Thursday, February 27, 2014

መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ ተሰጣቸው

ከዚህ በፊት መምህር ግርማ ወንድሙ ከ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አገልግሎት መታገድ በተያያዘ የቀድሞው የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አስተዳዳሪ መላከ ሰላም ዘላለም እሰይ ስለ መምህር ግርማ ምን ይላሉ? በሚል አገልግሎታቸው የተቋረጠበትን መልካም ያልሆነ ድርጊት እና የመምህር ግርማ ወንድሙን እውነተኛ ማንነት የሚያስረዳ ቃለምልልስ አስደምጠን ነበር:: ከታች በተያያዘው ደብዳቤ ላይ መላከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ የተሰጣቸው መሆኑን ያሳያል::
ደብዳቤው እንደሚከተለው ይነበባል
ቀን 26/12/2005
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ የወንጌል አገልግሎትና እንዲሁም የሕሙማን ሐብተ ፈውስ እንዲሰጡ ከብጹዕ ወቅዱስ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልካም ፍቃድ የተፈቀደልዎት ሲሆን ይህን አውቀው በፍቅር በሰላም እንዲያገለግሉ እናስታውቃለን::
በክርስቶስ ሰላም
ተጨማሪ መረጃ
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13144
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ማናቸው?

VDC part 26 ወጥቷል::

የቀድሞው የእገዳ ደብዳቤ

በሮም ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የተላከ ደብዳቤ 25/09/2006



Friday, February 21, 2014

ተዓምረኛው ንቡ ሚካኤል ቤተክርስቲያን


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

“የእግዚአብሔርን ሥራ በምድር ያደረገውን ታምራት እንድታዩ ኑ” መዝ. 45፡8
በንብ መንጋ የተከበበው የበሻሌ (ንቡ) ቅ/ሚካኤል፣ ቅ/እስጢፋኖስ እና ወአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ቤተክርስቲያን አመሰራረትና ገቢረ ተዓምራት አጭር መግለጫ

ቤተክርስቲያኑ ከመመስረቱ በፊት በቦታው ላይ ሲከናወኑ የነበሩ ልዩ ልዩ ታምራት፡-
1. ለብዙ ዓመታት ከተለያየ ቦታ ተጣልተው የነበሩ ምዕመናን ቦታው ላይ እየመጡ እርቀ ሰላም ሲፈጽሙበት ኖረዋል፤
2. ቤተክርስቲያኑ ከተተከለበት ቦታ ትልቅ የጽድ ዛፍ ላይ የሚወጣው ሙጫ እንደ እጣን ጢስ ሽታ ለብዙ ዓመታት አካባቢውን መዓዛው (ሽታው) ያውድ ነበር፡፡



3. በዚሁ ቦታ ላይ ሌሊት ሌሊት የመላዕክት ዝማሬ (ጣዕመ ዜማ) የከበሮ ድምጽ ይሰማ እንደነበረ በዕድሜ የገፉ የአካባቢው አዛውንቶች ተናግረዋል፡፡
4. በአካባቢው ከሚኖሩ ምዕመናን መካከል በመልካም ስራቸው የታወቁና ከ90 ዓመት በላይ ዕድሜ የነበራቸው እናት የቅዱስ ሚካኤል ታቦት (ጽላት) እንደሚተከል በተደጋጋሚ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ይናገሩ ነበር፡፡
5. ቀደም ሲል በእነ አብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት አካባቢ ጀምሮ ከተለያየ አካባቢ የሞቱ አባቶች አስከሬናቸው እየመጣ ሥርዓተ ቀብር ሲፈጸምበት የቆየ እና በተለያየ ጊዜ የቀስተ ደመና ብርሃን በመቃብሩ ላይ ይታይ እንደነበር በአካባቢው የሚኖሩ በዕድሜ የገፉ አዛውንቶች በግልጽ መስክረዋል፡፡ ዛሬም መቃብሩ በግልጽ ይታያል፡፡ ይህ ሁሉ ታሪክ ሲከናወን ከቆየ በኋላ እግዚአብሔር የፈቀደው ጊዜ ሲደርስ በአካባቢው ከሚኖሩ በዕድሜ ከገፉ አዛውንቶች መካከል በአንድ አርሶ አደር ምዕመን አማካኝነት በእግዚአብሔር ፈቃድ በተደጋጋሚ ራዕይ ተገልጾላቸው ያርሱበት የነበረውን ይዞታቸውን መሬት ለዚህ ታቦት መትከያ ቤተክርስቲያን እንዲሰራ መሬት በመስጠት አሁን በሚገኘው መቃኞ ቤተክርስቲያን ግንቦት 12 ቀን 2001 ዓ.ም ታቦቱ ሊገባ ችሏል፡፡
በቤተመቅደሱ ስለሚገኘው የንብ መንጋ አገባብ (አመጣጥ)

Saturday, January 4, 2014

Aba Sahle Mariam, a 110years old Ethiopian monk who died while he was praying in a cave.

