Tuesday, December 10, 2013

የዝሙት መንፈስ ምንድነው? አይነጥላ ምንድነው?


ዝሙት  
" የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች በዚህ የተገለጡ ናቸው " 1 ዮሐ, 3 : 10

ለብዙ ዘመን ያህል የካበተ የማሣሣቻ ልምድ ያለውና የሰዎችን መልካም ጠባይ የሚያበላሽው አንዱ የዝሙት መንፈስ ሲሆን ዘወትር እንደ አዲስ ነገር አመልካች በመሆንና ግፈትን በማጠናከር በልብ ውስጥ የሩካቤ ቅስቀሳ በማድረግና ሰዎች ዝሙትን እንደ ተለመደ ኖርማል ነገር አድርገው እንዲወስዲና ድርጊቱን በግልጽ ነውረኝነትና በድፍረት እንዲፈጽሙ ያነሣሣል : : የዝሙት መንፈስ እግዚአብሑር ለሰው ልጆች ከሰጠው የተፈጥሮ ጠባይ በማዛነፍና በማዛባት ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው ሰዎችን በማስነወር ለተፈጥሮ ግብር ተቃራኒ በማድረግና በማርከስ ፍጹም የአመንዝራነትና የሴሰኝነትን ሰይጣናዊ ጠባይ ያወርሳል ዛሬ በዓለማችን ላይ ያለው የተራቀቀ ቴክኒዎሎጂ በተለይም የኢንተርኔት አግልግሎት ከሰጠው አዎንታዎ ጥቅም በተጨማሪ በአሉታዊ መልኩ ሰዎች በዝሙት : በኮክብ ቆጠራ : በሥነ ልቦናና : በፍልስፍና ወዘተ . . . መንፈሶች እንዲ ልክፍት ከፍተኛ አስተዋጽፆ አበርክቷል : : " እንግዲህ በምድር ያሉትን ብልቶቻችሁን ግደሉ እነዝህም ዝሙትና ርኩሰት ፍትወትም ክፋ ምኞትም ጣዖትንም ማምለክ የሆነ መጐ ምጀት ነው በእነዚህም ጠንቅ የእግዚአብሔር ቁጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ ይመጣል : : "ቄላስይስ. 3 : 5 - 6  

