ ሕያው፤ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ።
የክብር ስግደት፦
* ለቅዱስ ሚካኤል እሰግዳለሁ፣ በቅዱስ ሚካኤል እሰግዳለሁ።
የፀጋ ስግደት፦
* ለድንግል ማርያምም እሰግዳለሁ፣ ክብር ምስጋና ይገባሻል።





Friday, February 10, 2012

Testimony of a protestant pastor from east Hararge

The pastor, based in Hararge, eastern Ethiopia, reveals the deleterious plan of protestants on ETOC.  Being famous in the town, he was abused by protestants to implement their destructive mission. He brought back all the materials which originate from USA. These materials are prepared to deceive and wage religious war on ETOC. Some of them are New King James version bible, many CDs and manuals partly prepared by him and are planned to be distributed. He explained why they hate Saint Mary, the cross and the arc of covenant. Later in his life his two legs were crippled and he has to use a stick to walk. This was the start of his awakening. This is a short clip taken from Memehir Grima new video, Part 15 (disk B).


Tuesday, January 17, 2012

Artist Tamirat Molla has been healed by Holy Water from Blood Cancer

This is the true story of Artsit Tamirat Molla, a famous musician in Ethiopia. He was cured from blood cancer by holy water. He asked his professor friend to bring to him holy water from Saint Mary Church in Ethiopia. In the next week his recovery has been miraculous even to Doctors in United states. የእመቤታችንን አማላጅነት በህይወታችን እናውቀዋለን::


Tuesday, January 3, 2012

Memihir Girma Miracles: Nequ part 14:The story of Fikrte Tibebu


This is the true story of Fikerte Tibebu, who has been blind for 19yrs. She is law graduate of Addis Ababa University and serving as a Legal Expert in Ethiopia's Human Right Commission . She was healed by the true power of the holy water by memehir Girma Wondimu in Estifanos Church, Addis Ababa. The news was captured in local( FM Sheger and newsprints) and international media ( Deutsche Welle-German Radio). This story is taken from part 14

DONOT miss the 3hr interview of  Memehir Girma with Abyssinia Radio as he explains everything and give his mobile address and when and how to CONTACT him.


Similar report witness are found here
http://www.debirhan.com/2011/06/miracles-at-ethiopian-orthodox-church.html

In case this link expires here is the story


By Anko Zuta,Blogger of De Birhan Blogspot
26-6-2011

A graduate of the Addis Abeba University Law School ,Fikerte Tibebu, has been healed from blindness after being baptised with Holy Water in St. Stephen's Church of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church ,Addis Abeba , Ethiopia. Fikerte was blinded some 19 years ago when she was a 7th grade student . Before joining Ethiopia's Human Right Commission as a Legal Expert, she worked at different departments of the Addis Abeba City Administration.
Many couldn't beleive their eyes when they noticed the lady they knew for many years writing with a braille and walking with a stick, suddenly running.

The above videos supported with an audio News reporting from the Addis Abeba based private FM Radio,Sheger 102.1 and live scene of the the baptism and ''exorcism'' explains that she has been blind for almost two decades and able to see after being baptised in St. Stephen's Church of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church ,Addis Abeba , Ethiopia.

This is a miracle! It has been also proved by the modern world science .

Her last message to the Radio audience and people at large was unifingly principled "May the Creator visit all those people who are worried like me , according to their own faiths/religions! "

When i was at home , I have been able to see first hand similar types of religious miracles in Entonto St.Mary Church, one of the oldest churches in north of Addis Abeba , built by King Menelik II and his wife Empress Tayetu a century and half ago.

Since coming to Europe I have been hearing of similar miracles happening in St. Stephen Church in the middle of Addis Abeba.

The head preacher and baptiser ,now ''Priest'' according to sources, Girma Wondimu , also on the above video has been the person religiously helping the process of healing and cure in St. Stephen Church . There are around two dozens of video CDs produced so far showing the types,means,and ways of healing by the same Priest exorcist . All these miraculous healing are done according to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church's ways and practices .
It was part of my plan to interview Priest Girma Wondimu in the past few months ,tough. I promise to interview him as soon as possible and produce a good report.

Until then ,I leave you with an article I wrote some five years ago about some of the amazing miracles i witnessed in the Entonto St. Mary Church. 
I had witnessed and heard of testimonies of people cured from various diseases such as HIV/AIDS,Cancer and so on and also people were able to be healed from complete blindness,and other disabilities in the Church of Entoto St.Mary .


Wednesday, December 28, 2011

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ? ኢትዮጵያውያንና የያዕቆብ የመጨረሻ ልጅ የቢኒዖን (ብንያም)ነገድ

የጸሎት ቦታ እንዴት ላዘጋጅ?

1. የጸሎት ጊዜያት

ልበ አምላክ ነቢየ ልዑል ቅዱስ ዳዊት”ስብዓ ለእለትየ እሴብሐከ በእንተ ኵነኔ ጽድቅከ ፣ስለ ጽድቅህ ፍርድ በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንሃለው”/መዝ 118-164/ብሎ እንደተናገረ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ሰባት ጊዜ በየእለቱ እንዲጸልይ ቤተ ክርስቲያን ታስተምረናለች፡፡ሰባቱ የጸሎት ጊዜያትም የሚከተሉት ናቸው፡፡

1.1 ጸሎተ ነግህ

ቅዱስ ዳዊት “አምላኬ አምላኬ በማለዳ ወደ አንተ እገሰግሳለሁ” መዝ 62÷11 እንዳለ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ ሲተካ፣ከመኝታችን ስንነሳ ምንጸልየው የጸሎት ዓይነት ጸሎተ ነግህ ይባላል፡፡በዚህ ጊዜ የሚከተሉትን ምስጢራት እያሰብን መጸለይ ይገባናል፡፡
.ሌሊቱን አሳልፎ ቀኑን ስለተካልን እያመሰገንን ወጥተን እስክንገባ በሰላም ጠብቆ ውሎአችንን የተባረከ እንዲያደርግልን እንጸልያለን።

·የመጀመሪያው ሰው አዳም የተፈጠረበትም ሰዓት በመሆኑ ያንን እያሰብን እንጸልያለን፡፡
·የሰውን ልጅ በመዓልትና በሌሊት የሚጠብቁ መላእክት ለተልዕኮ ሲፋጠኑ የሚገናኙበት ሰዓት ነው፡፡የሌሊቱ መልአክ ሲሄድ የቀኑ መልአክ ሲቀርብና ሲተካ የሚገናኙበት በመሆኑ በዚህም ሰዓት እንጸልያለን፡፡

.ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች በደል በጲላጦስ አደባባይ የቆመበት ሰዓት በመሆኑ እንጸልያለን።

1.2 ጸሎተ ሠለስት (3 ሰዓት)

ከነግህ በመቀጠል የምንጸልየው ጸሎት ጸሎተ ሠለስት (የሦስት ሰዓት) ጸሎት ይባላል፡፡ይህ የጸሎት ጊዜ
. ሔዋን የተፈጠረችበት
. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የቅዱስ ገብርኤልን ብሥራት የሰማችበት
. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ሲል በጲላጦስ አደባባይ የተገረፈበት
. ነቢዩ ዳንኤል ፊቱን ወደ ኢየሩሳሌም አቅጣጫ መልሶ የቤቱን መስኮት ከፍቶ የጸለየበት
. ለአባቶቻችን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ የወረደበት /በኢየሩሳሌም ጸንተው በመቆየታቸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ይህንን ታላቅ ጸጋ የተቀበሉበት /ሰዓት ነው፡፡

1.3 ቀትር(6 ሰዓት)

በእለቱ እኩሌታ ላይ የምናገኘው ይህ ሰዓትም እንደዚሁ የጸሎት ጊዜ ነው፡፡ይህም ጊዜ
.ሰይጣን አዳምን ያሳተበት
.በዕፀ በለስ ምክንያት ለስሕተት የተዳረገውን አዳምን ለማዳን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ አደባባይ የዋለበት
.የቀን እኩሌታ በመሆኑ የፀሐይ ሙቀት የሚያይልበት የሰው ልጅ ለድካም የሚዳረግበት በዚህም ምክንያት አጋንንት የሚበረታቱበት ጊዜ ነው።
.ስለዚህ የአዳምን ስሕተት፣ የዳግማዊ አዳም የኢየሱስ ክርስቶስ መሰቀልና መሞት፣እያሰብን የቀን እኩሌታ በመሆኑ መዳከማችንን ተገን አድርጎ አጋንንት እንዳይሰለጥንብን እየለመንን እንጸልያለን፡፡

1.4 ተሰዓተ ሰዓት (9 ሰዓት)

ዘጠኝ ሰዓት ላይ አራተኛውን ጸሎት እናደርሳለን።በዚህ ጊዜ
.ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ነጻ ለማውጣት በፈቃዱ ቅዱስ ሥጋውን ከቅድስት ነፍሱ የለየበት ሰዓት ነው።
·ቅዱሳን መላእክት የሰው ልጆችን በጎም ሆነ ክፉ ተግባር ወደ ፈጣሪ የሚያሳርጉበት ነው
·ቆርኖሌዎስ የተባለ መቶ አለቃ በጸሎት ጸንቶ ደጅ ሲጠና ከሰነበተ በኋላ ከፈጣሪው ምላሽ ያገኘበት ሰዓት ነው (ሐዋ 10÷ 9)
በዚህ ጊዜ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ እና ሞት አያሰብን ቅዱሳት መላእክት ከፈጣሪያቸው እንዲያስታርቁን እየለመንን የቆርኖሌዎስ እድል እንዲገጥመን እየተማጸንን እንጸልያለን፡፡

1.5 ጸሎተ ሰርክ (11 ሰዓት)

አምስተኛው የጸሎት ጊዜ የሠርክ ጸሎት ነው፡፡ስለዚህ የጸሎት ሰዓት ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ይላል፡፡”ጸሎቴን እንደ ዕጣን በፊትህ ተቀበልልኝ እጅ መንሳቴም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ትሁን” (መዝ 140 ÷2)
·ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው ከለየ በኋላ ወደ መቃብር የወረደበት ሰዓት ነው፡፡ (ማቴ. 27÷ 57)

1.6 ጸሎተ ንዋም (የመኝታ ጊዜ ጸሎት)

ይህ ጊዜ ዕለቱን በሰላም አሳልፈን ለሌሊቱ ዕረፍት የምንዘጋጅበት ነው፡፡በሰላም ላዋለን ፈጣሪ በሰላም አሳድረን ብለን ራሳችንን በእምነት የምናስረክብበት ነው፡፡እኛ ተኝተን የሚሆነውን አናውቅም እርሱ ግን የማያንቀላፋ እረኛ ስለሆነ ይጠብቀናል።ስለዚህ ከመተኛታችን በፊት ሊሌሊቱን እንዲባርክልን እንጸልያለን።
በዚህ ጊዜ፡-
·ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ ዛሙርቱን በጌቴሴማኒ ጸሎት አስተምሯቸዋል፡፡
·ቀኑ አልፎ በሌሊቱ ይተካል
ስለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለጸሎት ማስተማሩን እያሰብን እንጸልያለን፡፡ሰላም አሳድረንም ብለን ለፈጣሪ ራሳችንን በእምነት አደራ እናስረክባለን፡፡

1.7 መንፈቀ ሌሊት (እኩለ ሌሊት)

·እኩለ ሌሊትም እንደ ቀናቱ የጸሎት ሰዓታት የተለያዩ ትርጉሞች አሉት ።
ቅዱሰ ዳዊት ‘’መንፈቀ ሌሊት እትነሣእ ከመ እግነይ ለከ በእንተ ኵነኔ ጽድቅከ”“ስለ ጽድቅህ ፍርድ በእኩለ ሌሊት አመሰግነህ ዘንድ እነሳለሁ”/መዝ 118-62/በማለት ይህ ሰዓት ከእግዚአብሔር ጋራ የሚነጋገርበት እንደሆነ ገልጿል፡፡

· ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም ዋሻ የተወለደበት ሰዓት ነው።
· ሞትን ድል አድርጎ በታላቅ ኃይልም የተነሳው በሌሊት ነው።
· ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛ ለፍርድ ሚመጣበትም ሰዓት ነው።
ከዚህ የተነሳ ለእኛ ሲል ከሰማየ ሰማያት መውረዱን፣ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ መወለዱን በማሰብ ሞትን ድል እንደነሳልንም አስበን በማመስገን ዳግመኛ ለፍርድ ሲመጣ በቀኙ ከሚያቆማቸው ወገን እንዲያደርገን እየለመንን በዚህ ሰዓት እንጸልያለን፡፡

ሰባቱን የጸሎት ጊዜያት ጠብቀን መጸለይ ካልተቻለንስ?