Aba Sahle Mariam, an Ethiopian monk who died while he was praying in a cave. His body estimated to be 110years old is still intact having well recognizable features. He was kneeling down praying the moment he passed away.


Tuesday, December 31, 2013

ተአምር በ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ከርስቲያን /ሽሬ/

በሰሜን ትግራይ ክልል ከሽሬ ከተማ ወጣ ብሎ ማይ ወይኒ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ከርስቲያን ለረጅም አመታት በዓታቸውን አጽንተው የኖሩ እድሜ ጠገብና ፍጹም ጸሎተኛ የሆኑ ታላቅ አባት ነበሩ:: ባለፈው ዓመት ማለትም ኅዳር 2005 ሊቀ ትጉኃን ደረጀ ነጋሽ (ዘ ወይንዬ) በሚያዘጋጀው መንፈሳዊ ጉዞ አክሱም ጽዮን ደርሰን ስንመለስ፡ ወደዚህ ታላቅ ገዳም ለመሳለምና የእኚህን ቅዱስ አባት በረከት ለመቀበል የጉዞ ማኅበሩ በየዓመቱ እንደሚያደርገው ገብተን ነበር:: ገመና ሸፋኙ ይቅር ባይ ጌታ እኔን ደካማውን ልጁን ሳይገባኝ የዚህ በረከት ተካፋይ አደረገኝ:: ይህንን ፎቶ አሁን የለቀኩበት ዛሬ እኚህ ቅዱስ አባት በዚህ ዓመት በማረፋቸው ምክንያት ነው::
 
 
 
 
 
 
 








መምሕር ጻውሎስ መልከ ስላሴ ከተጠቀሱት አባት ጋር
ዘንድሮ የሄደው የአክሱም ተጓዥ ሁሉ እንደተለመደው ወደ ቦታው ቢሄድም እኚህን አባት በአካለ ሥጋ አላገኛቸውም ሕይወታቸውን ሙሉ ታምነውለት የኖሩለት እግዚአብሔር ዘንድ : በይባቤ መላእከት እና ዝማሬ ካህናት ታጅበው ሄደዋል:: የኖሩበት ዘመን ከሁለት መቶ ዓመታት በላይ እነደሆነ ይነገራል:: ዘንድሮ ኅዳር አቦ ለቁስቋም ዋዜማ ካህናቱ በአገልግሎት ላይ ሳሉ ያልተለመደ እንግዳ ድምጽ ሰሙ: ይኸውም ከካህናቱ ድምጽ በላይ የነምር (ነብር) ድምጽ ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ይሰማ ነበር ይላሉ ካህናቱ:: ውዲያውም ድንገት እንግዳ የሆኑ አባቶች መነኮሳት በኚህ ታላቅ አባት በአት (ቤት) ተገኙ:: እነርሱም በመንፈስ ቅዱስ ራእይ እኚህን ታላቅ አባት በክብር ገንዘው እናዲያሳርፉ ከዋልድባ የተላኩ አባቶች ነበሩ:: እነሆ ሳይገባን እኛም ልናገለግልባት የቆምንባት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ማለት ይህቺ ናት የማትመክን ዛሬም ቅዱሳንን የምትወልድ ሁሌም ተአምር የምትሰራ እነዚህን የመሳሰሉ አባቶችን ያፈራችና ወደፊትም የምታፈራ: በተቀደሱ ጸበሎችዋ የምትፈውስ፡ ተፈትና የምታሸንፍ ሁሌም በድንቅ ነገሮች የተመላችና በዙ ምስክሮች ያሏት ናት:: ተዋሕዶን ይጠብቅልን የአባታችን በረከታቸው ይደርብን በቦታው ተገኝተን ምስክርነቱን አድምጠን ለመባረክም ያብቃን:: "እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። "( ዕብ ፲፪፥፩ )
 ምንጭ
 የመምሕር ጻውሎስ መልከ ስላሴ ምስለ ገጽ (ፌስ ቡክ) የተወሰደ

ተአምራት በባሕታዊ ሳሙኤል ሶሙናዊ 

Miracles of Legedadi Saint Mary Church