የዝሙት መንፈስ የመግቢያ አቅጣጫዎች -

 አብሮ በሚወለድ አጋንንት ዛር በውርስ መንፈስ በኩል ከሴትዋጋር አብሮ በሚወለድ ወንድ የአጋንንት ዛር በተቃራኒው ደግሞ ከወንዱ ጋር አብራ በምትወለድ ሴት የአጋንት ዛር አማካኝነት - በመተት ለዲያብሎስ ያደሩ ሰዋች ወደ ሌሎች አስመትተው በመላክ - ከዓይን ላይ በሚነሣ መንፈስ (ብዳ) አማካኝነት ከውስጥ ወደ ውጭ በሚያይ የዝሙት መንፈስ ዓይን አማካኝነት የመንፈሱ ስሜት ይገባል : : - በማየት : በማዳመጥ : በማንበብ በኩል የሚገባ የወሲብ ፊልሞችንና ስዕሎችን በማየት ተመሣሣይ ወሲብ ነክ ንግግሮችን በሙሉ ሰሜት በማዳመጥና ጽሁፎችን በማንብ በፊልሙ በንግግሩና በጽሁፉ ላይ በሚናር ሙሉ ተመስጣ ወይም ከፍተኛ ትኩረት የተነሣ የዝሙት መንፈስ ወደ ሰዎች ይገባል : : ከዝህ በተጨማሪ መንፈሱ ከሰፈነበትና የሚውጠውን ለመፈለግ በሚንቀሣቀስበት አየርና መንገድ ላይ ያገኛቸውን ሁሉ ይጠልፋል : : ለዚህ በተለይ ምሳሌ የሚሆኑን በአገራችነ በኑሮና በባህል ተጽዕኖ አስገዳጅት ቺግር የገጠማቸውን አንዳንድ እህቶቻችንን እያሳደደና መጥፏ አማራጭ እያሳያቸው የሴትኛ አድሪነት ሕይወትን እንዲመሩ የመገፋፋቱ ጉዳይ ነው : : የእነዚህ የዝሙት መንፈሶች ተጋቦት ፈጣን በመሆኑ ዱያቢሎስ ስዎቹን ቅብጥብጥ : እፍረተ-ቢስ : ነውረኛ ርካታ-ቢስ ወዘተ. . . በማድረግ በመጨረሻ ሥነ-ምግባራቸውና ግብራቺው ለክርስቲያናዊ ሕይወት የሃይማኖት ቅድስና አደገኛ ይሆናል : : የሩካቤ ክፉ መንፈሶች ከሌሎቹ የጥፋተ መንፈሶች ለየት ባለ መንገድ ብዙ ጠባይ አላቸው : : ከነዚህም ውስጥ ለምሳሌ ሴት አጋንንት ዛር ከውንዱ ጋር አብራ ከተወለደች በእድገቱና በዕድሉ ስለምትቀና ሩካቤውን ለራስዋ በምትፈለልገው መልክ ትቆጣጠራለች : : በዚህ የተነሳ ሰውየውን ዓይነ-አፋር : ፈሪ እና : ድንጉጥ ልታደርገው ትችላለች በሴቷ ውስጥም ያለው ወንድ አጋንንት እንደዚሁ ዓይነት ተመሣሣይ ጠባይ ያሳያል ብዙ ጊዜ ይህ የዝሙት መንፈስ በዛር በኩል ውርስ ሆኖ ሊመጣ ወንዱንም ሆነ ሴቷን ፍጹም ዓይን ወደ አወጣ ሴሰኝነት በታቃራኒው ወደ ዓይነ-አፋርነት በመለወጥ ከፍተኛ አለመግባባት በባልና በሚስት መካከል በመፍጠር የወንዱ ሕይወት በሴቷ የሴቷ ሕይወት ደግሞ ሁለቱንም ጻታዎች ልባቸውን የሩካቤ ስሚታቸወን የሞተ አድርጎ በማሳቀቅ የሚያዝኑና የሚያለቅሱ ብቸኛ ሰው ሆነው የሌሎችን ትዳርና ልጆች ሲያዩ እንዲማረሩ አድርጎ ሕይወታቸውን በራሳቸው እጅ እንዲያሳልፉ ይህ የዛር መንፈስ ግፊት ያደርጋል : : የመንፈሱ ተጽዕኖ እጅግ ከባድና የሰዎች ጠባይ አውሬነት ሁሉ እስከ መለወጥ ያደርሳል ምክንያቱ ደግሞ ተደጋግሞ እንደተገለጸው አብሮ የተወለደው አጋንንት ዛር ሙሉ በሙሉ ከሰዎች ጋር ስለተዋሃደና ቤቱን በላያቸው ላይ ሠርቶ ዘሬናቸው እያለ ስለሚፍክር ነው : : 
 
" ይህን እወቁ አመንዝራም ቢሆን ወይም ርኩስ ወይም የሚመኝ እርሱም ጣዖት የሚያመልክ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መግስት ርስት የለውም " ኤፌ 5 : 5 

የሳጥናኤል ሠራዊት  * ባጀት አይፈልጉም የሚንቀሳቀሱት በአንተ በጀት ነው : : * ቢሯቸው አይዘጋም ምን ጊዜ ምክፍት ነው : : * አያንቀላፉም መዘናጋት በእነርሱ ዘንድ የለም : : * አያረጁም ጡረታ አይወጡም * በፓሊስ አይያዙም በፍርድቤት አይዳኙም * አይቀበሩም ወደ ሲኦል ተሸኝተው ካልታሰሩ በስተቀር አይሞቱም : : 

" የድንግል ማርያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ከርኩሳን መናፍስትና ከሴሰኝነት ያውጣንና ይጠብቀን " አሜን !