በሰባቱ የጸሎ ሰዓታት የታቻለንን ያህል እንድንጸልይ ታዘናል፡፡እነዚህን የጸሎት ሰዓታት በገዳም ያሉ መነኮሳት በየበረሃው የሚዞሩ ባሕታውያን ይጠብቋቸዋል፡፡ይጸልዩባቸዋልም፡፡በከተማ በሥራ ምክንያት ሩጫ በዝቶበት በሁሉም ሰዓት መጸለይ የማይችል ክርስቲያን ግን ቢያንስ በማለዳ ከእንቅልፉ ሲነሳ እና ማታ ወደ መኝታው ሲያመራ መጸለይ ይገባዋል።ጠዋት እና ማታ በመጸለይ ከፈጣሪ ጋራ ያለው የአባትና ልጅ ግንኙነት እንዳይቋረጥ ማድረግ ይገባዋል፡፡
ምን እንጸልይ?
በመደበኛነት ልንጸልያቸው የሚገቡ ጸሎታት /በቤተክርስቲያናችን አባቶች በገዳማቱ በአድባራቱ የሚዘወተሩ እለታዊ ጸሎታት/ እነኚህ ናቸው፡፡

1.መዝሙረ ዳዊት

መዝሙረ ዳዊት በገዳማት ከሚኖሩ አበው መነኮሳት ባህታውያን ጀምሮ በካህናት፣ምእመናን በሁሉም ዘንድ በየእለቱ የሚጸለይ ጸሎት ነው።አባቶች ከፊደል ቆጠራው ቀጥሎ ዳዊቱን ያጠኑና ከዚህ ጊዜ ጀምረው እየደገሙት፣እየጸለዩበት ይኖራሉ።ዳዊት ሳይደግሙ ወደ ዕለታዊ ተግባራቸው አይሰማሩም።መዝሙረ ዳዊት እንደሌሎች ጸሎታት ሁሉ በየዕለቱ ተለይቶ የሚጸለይ አለው።ቀጥለን እንመልከት
ሰኞ ከ 1 - 30፣ማክሰኞ ከ 31 – 60፣ረቡዕ ከ 61 – 80፣ሐሙስ ከ 81 – 110፣አርብ ከ 111 – 130፣ቅዳሜ ከ 131 – 150
እሁድ- ጸሎተ ነቢያት እና መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ይጸለያል፡፡

አንድ ንጉሥ
መዝሙረ ዳዊትን ስንጸልይ ለዕለቱ የታዘዘውን ሃያ እና ሰላሳ መዝሙር ማድረስ ባንችል እንኳን አንድ ንጉሥ ማድረስ ይገባናል። አንድ ንጉሥ የሚባለው፡-አስር መዝሙር ነው፡፡ለምሳሌ ሰከኞ አንድ ንጉስ ለማድረስ ከፈቀዱ ከ 1 – 10 ያለውን ያደርሳሉ፡፡ከማክሰኞ ከሆነ ደግሞ ከ 30 -40 ያውን የመጀመሪያውን አስር መዝሙር ያደርሳሉ ማለት ነው፡፡ይህን ሁሉ ማድረስ ያልተቻለው ግን የተወሰኑ መዝሙራትን መርጦ በየእለቱ ያደርሳል፡፡

2. ውዳሴ ማርያም
ውዳሴ ማርያም ከተቻለ የሰባቱን ዕለታት ካልተቻለ የእለቱን ማድረስ ተገቢ ነው።የዘወትር ጸሎት ካደረስን በኋላ የዕለቱን ውዳሴ ማርያም አድርሰን ይዌድስዋ መላዕክትን ደግመን ከእመቤታችን በረከት ተሳታፊ መሆን ተገቢ ነው፡፡በዋልድባ የሚኖሩ መነኮሳት ውዳሴ ማርያም ከቅዳሴ ማርያም ሳያደርሱ ውለው አያድሩም፡፡በየአብነት ትምህርት ቤቱ የሚገኙ መምህራንና ተማሪዎች እና በየገዳማት ያሉ መነኮሳት ሁሉ ውዳሴ ማርያምን በየዕለቱ ያደርሳሉ፡፡እኛም ከአበው ተምረን ማታ ከመኝታ በፊት ወይም ጠዋት ስንነሳ ይህን ጸሎት ማድረስ ተገቢ ነው፡፡

3. ወንጌል ዘዮሐንስ
የዮሐንስ ወንጌልን በየምዕራፍ ከፋፍለን በየእለቱ ማንበብ ሌላው ጸሎት ነው፡፡አባቶች ይህንን ጸሎት በየእለቱ እያደረሱ ብዙ ተጠቅመውበታል።

4.ሌሎች ጸሎታት
ውዳሴ አምላክ፣ ሰኔ ጎለጎታ፣ መልክአ ኢየሱስ፣ መልክአ ማርያም ፣ በመዝገበ ጸሎት እንዲሁም በመዝሙረ ዳዊት መጽሐፍት ላይ ያሉትን ሌሎች ጸሎታት፣እንዲሁም ገድላት፣ተአምራትን፣እንደ ችሎታችን በየዕለቱ እናደርሳለን፡፡ቢያንስ ግን ይህ ሁሉ ባይሆንልን ከላይ የጠቀስነውን የመዝሙረ ዳዊትና ፣ውዳሴ ማርያምን ጸሎት ማድረስ ይገባናል፡፡

አጭር ጸሎት
በተቻኮልን እና መጻሕፍትን ለማንበብ ጨርሶውን ጊዜ በማይኖረን ሰዓት ይህንን እንድንጸልይ አንዳንድ አባቶች ይመክሩናል።አቡነ ዘበሰማያት፣ጸሎተ ሃይማኖት፣ሰላም ለኪ /ስለ ውዳሴ ማርያም ፈንታ/፣አቡነ ዘመሰማያት፣አንድ ከመዝሙረ ዳዊት/ መዝሙር 150/ በመዝሙረ ዳዊት ፈንታ/በመጨረሻም አቡነ ዘበሰማያት ማድረስ ብንችል መልካም ነው ።ጸሎተ ሃይማኖት የህይማንት መግለጫ በምህኑ እንጸልየዋለን። በመካከል ሰላም ለኪ በመድገማችንም የውዳሴ ማርያም በረከት ይደርሰናል። መዝሙረ ዳዊት 150 ስናደርስ ደግሞ ሁሉንም መዝሙራት የደገምን ያህል ይሆንልንና የዳዊቱን በረከት እናገኛለን፡፡ይህንን ሁሉ ማድረስ ካልተቻለን ግን ቢያንስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን አቡነ ዘበሰማያት ብለን ከቤታችን ልንወጣ ይገባናል።አጭር ጸሎት ከሥፍራ ሥፍራ ሊለያይ ይችላል፡;ዘጠኝ ሰላም ለኪ፣አስራ ሁለት አቡነ ዘበሰማያት በገዳማት ያሉ አበው ያደርሳሉ።

