Wednesday, June 3, 2015

ታላቅ ተዓምራት- የፈለገ ሕይወት መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፣ወቅድስት ሃና ወቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፲ የሚገኘው የፈለገ ሕይወት መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፣ወቅድስት ሃና ወቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ሰሞኑን ታላቅ ተዓምራትን እያሳየ ነው። ሰዎች ይዘባበታሉ እግዚአብሔር ግን ሥራውን እየሰራ ነው፣ ሰዎች ልብ እንበል "በዚያን ጊዜ ብዙዎች መንገዶቻቸውን ይስታሉ" እንደተባለው ዘወትር በአጠገባችን ከከበበን ጠላት ዲያብሎስ ርቀን የቃሉን ድምጽ ሰምተን ወደ እርሱ ብንጠጋ እንባረካለን። ረደኤተ እግዚአብሔር አይለየን አሜን

ደብረ እያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ? 

ኢትዮጵያውያንና የያዕቆብ የመጨረሻ ልጅ የቢኒዖን (ብንያም)ነገድ

የፈለገ ሕይወት መጥምቁ ዮሐንስ ወቅድስት ሃና ወቅዱስ ዑራኤል ገቢረ ተዓምራት -save waldiba


 

Tuesday, June 2, 2015

ድንቅ ታምር ጃማ ማርያም

ዳግማዊት ጎለጎታ ድንጋይ ገጠም ጃማ ማርያም ቤተ ክርስቲያኗ የተመሰረተችው በ17ተኛው ክ/ዘ በልጅ እያሱ ዘመነ መንግስት እንደተሰራች የሚነገርላት ጃማ ማርያም ዳግማዊት ጎለጎታ እንድትባል ያስቻላት ከዕየሩሳለም ጎለጎታ ቀጥላ ሁለተኛዋ በመሆኗ እና ድንቅና ታምራዊዋ ጸበል ከፈለቀበት ከ1965 ዓ/ም ጀምሮ ደንቅ ታምር እየሰራ የገኛል ለምሳሌ :-\አይነ ስውራንን ፥መንፈስ የተጠናወታቸውን ፥አካላቸው ሽባ የሆነውን ፥አፋቸው የማይናገረውን፥የዘመኑ በሽታ(HIv)ን ጨምሮ እና ሌሎችንም በርካታ በሽታወችን የምፈውሰው ከድንጋይንና ከተራራ ላይ የሚፈልቀው ጸበል ድንቅ ታምር እየሰራ ስለመሆኑ ታምሩ ይመሰክራል በመሆኑም ግንቦት 21/2007ዓ/ም የንግስናዋ እለት ከ2000 በላይ ምዕመናን ለበዓሏ ታድሟል ውድ ጓደኞቸ ሼርና ላይክ በማድረግ ከዚህ ታምር ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ በእግዚዓብሄር ስም አሳሰብኋችሁ የእግዚዓብሄር እና የቅድስት ድንግል ማርያም በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን፡፡







Monday, June 1, 2015

ፓሊካርፕ (ከ69-155ዓ/ም) የተጋድሎ ሜዳው ምስክር


ትርጉም ዘላለም ቸርነት
ጌታ ኢየሱስ እንዲህ አለ፡- ‹‹ቤተክርስቲያኔን በዚህች ዐለት ላይ እሠራለሁ፤የገሃነም ልጆችም አይቋቋሟትም›› ማቴ. 16÷18
እናም በአስገራሚ ክብርና ኃይል ቤተክርስቲያኑን መሠረተ፡፡ ክርስቶስ ከመቃቭር ተነሣ ሞተ ይይዘው ዘንድ አልቻለምና፡፡ ሕያውነቱንም በግልጥ አሳየ፤ በሃምሳኛውም ቀን መንፈሱን በእሳት ልሳን መልክ ላከው፡፡ ይህም ፈሪዎችና ግራ የገባቸውን ደቀ መዛሙርት ቆራጥና ጀግና የመስቀል አርበኞች አደርጋቸው፡፡ እነርሱም በሽተኞች ፈውሱ ሙታንን አስነሱ፤ በግልጥነትም ወንጌልን ስበኩ በአገልግሎታቸውም በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ፈለሱ፡፡ የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ደቀመዛሙርትን ገርፈው ዳግመኛ ስለ ክርስቶስ እንዳይናገሩ ቢያስጠነቅቋቸውም ምላሻቸው ግን ‹‹ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባናል፤ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ዝም አንልም የሚል ሆነ፡፡