አይነ ጥላ

በማለዳ መያዝ መጽሐፍ ገጽ.57 
አይነ ጥላ በምናየው በምንረዳው በምንገነዘበው ወዘተ..መንገዳችን ላይ አሸምቆና ተደብቆ ጉዳት የሚያደርስብን የሚያርፍብ የክፉውን መንፈስ ጥላ ዋንኛው የዲያብሎስ የጥቃት ክንድ ነው::
የዓይነ ጥላ መንፈስን ልዩ የሚያደርገው በመጀመርያ ደረጃ በውስጣችን ሲገባ ከጠባያችን ጋር መመሳሰል መቻሉ አንዱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ተምረን ጥረን ግረን የት እንደምንደርስ እንዴት እንደምናድግና ዕድላችን እንዴት እንደሚቃና አስቀድሞ በማወቅና አርቆ የማየት ከፍተኛ ችሎታ ያለው መንፈስ መሆኑ ነው:: .....
ለምሳሌ እንመልከት
ቢሮ ከሆነ አንተ ውስጥ ያለው አይነጥላ  ከአንተው ላይ ተነስቶ አለቃህ ውስጥ ቀድሞ ገብቶ ይጠብቅሃል:: ቢሮ እንደደረስክ ራስህን እስክትጠላ በከባድ ቁጣና ሞራል በሚነካ ዘለፋ ያስተናግድሃል::የሥራህ ሕልውናም ሊያከትም እንደሚችል በመግለጽ ያስፈራራሃል ያስጠነቅቅሃል:: አንተም ያዙኝ ልቀቁኝ ማለት ትጀምራለህ:: ወደ አካል ግጭት ሁሉ ልታመራ ትችላለህ::
ተጨማሪ ያንብቡ...
በማለዳ መያዝ ቅጽ አንድ ከገጽ 57 ጀምሮ..

Monday, November 4, 2013

ከዓይን ላይ የሚነሣ መንፈስ (ቡዳ)



ከዓይን ላይ የሚነሣ መንፈስ (ቡዳ) ሰዎችን የተለማመደ ለዘናት ከሰው ልጆች ጠባይ ጋር ተመሳስሎ የኖረና ዘሩ ያደረገ ዓይነቱ ይለያይ እንጂ ሰውን በከፍተኛ ደረጆ የማጥቃት ልምድ ያካባተ የቱጋ ይዞ መቼ እንደሚጥል መረጀ ያለው ከመተቶች ሁሉ በበለጠ ሁኔታ የከፋ ጉዳት የሚያደርስ ከአንድ ወደ ሌላው ረቀቅ ባለ ችሎታ የሚተላለፍ አደገኛ የሆነ መንፈስ ነው : : ከዓይን ላይ የሚነሣ መንፈስን በአጭሩ (ቡዳ) በማለት ይጠራል : :

( የመንፈሱ የመግቢያ አቅጣጫዎች )

- ከቤተሰብ የሚወረስ ዛር ብዙ ጊዜ የቡዳ መንፈስ መነሻው ከእናት : ከአባት : ከአያት :
ከቅድመ አያት : ከቅም አያት ወዘተ . . . ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ዛር ሲሆን በመዋለድ በአካል በደምና በነፍስ ውስጥ ተዋሕዶ እየተወራረሰ እንደ ልክፍት የሚይዝ ነው : :