የጸሎት ቅደም ተከተል
አቡነ ዘመሰማያት: አንድ ከመዝሙረ ዳዊት:ውዳሴ ማርያም: እና ሌሎችም:ቀጥሎም አቡነ ዘመሰማያት በ እንተ እግዘዕትነ ማርያም: ጸሎተ ሃይማኖት በመጨረሻም አቡነ ዘመሰማያት ኪርያላይሶን 41 ግዚ::


አጭር ጸሎትን እነደ መደበኛ ማድረግ ለፈተና ያጋልጣል

አጭር ጸሎት የምንጸልየው በጣም በተቸገርንበት፣ጊዜ ባጣንበት ሰዓት ነው።ይህንን ጸሎት እንደመደበኛ ይዞ በየእለቱ አንድ አቡነ ዘበሰማያት ብቻ መድገም ግን ስንፍና እንዳይሆን ያስፈራል።ይልቁንም በክርስትና ሕይወት ጅማሬ ላይ ያሉ ምእመናን/ወጣንያን/ክርስትናውን እስኪላመዱ ጸሎታቸው አጭር ሊሆን ይችላል።እየቆዩ ሲሄዱ ግን በጸሎት እየበረቱ ወደ መደበኛው ጸሎት መድረስ አለባቸው።ሁል ግዜ ወተት መመኘት ሁል ግዜ አልበረታውም እያሉ አጭር ጸሎት እያደረሱ መተኛት ተገቢ አይደለም።ይህ አይነቱ አካሄድ የእግዚአብሔርን ቸርነት ለስንፍና ምክንያት አድርጎ መጠቀምም ነው።ከዚህ ጋር በቤተክርስቲያን አገልገሎት ላይ ያለንም ዳዊት መድገም ውዳሴ ማርያም ማድረስ ይጠበቅብናል።የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ፣ዲያቆናት፣ቀሳውስት፣ሰባክያነ ወንጌል፣መዘምራን……እነዚህን ጸሎታት መጸለይ ይጠበቅባቸዋል።አልያ ግን እያወቅን ጸሎት ማድረስ እንዳለብን ብዙ ጊዜ ተምረን እንዳልተምርን ቸል ብንል ለፈተና መጋለጥ ይመጣል።ከእግዚአብሔርም ቸርነት እንድንርቅ ያደርገናል።

አቡነ ዘበሰማያት የጸሎታችን መነሻና መድረሻ ጸሎት ስናደርስ የጸሎታችን መነሻ (መጀመሪያ) አቡነ ዘበሰማያት ነው፡፡በመካከል ጸሎት አቋርጠን ከሰው የምንነጋገርበት ጉዳይ ቢገጥመን በአቡነ ዘበሰማያት ማሰር ተገቢ ነው፡፡በአቡነ ዘበሰማያት አስረን የገጠመንን ጉዳይ ፈፅመን እንመለሳለን፡፡ከዚያም አቡነ ዘበሰማያት ብለን ካቆምንበት እንቀጥላለን።ጸሎታችንን በአቡነ ዘበሰማያት ሳናስር በመሃል እንዳሻን እንዳናቋርጥ አበው ያስተምሩናል፡፡

የማህበር ጸሎት

በቤታችን ከምንጸልየው ጸሎት በተጨማሪ በቤተክርስቲያን ተገኝተን ጸሎት ማድረስ ተገቢ ነው።ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ቤት እንደመሆና በእርሱአ የሚጸለይ ጸሎት ከጸሎታት ሁሉ የላቀ ነው።በካህናት እየተመራ ፣በሕብረት ሆነን የምናደርሰው በመሆኑ ታላቅ ኃይል አለው።እግዚአብሔር በቤተ መቅደስ የምንጸልየውን ጸሎት እንደሚሰማ ሲያመለክተን እንዲህ በማለት ነግሮናል።”አሁንም በዚህ ሥፍራ ለሚጸለይ ጸሎት ዓይኖቼ ይገለጣሉ ፣ጆሮቼም ያደምጣሉ።ስሜ ለዘላለም በዚያ ይኖር ዘንድ ይህን ቤት መርጫለሁ ቀድሻለሁም ዓይኖቼ እና ልቤም ዘወትር በዚያ ይሆናሉ።”/2 ዜና መዋ 7-15/ ከዚህ አንጻር በቤተ መቅደስ እየተገኘን መጸለይ ተገቢ ነው።በሰንበት ቀን ኪዳን ማድረስ ፣ ቅዳሴ ማስቀደስ የመጀመሪያው እና ዋነኛው ተግባራችን መሆን አለበት።በሰንበት ያለ በቂ ምክንያት ቅዳሴ የሚያስታጉል በቀደሙ አባቶች /አባ ሚካኤል ወአባ ገብረኤል/ቃል መወገዙን የተአምረ ማርያም መቅድም ይነግረናል።ከዚህ ጋር በሰዓታት ፣በማኅሌት ጸሎታት ላይ በመገኘት ቤተ ክርስቲያናችን ካዘጋጀችልን የማይጠገብ ማእድ ልንሳተፍም ይገባናል።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች የሃይማኖታችን ፍጹም ፍቅር የሚኖረን ከእነዚህ ጸሎታት ጋር ስንተዋወቅ ነው።አልያ የእንጀራ ልጅ መሆን ይመጣል።የመናፍቃንን አዳራሽ መናፈቅ ይመጣል።

ከላይ በተመለከተው የጸሎት ጊዜ እየተጠቀምን፣የጸሎት ዓይነቶችንም በምንችለው መልኩ እያደረስን፣በቤተ መቅደስ እየተገኘን ኪዳን እያደረስን፣ቅዳሴ እያስቀደስን ከፈጣሪን ጋራ እለት እለት እንነጋገር ጸሎት ከሌለ መንፈሳዊነት ጥያቄ ውስጥ ይገባል፡፡ከጄነሬተሩ ተቋርጦ ገመዱ ተበጥሶ ብቻውን እንደተንጠለጠለ አምፖል መሆን ይመጣል፡፡ስለዚህ በርቱ  ጸልዩ ፈጣሪ ለሁላችንም ብርታቱን ያድለን፡፡አሜን

የጸሎት ቦታ እንዴት ላዘጋጅ?