መከተል የሞት ፍርድ የሚያስከትል ወንጀል ሆኖ እንዲቆጠር አዋጅን አወጡ፡፡ በአገሪቱ በሚከሰተውም አደጋና ጥፋት
ክርስቲያኖችን ተጠያቂ ማድረግ ጀመሩ፡፡ አንድ የጥንት ክርስቲያንእንደተናገረው የጎርፍ መጥለቅለቅ ከመጣ ድርቅና ርሃብ ከሆነ ወይም መቅሰፍት ከወረደ እነዚህ አረማውያን እንዲህ ሲሉ ይጮሃሉ ‹‹ክርስቲያኖቹን ለአንበሳ እንወርውራቸው!›› በዚህ ዘመን በክርስቲያኖች የማምለኪያ ቤቶች ውስጥ ዓይነት የአማልክት ምሥል ስለሌለ አረማውያን ክርስቲያኖችን በአማልክት ሕውና እንደማያምኑ ተረድተዋል፡፡ ስለዚህም ክርስቲያኖችን የሚተሯቸው ‹‹አምላክ የለሾች›› ብለው ነበርለለ ነገሩ ገን የተገላቢጦሽ ነበር 2ኛ ዮሐ.9 በየሐንስ ራእይ ላይም በስደቱ ዘመን ለነበረችው የሰምርኔስ ቤተክርስቲያን (ፖሊካርፕ የነበረባት) ጌታችን በዮሐንስ
አማካኝነት በላከው ምልእክት በውሸተኞች የሚደርስባቸውን ስድብ እንደሚያውቅላቸው ተናግሯል፤ ራእ 2÷9 ሮማውያን ብዙዎችን የመጀመሪያ የጌታ ደቀመዛሙርት ለሞት አሳልፈው ሰጥተዋቸዋል፡፡ የጳውሎስን አንገት ሲቆርጡ ጰየጥሮስን ሰቅለውታል፡፡ ለሌቹንም በእሳት አቃጥሏቸው፤ በሰይፍ ገደሏቸው ለአውሬ ጣሏቸው፡፡‹‹ዓለም እናንተን ቢጠላችሁ በቅድሚያ እኔን እንደጠላ አስተውሉ እኔን አሳደው ከሆነ እናንተንም ያሳድዷችኋል›› የሚለው የእየሱስ ቃል በጆሮዋቸው እየደወለ ነፍሳቸውን ሰጡ፡፡

የክርስቲያኖች በቁጥር ማደግ ብሎም ለጣዖቶቻቸው አንሰግድም ማለታቸው የሮም ገዢዎችን በፍርሃት ላይ ስለጣላቸው ክርስቶስን የጥንት ቤተክርስቲያን ታሪክ እደሚነግረን የጌታ ሰማዕታት ሕይወታቸውን በወንጌል ምክንያት ለሞት አሳልፈው ሲሰጡ በድንጋጤና በመርበትበት ሳይሆን ፊታቸው ከተስፋቸው በተገኘ ብርሃን ፈክቶና ጉዳዮቻቸው አማውያንን ግራ በሚያጋባ የደስታ ዝማሬ ታጅበው ነበር፡፡ እንዲህ እየዘመሩ ነበር የሚሞቱት ‹‹ለወደደን ከኃጢያታችንም በደሙ ላጠበም ለአባቱም መንግሥት ካህናት እንደንንሆን ላደረገን ለእርሱ ክብር ይሁን!›› በዚያ በከፋ የስደት ወቅት ቤተክርስቲያን በሮም ግዛት ውስጥ እያደገች እየጠነከረች እየበዛችና እየሰፋች ሄደች፡፡ ከዚህም በኋላ በሐዋርያትና በደቀመዛሙርት እግር የሚተካ አዲስ ትውልድ ብቅ አለ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ፖሊካርፕ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው፡፡ ፓሊካርፕ በወጣትነቱ በሐዋርያው ዮሐንስ እግር ሥር ሆኖ
የተማረ ነበር፡፡ ብዙ ሰዎችንም ወደ ዘላለም ሕይወት መርቷል፡፡

