Tuesday, August 19, 2014

ከእጇ ዘይት የሚፈልቅ የቅድስት ኤልሳቤጥ አስገራሚ ታሪክ

ወንድሞቼ እና እህቶቼ ይህንን ድንቅ ተአምር ስናገር እግዚአብሔር ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ እመቤታችንም ምን ያህል ክብርት እንደሆነች እያደነቅሁ ነዉ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነዉ ይህች የምትመለከቷት ቅድስት የድሮ ስሟ ሳሚያ ዮሴፍ ባሲሊዮስ ትባላለች፡፡ የቅርብ ጊዜ ቅድስት ናት ያረፈችውም 6 ወር በፊት ነዉ፡፡ ከእጇ ዘይት የሚፈልቅበት ምክንያቱ እንዲህ ነዉ፡፡ይህች ሴት በኃጥያት ትኖር ነበር(በሕይወቷ ቤተ ክርስትያን የሔደችዉ ልጇን ክርስትና ልታስነሳ ነበር) ሴት ልጇ ደግሞ ወደ ቤተክርስትያን ትሄዳለች ልጅቷ ስለእናቷ ወደ ቤተክርስትያን እንድትሔድላት ትጸልይ ነበር እናትየዋ በቀን 60 ሲጋራ ከማጨሷም በላይ ልጅቷን ልትመታት ትደርስ ነበር በቤቱ የአቡነ ሺኖዳ ስብከት ከተከፈተ ንዴቱ ይብስባት ነበር ዘፈን ከሆነ ግን ደስታውን አትችለውም፡፡ልጅቷ ግን መፀለይዋን አላቋረጠችም እንደውም ንስሐ አባቷን እያመጣች ልታስመክራት ስትሞክር ፈቃደኛ አልነበርችም፡፡ነገር ግን ንስሐ ተስፋ አልቆረጡም እንደውም በቅዳሴ ጊዜ ስሟን ጠርተዉ ስለፀለዩላት በሌላ ቀን ሲመጡ ተቀበለቻቸዉ ከመግባታቸዉ በፊት በሩ ላይ የመስቀል ምልክት አድርገዉ ነበር፡፡ከዚያ ለምን ወደ ቤተከርስትያን አትመጪም ሲሏት ቤተክርስትያን ያሉት ሰዎች ጥሩ አይደሉም ምክንያቱም ቅዱስ ቁርባን ተቀብለናል ብለዉ ግን ደግሞ ይተማማሉ አንዱ ላንዱ ጥሩ ጥሩ አይመኙም ብላ ለካህኑ ነገረቻቸዉ እርሳቸውም ልጄ ኃጥያተኛም እንዳለ ሁሉ ጻድቃንም አሉ ስለዚህ ጻድቃኖችንም ማየት ይኖርብናል ብለዉ ነገሯት ከዚያም ልጇ ከትምህርት ቤት ስትመጣ የእናቷን እና የካህኑን ውይይት ስታይ ደነገጠች ተደሰተችም ከዚያም ዓርብ ቤተክርስትያን እንድትሔድ ቃል አስገባቻት(ዓርብ ያለችበት ምክንያት ግብፅ ውስጥ ዓርብ በሙስሊሞቹ ምክንያት ሰለሚዘጋ እሁድ ደግሞ በክርስያኖቹ ምክንያት ስራ ዝግ ነዉ፡፡ቅዳሜ የስራ ቀን ነዉ፡፡

ከዚያም ዓርብ ደርሶ ቤተክርስትያ ሄዱ ቅዳሴዉ ሲጀመር እናትየዋ ማልቀስ ጀመረች ሙሉ ቅዳሴውን እስኪያልቅ ታለቅስ ነበር፡፡ካህኑ ቅዳሴውን በዓረብኛ ነበር የቀደሰዉ በኮፕት ቋንቋ ከቀደሰ ግን ቋንቋ ከቀደሰዉ ገና ከጅምሩ ላይገባት ስለሚችል ብሎ

የዘማሪ አለማየሁ ኡርጌ ምስክርነት- በፀበል ኃይል ከሞት መዳን

ዘማሪ አለማየሁ ኡርጌ ከአገልግሎት መልስ ባላወቀው ሁኔታ ከባድ ሕመም አጋጠመው::ያጋጠመው ሕመም ግን መፍትሔ እንደሌለው እና እግሩ መቆረጥ እንዳለበት ተነገረው:: በፀበል ኃይል እግዚያብሔር ያደረገለትን ድንቅ ተዓምር ከምስለ ወድምጹ ይከታተሉ::

 

ወንቅእሸት - ሙት አንሳው- ቅዱስ ገብርኤል ገዳም
ሸንኮራ ዩሐንስ ጸበል; አንጀት ካንሰር; ፍቅርተ; የእግር እብጠት

Wednesday, July 30, 2014

ድንቅ ተዓምር በሸንኮራ ቅዱስ ዩሐንስ ጸበል


የተወደዳችሁ የእግዚያብሔር ቤተሰቦች ዛሬ የምንመሰክራላችሁ ተዓምር ለወንድም አንተነሕ ኃይሌ የተደረገለት ሲሆን: ይህ ወንድም በ2005 ዓ.ም ታሞ ወደ ሕክምና ጣቢያ በመሔድ ምርመራ ያደርጋል:: ነገር ግን ውጤቱ አስደንጋጭ ብሎም ያልተጠበቀ ነበር:: የሕክምና ዶክተሩ የአንጀት ካንሰር እንዳለበት ይነግሩታል:: ይህ ብቻ አደለም ሌላ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ነገርም ነገሩት እርሱም በዚች አለም በህይወት ሊቆይ የሚችለው ቢበዛ ለ 3ወር ብቻ እንደሆነም ጭምር ያስረዱታል:: በዚህም አስደንጋጭ ዜና ተስፋ መቁረጥ ቢደርስበትም የተለያዩ ሆስፒታሎች ጋር በመሔድ የሕክምና እርዳታን ይሞክር ጀመር:: ለምሳሌ ኮርያ ሆስፒታል: ተክለሐይማኖት ሆስፒታል: ብሩክ ክሊኒክ ላንድ ማርክ እና ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከሔደባቸው የተወሱኑ የሕክምና ጣቢያዎች ሲሆኑ የተሻላ ነገርን ግን ማግኘት አልቻለም:: በስተመጨረሻ ላይ ግን ወደ እግዚያብሄር መፍትሔዎች አዳኝነት በመመለስ በሸንኮራ ዩሐንስ ጸበል በመጠጣት የእግዚያብሔር አዳኝነትን መጠባባቅ ያዘ:: በዚህ አመት ባደረገው ምርመራ በአሁኑ ግዜ በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ ሲሆን "የካንሰር ስፔሻሊስት" እና የቅዱስ ዩሐንስ ሸንኮራ ጸበል ረድተውኛል" ሲል ቃል በቃል ተናግሯል:: ከዚህ በታች በምታዩት ፎቶ ላይ ዶክመንቶቹን እያሳየ እንዳለ እናያለን::

"እግዚያብሄር በጻድቁ እንደተገለጠ እወቁ..":: መዝ 4:3