ስለ ጸሎት እና ክርስቲያናዊ ህይወት 
http://www.eotc-mkidusan.org/site/images/stories/pdfs/Kirstianawi_Hiwot_Ena_Migbar3.pdf

ኢትዮጵያውያንና የያዕቆብ የመጨረሻ ልጅ የቢኒዖን (ብንያም)ነገድ 
 ሁሉንም ከመምህር ግርማ ጥልቅ መንፈሳዊ ትምህርቶች

ቢኒዖኒ ማለት የጭንቅ/ሙት ልጅ ማለት ሲሆን እናቱ እሱን ስትወልድ በመጨረሻ ጣሯ ያወጣችለት ሥም ነው፡፡ ቢኒዖኒ እንደ ወንድሙ ዩሴፍ እናቱ በበረከትና በእግዚአበሔር አምልኮት ሳይሆን የፀነሰችው የአባቷን የላባን ጣዖት ሰርቃ በነበረበት ወቅትና ያዕቆብ ቤተሰቡን ይዞ ከላባ በተለየ ጊዜ ላባ ጣዖቴን ሰረቀሃል ብሎ ሲከተለው ያዕቆብም ከቤተሰቤ ያንተን ጣዖት የሰረቀ/የምታገኝበተ ሰው እሱ ይሙት (ዘፍጥረት 31፡ 32)ብሎ ከረገመ በኋላ ነው (ሙሉ ታሪኩ ዘፍ 31፡ 22-42)፡፡ እንደ ያዕቆበም እርግማን ራሔል ቢኒዖኒን (ብንያምን) ስተወልድ በጭንቅ ሞተች!! ምንም እናቱ ቢኒዖኒ (የጭንቀቴ ልጅ) ብትለውም አባቱ ይወደው ነበርና ብንያም (የቀኝ ክንዴ) ብሎት ነበር (ዘፍ 35፡ 16-21)፡፡ ሆኖም ግን በኋላ ያዕቆብ የልጆቹን መጻኢ ዕድል ለመወቅ እግዚአብሔርን ሲጠይቅ የብንያም ዕጣፈንታ በጣም የሚያሳዝን እንደሆነ እግዚአብሔር ነግሮት ብንያም ነጣቂ ተኩላ ነው (ዘፍ 49፡ 27) ብሎ ነበር፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ የብንያም ነገድ አሳዛኝ ታሪክ ያለው ነው፡፡ምክነያቱም በዘር የተላለፈ የክፉ መንፈስ (እናቱ ራሔል ያመለከችወ ጣዖት) እንደሆነ የሀይማኖት ጠባብቶች/ፈላስፋዎች ይናገራሉ፡፡ ይህ የክፉ መንፈስ ዘር ከዘመናት በኋላ የብንያም ነገድ የሆነውን ንጉሱ ሳዖልን እንዴት እንደጣለው መጽሐፍ (ሳሙ ቀ ዳማዊ 31፡ 1-13) እንድናሰተውል ይጋብዘናል (ሙሉ ታሪኩ መ.ሳ ቀዳማዊ)፡፡ ኋላም በክርስቶስ ዘመን የብንያም ነገድ የሆነውን ሳዖል (ኋላ ቅዱስ ጳውሎስ) የቱንም ያህል ለእግዚአብሔር ቀናኢ ቢሆንም ክርስቶስን ለማሳደድ ዳርጎት እንደነበር፣ ልዑል አምላክ ግን ለእሱ ያለውን ቀናኢነት ስለተመለከተለት ለጥፋት ሲጓዝ መንገድ እንደዘጋብት፣ አይኑን እነዳሳወረው ይድንምና ማድረግ የሚገባውን ያውቅ ዘንድ ወደ ካህኑ ሐናንያ እንደላከው፣ ከአይኖቹም ቅርፊት እንደተነሳ መጽሐፍ ይናገራል(ሐዋ 9፡ 1-21)፡፡ ይህ ሁሉ ከሆነም በኋላና ቅዱስ ጳውሎስ በጨርቁ ሳይቀር የሌሎችን ደዌና ርኩስ መንፈስ እያሰወገደ አንኳን ይህ ክፉ መንፈስ እጅግ ሲፈታተነው እንደነበር መጽሐፍ ይናገራል፡፡ በመጨረሻ ግን ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን የክፉ መንፈስ ዘር ለማቋረጥ የቻለ የብንያም ወገን ሆኗል፡፡

በዘር የሚተላለፉ ሚስጥራዊ የጤና ችግሮችና የክፉ መናፍስት ጥቃቶች (Genetically transferable enigmatic health challenges vs evil spirit attacks) ሁላችንም በአፅእኖት ልናስተውለው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ ብዙ ችግሮቻችን ከዘር የተወረሱ ተብለው በስያሜና በይሁንታ ተሸፋፍነው የክፉ መናፍሰት ሴራዎች ለመሆናቸው ጉዳይ ሳንሰጣቸው ቀርተናል፡፡
• አይናችን ቢፈዝ የዘር ተብለን መነፅር መሰካት፡፡ መነፅሩ ባልኖረበት ዘመን በኖሩ ዘሮቻችን (ወገኖቻችን) የማይታወቀው የእይታ ችግር (Sight) ዛሬ ብዙዎቻችንን እንዳጠቃን እናስተውል፡፡ መነፅሩ ባይኖር ምን ልንባል ነው? አይነስውር?
• ነርቭ፣ስኳር፣ደምግፊት፣ ኦቲዝም/ዳይሜንሺያ፣ አስም፣አለርጂ፣ ለምፅን ጨምሮ ልዩ ልዩ የቆዳ ችግሮች ወዘተ ሁሉ ከዘር ጋር እንሚገናኙ ሳይንስ ይናገራል፡፡ ነገሩ ልክ ነው ግን ሳያንስ ችግሩ በዘር በሚመጣ የመንፈስ ጥቃት ሳይሆን በዘር በሚተላለፍ ደካማ ዘረ-መል (gene) እንደሆነና ለማቋረጥ ምናአልባት ዘረ-መሎቹን ማሰወገድ (gene knock out) አመራጭ ነው ይለናል፡፡ የስነሕይወቱ ሳይንስ (Biology) ይህን ይበል እንጂ በተግባር ግን ጉዳዩ ውስበስብና የማይቻልም ነው፡፡