የሰምርኔሱ ጳጳስ ፖሊካርፕ በእምነቱ ምክንያት በርካታ የመከራና የእስር ዓመታትን አሳልፏል፡፡በከሎስየም የትርኢት ሜዳ(Arena) መሃል አንድ ወጣት ቆሟል፤ አንድ አንበሳም በወጣቱ ዙሪያ ይንጎራደዳል፡፡ የተሰበሰበው ሕዝብ ምንም ዓይነት ድምጽ ሳያሰማ የሚሆነውን ይከታተላል፡፡ ከንጉሳዊ ዙፋን በፈገግታ ይመለከተዋል፡፡ በዚህ በሰርምኔስ ግዛት ማንኛውም ክርስቲያን እምነቱን ካልካደ ይህ ወጣት በዚህ የትርኢት ሜዳ አንበሳ ፊት የቆመው፤ ‹‹ወደዚህ ና›› አለ ገዢው በወጣቱ ላይ እየጮኸ

‹‹አንተ ወጣት ነህ፤ ገናም ረጅም የሕይወት ዘመን ይጠብቅሃል አሁንም አልዘገየህም አንዳንዶቹ ጓደኞችህ በቄሳር ምለዋል፡፡
አንተም በቄሳር ብትምል አንበሶቹን አርቅልሃለሁ እናም በቄሳር ማልና በሕይወት ኑር›› አለውው፡ ወጣቱ ግን ራሱን በአሉታ በመነቅነቅ ወደ አንበሳው ተጠጋ፡፡ አንበሳው ቀጥ ብሎ ከቆመ በኋላ ወደ ወጣቱ ተስፈንጥሮ ዘለለ፡፡ ለቅትበት ከታገሉ በኋላ አንበሳው ወጣቱን በጠንካራ ጥርሶቹ ዘነጠለው፡፡ የተሰበሰበውም ሕዝብ በደስታ እያጨበጨበ ‹‹ሞተ ለአማልክት የለሾች ሲል ጮኸ፡፡ ከገዢዎቹ አንዱ እንዲህ አለ ‹‹ይሄ ወጣት ተራ አማኝ ነበር፡- ሌላውም ቀጠለና ‹‹ፓሊካርፕን እንፈልጋለን መሪያቸውን፡፤ ሞተ ለአማክት የለሾች! ሞት ለፖሊካርፕ!›› ሲል በትርኢት ሜዳው የተሰበሰበው ሕዝብ ሁሉ በአንድ ድምጽ‹‹ሞተ ለአማልክት የለሾች !ሞት ለፖሊካርፕ! ሲል በትርኢት ሜዳው የተሰበሰበው ሕዝብ ሁሉ ሁሉ በአንድ ድምጽ ‹‹ሞተ ለአማልክት የለሾች! ሞተ ለፖሊካርፕ!›. አለ መጮሕ ጀመረ፡፡ በዚህ ጊዜ ፖሊካርፕ በወታደሮች ተይዞ እንዲመጣ ትእዛዝ ተሰጠ፡፡ ወታደሮችተይዞ እንዲመጣ ትእዛዝ ተሰጠ፡፡ ወታደሮቹ ፖሊካርፕን ባገኙት ጊዜ በትርኢቱ ሜዳ ወደ ተሰበሰበው ሕዝብና ወደ ሮማው ገዢ ለመውሰድ አጣደፉት፡፡ በወታደሮች ታጅቦ የክርስቲያኖች መሪ የተባለው ፖሊካርፕ እንደመጣ ደም የጠጠማው አረማዊ ሁሉ በአነድ ድምጽ ‹‹ሞተ ለፖሊካርፕ!›› ሲሉ ጮኹ፡፡ የወይን ጠጅ ቀለም ያለው መቀነት ታጥቆ ወርቃማ ልብስ የለበሰው የሮማው ገዢ ከዙፋኑ ተነስቶ በሰገነቱ ለይ ቆመ፡፡ በአቧራ የቆሸሸውን ፖሊካርፕን በትክታ ፈገግ ብሎ ተመለከተው፡፤ እጁንም አወዛውዞ የሕዝቡን ጩኸት ዝም አወሰኘና፤