- በሌሎች ላይ የሚያርፍ መንፈስ ይህ ከመነሻው ተሸጋጋሪ ሳይሆን ከውጪ ወደ ውስጥ በዓይን አማካኝነት ወደ ሌሎች የሚሄድና በሌሎች ላይ የሚያርፍ መንፈስ ሲሆን በሇላም ተመልሶ ከውሰጥ ወደ ውጭ ሌላውን ለመብላት የሚንቀሳቀስ ጠላት ነው : : ከሰባት ዓመት በሇላ ግን ራሱ ቡዳው ተሻጋሪ መንፈስ ይሆናል : : መንፈሱ በሰውነትችን ውስጥ ሥፍራ የሚዘው በሶስት ባታዎች ላይ ነው : :

1. በደም ውስጥ

2. ሥጋ ላይ

3. ነፍስ ጋር

* በደም ውስጥ የሚቀመጥ የቡዳ መንፈስ በደም ውስጥ የተዋሐደው ይህ መንፈስ አንዳንድ የደም ግብሮችን የለመደና የሚጠይቅ ዶሮ : በግ ወዘተ . . . እረዱልኝ
የሚል አልፎ ተርፎም አምባ ጐር አስነስቶ በዚሁ ጸብ ሣብይም ደም ማፍሳስ ደም ሲፈስ ማየት የሚፈልግ መንፈስ ነው : : በዝህም ምክንያት የቡዳውና መንፈስ ተለውጦ
የዛሩን ጠባይ ይወርሣል ማለት ነው : :

* ሥጋ ላይ ያለ የቡዳ መንፈስ ዓይን ላይ ተቀምጦና ከዐዓን ላይ እየተነሣ ሌሎችን
ለማጥቃት የሚሰማራ መንፈስ ነው : :

* ከነፍስ ጋር የተዋሃደ የቡዳ መንፈስ በዚሀ ሄደት ክፉው መንፈስ መቶ በማቶ ከነፍሳችን ጋር ተዋሕዷል ማለት ነው : :

ይህንን ከውሰጣችን ለመለየት ብዙ ጊዜ ያየሚፈጅ ሲሆን ተከታታይ " የቅድስ ቁርባንና" የጸሎት ሥርዐት ያስፈልጋል : : ምክንያቱም ነፍሳችንና መንፈሱ አንድ
በመሆናቸው ነው : : ይህ ከነፍስ ጋር የተዋሃደ መንፈስ ሥር የሰደደ መሰረት ስለያዘ ጥቃቱ ከበድ የለ ነው : :

በዚህ ዘመን ከነፍስ ጋር በፍጥነት ለሚዋሃዲ መንፈሶች ምሳሎ የሚሆኑን የመናፍቅና የዶ/ር ራምፓና የኦሾ የሣይኮሎጂ መንፈሶች
ናቸው : :

{ የመንፈሱ የጥቃት መንገዶች }

- የራሱን የሰውየውን ነሮ የሚበላ መንፈስ
ገንዘቡን ጊዜውን በአጠቃላይ በረከቱን ሁሉ እየበላ ዕድሜ ልኩን እንደባዘነ እንደደከመና እንደባከነ እንዲኖር ያደርገዋል : :

- ዕድልን የሚበላ መንፈስ ሁልጊዜ ከጠማማ ከክፉ ከሙዋርተኛና ጠባዩን ከሚያበለሽ ሰው
ጋር የሚያገናኝ መንፈስ ነው : :

በአጠቃላይ ዕድሉ ከመጥፎ ሰው ጋር ስለሚያውለው የራሱ ጠባይ ወደ ክፉት ያዘነበለ ይሆናል : :

- እየበላ የሌሎችን ሕይወት የሚያበላሽ የቡዳ መንፈስ ከላይ የተጠቀሱት ሁለቱ የቡዳ የጥቃት መንገዶች ከአካላዊ ጤና ጋር በቀጥታ የተገናኘ ጉዳት የማያደርሱ ሲሆኑ ይህ ሶስተኛው መንፈስ ግን አካልን የሚይዝ የሚበላ ጤናን የሚያውክና አዚም የሚሆን መንፈስ ነው : :