• አንዴ የዘር (genetic) ተብሎ ተፈቅዶለታልና ይህ ክፉ መንፈስ ከኛ በሚመጡት የልጅ ልጆቻችን እንዲቀጥል ፍቃድ መስጠታችንን አንዘንጋ፡፡ እንደ ጳውሎስ እሰካለቋረጥነው ድረስ እንሚቀጥል ልብ ልንል ይገባል፡፡!
እኔም በአቅሜ በማስተዋል እንድንሔድ እናገራለሁ፡፡ ሊያውም ሳልወድ በግዴ! ለካ እንዲህም አለ! ለልዑል አመላክ ምሰጋና ይግባውና እኛን ሆኖ ተግልጦ በምደር የተናገረውንና የሠራውን ብዙዎቻችን ሳንወድ በግዳችን ዛሬ አይተን እንድናምን አድርጓል፡፡ ምንም ሳያዩ ያመኑ ብፁዐን ናቸው ቢባልም፡፡ አይተን ላመንውም እግዚአበሔር ይመስገን! አይተውም አናምንም ብለው የተሰጣቸውን እድል አምቢ ያሉ ብዙዎች ይልቁንም የሚበልጡት ናቸውና፡፡ ማንም ሰው (ከለየላቸው በጣም ጥቂቶች በስተቀር) በእግዚአበሔር ታምናለህ ቢባል መልሱ አዎ ለመሆኑ አያከራክርም፡፡ እውን ግን አምናለሁ የሚለው ሁሉ ያምናል?! ከጥቂቶች በቀር አጠያያቂ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ እግዚአበሔርን አምናለሁ ብሎ የሚለው በዙ ሰው ሰይጣን አለ የለም ሲሉት የለም ብሎ የሚያምን መሆኑ በራሱ የእግዚአበሔርንም ስለሚፈራ ነው እንጂ በትክክለ አንዳለ ስለሚያምን አይደለም አግዚአበሔር አለ የሚለው፡፡ የእግዚአብሔርን ሀልዎት የሚያምን ሰይጣን እንዳለ አሳምሮ ያውቀዋልና! በሌላ መልኩ ስንታይ ደግሞ ከእግዚአበሔር ኃይል ይልቅ የሰይጣንን እገዛ አበዝተን የምነፈልግ ለመሆኑ በደንብ የምናስተውል ከሆነ ጠንቋይ፣ ቃልቻ፣ ደብተራ ወይም ሌላ አለ በተባለበት ቦታ የሚጎረፈውን ሕዝብ መመልከት ነው፡፡ በተቃራኒው የልዑል አምላክ ኃይል መገለጫዎች እንደ ኋላ ቀርነት ሞኝነት ሲቆጠሩ በትልልቅ መንፈሳዊያን በተባሉ ሰዎች ሳይቀር ይታያል፡፡ ነገሩ አይፈረድብንም መተት እንጂ የእግዚአበሔር ሥም ኃይል እንደሚሰራ መቼ በልባችን እናምናለንና የቱንም ያህል በአፋችን ኃይል የእግዚአበሔር ነው እያልን ብንቀሳፍትም፡፡ ይህ ሕዝብ በከንፈሩ የእርግማን ዘሮች!

ያመልከኛል… የሚለው የአምላክ ቃል በትክክልም ለእኛ እንደሆነ እናስተውል፡፡ እኮ ኃይል የእግዚአበሔር እንደሆነ ካመንን ለሚያምን ሁሉ ይሆንለታል ይላል፡፡ እንኳን ሁሉ ሊሆንልን እንቆጣጠረዋለን የምንለው ሁሉ ሲጠፋብን ነው የሚታየው፡፡ ችግሩ የእኛ ማመን ነው ወይስ የአምላክ ኃይል አለመኖር????? ሁላችንም ራሳችንን እንጠይቅ፡፡ ያመንን የመሰለን ሁሉ ተሸውደን የምድሩስ የምድር ነው የገሃነም እራት እንዳንሆን፡፡ ዳሩ ገሃንም (የዘላለም እሳት!!!) እንዳለስ ብናምን መች እንዲህ እንሆናለን፡፡ አለማመናችን በእናምናለን ድፍንነታችን መሸፈኑ ደግሞ አደጋው የከፋ ነው፡፡ አለማመኔን አርዳው (ቃሉ በወንጌል ማርቆስ 9፡ 23-24 አንድ ሰው ወደ ጌታ ቀርቦ ልጁን እንዲፈውስለት ቢቻልህ እዘንልኝ ባለው ጊዜ ጌታ ብቻልህ ትለኛለህ? ለሚያምን ሁሉ ይቻላል ባለው ጊዜ ሰውየው ደንግጦ ጌታ ሆይ አለማመኔን እርዳው ያለው ትዝ ስላለኝ ነው) ለማለት አንኳን እድል አላገኘንምና፡፡
አንዳንዶቻችን ራሳችንን መደለላችን እንኳን ሳይታወቀን አይተን እንድናምን የእግዚአበሔር ኃይል ሲገለጥልን እንኳን በምልክት አናምንም በሚል የራሱ በውስጣችን ያለው የክፉ መንፈስ ስልታዊ ሴራ እንዳናምን ተዳፍኖብን እንቀራለን፡፡ በእግዚአበሔር ተዓምር ማመን ምኑ ነው ጥፋቱ፡፡ ምልክትን ሁል ጊዜ ግን መከተል እንደሌለብንና ከእግዚአበሔር ያልሆኑ ምልክቶች እንዳያሳስቱን ምልክትን በጥንቃቄ እንድናስተውል ተነገረን እንጂ የልዑል አምላክ ኃይል ሲገለጥ ምልክት ነው እያልን እንድናወግዝ ልባችንንም እንድናደነድን አይደለም፡፡ በትክክልም እግዚአበሔር አምላክ ድሮ (እኛን ተረት እንደሚመስለን ሳይሆን) እንደሚያደርገው ዛሬም ያደርጋል፡፡ በትክክልም እሱን በሚያመለኩት ላይ ኃይሉን ይገልጣል፡፡ ችግሩ የልዑል አምላክ እግዚአበሔር ተዐምር ሳይሆን ምልክቱ እንዲገለፅበት ፀጋው የተሰጠውን ሰው ጭራሽ ተሰባሪና ሰው መሆኑን ዘንግተን የእሱ አምላኪ ስንሆን ነው፡፡ አደጋው ለባለፀጋውም ለእኛም ነው፡፡ ፀጋው በትክክል ከልዑል አምላክ ቢሆንም የሰዎች ሰውየውን ማድነቅና (ማክበር ግን አይደለም) ፈተና በመሆን ትመክህት እንዲያድርበት ሆኖ በመጨረሻ እሱም የተከተሉትም በአሰከፊ ሁኔታ መጥፋታቸው ነው፡፡ ትምክህታችውን ለልዑል አምላክ ክብር መገለጫ የሰጡ ግን ምንም አይሆኑም፡፡ ከላይ የጠቀስንውን የቅዱስ ጳውሎስን ታሪክ ማስተዋል ጥሩ ምሳሌ ነው፡፡ ትምክህቱ በልዑል አምላክ እግዚአበሔር ነበርና፡፡ በድፍረትም እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደምመስል እናንተ እኔን ምሰሉ እንዳለም፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ ንግግር ከስጋዊ ትመክህት አልነበረም በአምላክ ዘንድ ያለውን መተማመንና ለእምነቱም ያለውን ቁርጠኝነት ለሌሎችም ለማሳየት እንጂ፡፡

የምንገርመው ግን የእግዚአበሔር ሲሆን በምልክት አናምንም ያለንው የሰይጣንና አጋንንት ሥራዎች በሆኑት ምትሃቶች (ማጂክ) ስናምን አለማፈራችን ነው፡፡ ኧረ አንዳንዴም ሳይነሳዊ ትንታኔም ለመስጠት እንሞክራለን! እስኪ በየ ጋዜጣው/መጽሔቱ ላይ ያሉ የአስትሮሎጂ (የእድል ጥንቆላዎች)፣የኦሾና ራምፓ፣ የመዳፍ መስመር የመሳሰሉትን ስናነብ ምን እያደረግን እንደሆነ እራሳችንን እንታዘብ፡፡ በየጠንቋዩና ቃልቻው ቤት ለሚደረጉ የሰይጣን ምልክቶችስ፡፡ በአንድ ወቅት ዛሬ በማረሚያ ቤት ያለው ሰው በጣም ብዙና እጅግ ትልቅ የተባሉ ሳይቀሩ ተከታዮቹ እንደሆኑ ያወቅንው ኋላ ነው፡፡ የሰውም ብዛት ሲታይ ምን ያህሉ ሰው እውን እግዚአበሔርን እያመለከ እንደሆነ ጥያቄ ውስጥ የጣለ ነው፡፡ አንዳንዶች የሌሎችን ገንዘብ ፍለጋ (ለመሰለብ) ወይም ሌላውን ለማጥፋት በመቶ ሺዎች ገብረዋል፡፡ የክፉ ሰው ዘሮች! እነዘህ ክፋቶች እንደሚሆኑልን ስለምናምን በመቶ ሺዎች እንገብራለን፡፡ የእግዚአብሔርን ኃይል ግን ለማስተዋል አእምሮአችን ተዘግቶብናል፡፡ እግዚአብሔርን ለማወቅ አልፈለግንምና፡፡ እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልፈለጉት መጠን የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው ይላልና፡፡

አምላክ ሆይ ለማይረባ አእመሮ አሳልፈህ አትስጠን! እናስተውል ዘንድ አቤቱ አእሚሯችንን ክፈት! እርግማናችንንም አስወግድ! አሜን!

Who is priest/Exorcist Memeher Girma Wondimu?

 

የቀድሞው የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አስተዳዳሪ መላከ ሰላም ዘላለም እሰይ ስለ መምህር ግርማ ምን ይላሉ? 

 

 

What are the views of Ethiopian Orthodox Church on Memehir Girma Wondimu and his healing services?



 

Interview of Memehir Girma with radio Abysinia on leb le leb program

This is 4 part interview with Memehir Girma on radio Abyssinia. He has a message for Ethiopian diaspora. Memehir Girma clarifies everything he does and delivers a strong message on how to identify and remove the influence of evil spirit effects on family and life. He gives his contact address, mobile with precise instruction on how and when to contact Memehir Grima.  This is a must listen!!


Part 1 & 2


PART 3 CLICK here!



From memihir Girma VCD-

Nequ part 12 

In this video you see evidence that Memehir Grima is given the rank of gospel preacher on September 23,  1985 E.C. considering his long services. Along with this various other certificates showing his ability to heal and preach are presented. These are then followed by a ceremony honoring the services of Memehir Girma. It is opened by administrator of saint Estifanos church. Memehir girma is honored for his true healing services, preaching and contribution to the development of the church. The following are particularly mentioned: his 35yrs work that converted and brought back many followers to the church, he has helped many be free of bad spirits, claim back their spiritual life up to the holy Eucharist among others. The testimony of many church fathers follows, approving the he is the real father.

 

Nequ part 16

In Addis Admas news and others you may have read that memehir Girma service has been banned. In this part you see that he has been given the permission to continue his services after it has been proved by ETOC patriarchate head office on November 10,2004 E.C that his healing services are real. 

From cnn ireport. Please see this report in Part 15A too.

 http://ireport.cnn.com/docs/DOC-627906

Thousands of Ethiopians, foreigners find healing in Addis Abeba

Priest/Exorcist Girma Wondimu
The head priest/exorcist has advice
28-6-2011
By Tedla T.

Thousands of Ethiopians and some foreigners head to two Churches in Addis Abeba looking for religious healings from an Orthodox Priest/Exorcist Girma Wondimu. On Saturday and Sunday to St. Stephen Church, Meskel Square and on Tuesday and Wednesday to St. Michael Church, in Merkato, Addis Abeba. Thousands of Ethiopians and foreigners have given testimonies of healing and many have been open-mouthed by the miracles they have witnessed. Almost all types of ailments are healed through ‘Faith Healing’. This is one of the talking points in the religiously strong Addis Abeba today. The Priest regularly gives religious teachings and healing through baptismal and exorcism in the Ethiopian Orthodox Christian ways. I have had the opportunity to speak to him.
The excerpt follows,

Tell me about yourself please?

Priest/Exorcist Girma: I was born in 1951 (Ethiopian Calendar) in Bale, Ethiopia. In 1962(Eth.Calander) , I was ordained a deacon by Abune Mekarios at the St. Michael Church, in Bale Goba . I served as a deacon for 15 years in different parishes in Bale, Ethiopia. Then I completed preaching and prayer courses. Recently I was given additional trainings on prayers by religious fathers. They strengthened me. By taking the Holy Eucharist (Communion) often, I also got the spiritual gift from God that enables me identify the spirit. When teaching the Gospel to the people attending worship, I was then able to identify where the spirits were  amongst worshipers. When you take the Holy Communion, you see what Jesus Christ had seen. You do what Jesus Christ did. Because He said in the Gospel of John 14:12 “Very truly I tell you, whoever believes in me will do the works I have been doing, and they will do even greater things than these, because I am going to the Father.” In this world where betrayal is much, God is out of the philosophy; to quieten the material world’s wealth and wisdom, and reveal the secret; he showed/gave me the opportunity through His gift. So now I can say I have a Doctorate Degree of 35 years of investigation and research on spirits. And in all those years, I had served in Bale Goba, Zeway, Butajira (many Pentecostals and Muslims have been converted to Christianity),Meki,Jima,Teppi,Yirga Cheffe, Sidamo, Harar, Somali region, Neeus Tabia Ketema, Sudan, I have been in Addis Abeba for the past good years and will soon be heading to Wello, Haik, and others.

What did it include, prayers only or did it include healing and other services as I watched in the series of the Video CDs of the Faith Healings you have released?

Priest/Exorcist Girma : What you watched on the Video CDs is just a tip of it. Through my Service, all kinds of healing, safety and deliverance works are done. I spent all the 35 years in this Service. Out of the 35 years, I spent  nine of them exiled in Sudan.

Do you have a family?

Priest/Exorcist Girma : I am married and have three children. I live with my family now.

Doing these time and space taking Faith Healing Services and being over crowded with such a large mass, Won’t this affect your private and family life?

Priest/Exorcist Girma : My private life is only for prayer. The rest would all be fulfilled by the Will of God. After my Faith Healing programs, I spend my time in prayers and taking the Holy Communion frequently, because the way to defend devil is when you have Lord inside you, so it is by taking the Holy Communion that the devil is won and you get strengthened. Because He said “I am the bread of life.’’

Can you list me the total number of healings and their types?

Priest/Exorcist Girma: They are so many . Because it is quite expensive to have the blank CDs we use for recording the films on, we only do recordings sometimes and only few of the miracles selected. Hundreds of people are healed every day. For instance in Somali region, Ethiopia, we used to heal a bunch of 20 to 40 people at a time. So it is difficult to put it in figures but you can say around a million. You can say almost half of the 80 million of our population has been affected by demons. You can say after the revolution (1974), Habessha has become devil.
There were many types of cures ;some whose tongues was inside their necks were healed , crippled, disabled, deaf and some who were in coma were also healed, scientists were also cured, infertile gave birth , Pentecostal spirits were also healed . Many Europeans and Americans have been healed here too. Some of them are in high positions in their own countries. Their demons are easy to exorcise because it is not worshiped unlike ours.
I know that most priests in the old days used to have the gift of Faith Healing. Especially those that were before the coming of modern schooling were able to heal. Then, those who have abused their religious education for their own and devil’s benefits have popped up, who are wrongly named, Debteras (evil doers).


To those of my fellows in my generation who believe in rationality and logic such cures and miracles are unacceptable, some would even laugh when told about the miracles. What is your message for these people?


Priest/Exorcist Girma: These people are of four types: those that have totally denied God and are possessed by demon, second are relatives of the devil (witches, shamans, evil eyes and son ), third those affected by the spirit of philosophy (these is the modern Satan, say as in the case of Marxist and similar laws), fourth are those who succeed the place of devil by having a behaviour of discriminating, hate, and love of riches . The last or the fifth group are Christians. The four believe in materials. They believe in philosophies and when they see miracles they happen to be scared or at other times continue with their denials.


Such services of “Faith Healing’’ in our Church are increasing. I have seen many cases in Addis Abeba in places like Piassa, Ferensayee and so on. Some were proved wrong. How do you see that?


Priest/Exorcist Girma: Gifts of God's generosity are different. As long as one can heal, opposes the devil, and the rules and regulations of the Church are respected, I wouldn’t have anything against it. I believe the gift is only from God.


Did you have bad experiences?


Priest/Exorcist Girma: I was labelled by some laity as a non Christian and was even unable to find a place to sleep for some time. Some had also said that I don’t eat food at all. When I said that my time to break my fast has reached, an elderly lady whose children have been healed once said to me “do you also eat?” I also heard that some people accused me of being a magician, using a Sudanese witchcraft. Those who have been doing this were the types of people I sectioned into four above . One of the saddening things is that priests that knew me very well also failed to testify about me due to jealousy and bad intentions. Some with a rank of Pope, whom I had known in person, had also sent out a rumour, stating that I had a Sudanese witchcraft to do all these healings and this, had stereotyped many worshipers. This shows that the spirits of jealousy and badness that were in there during Genesis had not yet left the Church. There were also intimidations, breaking of my water pipe, protests and so on. But this is all improving now. Worshipers have known the truth now.


They say treasury gifts can spoil …do u take gifts?

Priest/Exorcist Girma: For all these services, nobody pays. It is all free. And there is no precondition to be healed all human beings of all religions, race or identity are allowed to come for healing. They get all the services for free.


So how do you live? Any source of income?

Priest/Exorcist Girma: From the sale of the Video CDs. The CDs show some of the live recorded miraculous ‘Faith Healing’ programs and preaching.

 

Do you have message for Ethiopians? We Ethiopians are suffering and agonized both in Ethiopia or while in exile. Our problems seem to be endless. Though we were one of the grandest, now we are the helpless.


Priest/Exorcist Girma : Very good. We are in this alarming image for one thing because our ‘Ethiopianess’ has gone out of us. Secondly, our religious direction has been contaminated by the communist thinking. Thirdly, a cursing spirit has entered us and our leaders have built the generation repeating the ‘Destroy it!’’ slogan. There was this culture that promoted the destruction of our past history, the Church, the monuments, and the heroes who protected the country. I am not a politician but I think a child that grew up with those slogans of ‘destroy it’ couldn’t be able to have love for the Country and values and respect for a religion. So we are harvesting a generation that grew up with the ‘destroy it’ slogan/word. That is why whatever we work and our fruits are destroyed, we are exiled and there is destruction there too, here we are and it is destroyed too, it is all destruction. Why? Because what we sow was curse, so we reap curse too. Ethical morality has been broken by Marxist thinking too. Sixty thousand Ethiopians in the times of the Revolution were always marching on Sundays saying “destroy it”, they used to eat meat on Wednesday and Friday that was a time where there was extreme exaltation and indulgence .When their slogan was made a reality by God, it is destruction again. The other thing is that , “going 40 years forward and 40 years backward’’ has become one of the natures of the Ethiopian history.


What is the solution?


Priest/Exorcist Girma : We have to return backward meaning to prayers, ethical education, the religious martyrdom of our fathers, firmness in belief, ceasing lying, and fearing God. Ethiopians have to begin a life of sainthood/sanctification. Sanctified people won’t starve, go to war, migrate, because God is the worrier under the protection of Angeles, they will be victorious. We aren’t sanctified. So all of us have to be blessed. If all are blessed, they will always win.

People of the world had attempted to change the world with materials but material is only reducing human beings. We see the technologies, satellites, internet, and mobiles advancing…although it is good and useful; it is also passing its limit. Leaders have been very wrong. Politicians have extremely lost their direction. So unless we return to the One who shows us directions, we will be in complete darkness. If we return to God, what we Ethiopians have is enough to the world. We are not either with the West or with ourselves; we have become losers.

In short, I would like to say to Ethiopians from the youth to elders to stop being lured with little things for the sake of filling their belly and be firm on their faith.