‹‹አንተ የክርስቲያኖች አስተማሪ ፖሊካርፕ ነህ?››
‹‹አዎን እኔ ነኝ›› መለሰ ፖሊካርፕ፡፡
‹‹በዚህ በሽምግልና ክብርህን የምትጠብቅ ይመስለኛል›› ቀጠለ ገዢው፡-‹‹በቄሳር ስም ማልና ራስህን አድን በተጨማሪም ወደ እነዚህ እስረኛ ክርስቲያኖች ፊትህን መልስና ጣትህን በመጠቆም፡- እናንተ አምላክ የለሾች ጥፉ! ብለህ አውጅ›› አለው፡፡ፖሊካርፕ ግን በተቃራኒው ፊቱን ወደ ትርኢቱ ተመልካች ሕዝብ አድርጎ ጣቱንም በእርሱ ላይ በመቀሰር ‹፣እናንተ አምላክ የለሾች ራቁ›› ሲል ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አንሥቶ ጮኸ፡፡ በዚህ ጊዜ ሕዝቡ ጥርሱን አፋጨበት፡፡ ‹‹ዕንዴት ቢደፈፍርን ነው አምላክ የለሾች የሚለን?›› ሲሉም ብንዴት ተንቀጠቀጡ፡፡ ገዢው ግን አሁንም ፖሊካርጵን ሊያጠምደው ፈለገና ‹‹በቄሳር ማል በሰላም እለቅሃለሁ፤ እናም ክርስቶስ ካደ›. አለው፡፡ ፓሊካርፕ ግን ቀጥ- ብሎ እንደቆመ፡- ‹‹ለ86 ዓመታት ያህል የእርሱ አገልጋይ ነበርሁ፤ በእነዚህም ዓመታት አንድም ቀን አስከፍቶኝ አያውቅም፤ ታዲያ ያዳነኝን ንጉሤን መካድና መስደብ እንዴት ይሆንልኛል?›› ሲል ተናገረ፡፡
‹‹በቄሳር ማል፤ ገዢው በንዴት ጦፎ ጮኸ
‹‹በቄሳር እንድምል እንዲያው በከንቱ አትልፋ በግልጽ
እንድትሰማኝ እፈልጋለሁ እን ክርስቲያን ነኝ››
‹‹ አዚህ አደገኛ አውሬዎች አሉ›› ገዢው ማስፈራራቱን ቀጠለ
‹‹ሃሳብህን የማትለውጥ ከሆነ ለእርሱ ወርሬ እሰጥሃለሁ››
‹‹አምጣቸው!›› ፓሊካርፕ በጽናት መለሰ፡፡
‹‹አውሬዎቹን የማትፈራ ከሆነ በሕይወት ሳለህ በእሳት
አቃጥልሃለሁ›.
‹‹ጥቂት ጊዜ ነድዶ በሚጠፋ እሳት ልታስፈራራኝ አትሞክር›› አለ
ፖሊካርፕ ነገር ግን እግዚአብሔርን ለማያውቁ የተዘጋቸውን
ዘላለማዊ ገሃነመ እሳት ዘንግተሃል ለምን ትዘገያለህ? ፊትህ ናና የወደድኸውን አድረርግ›› ከሕዝቡ መሃል አንድ ሰው እንዲህ ሲል በድንግት ጮኸ ‹‹ይሄ የክርስቲያኖች አባት የሚባለው ነው ፤ ብዙዎችንም ለአማልክቶቻችን እንዳይሰግዱ ያስተማረ ነው፤ አቃጥሉት ወታደሮቹ በዚህ ጊዜ ፖሊካርፕን ከምሰሶ ጋር ሊያስሩት መጡ፡፡ፖሊካርፕም ‹‹በእሳቱ ነበልባል ፊት እንድጸና የሚያጠነክረኝ እርሱ በመንደጃው ምሶሶ ላይ ሳልታሰር ጸንቼ እንድቆም ያበረታኛል.›› አለ፡፡ ከሥሩም እንጨትና ጭራሮ ሰብስበው ዘይት በማፍሰስ እሳት ለኮሱበት፡፡ በእሳቱ ነበልባል ውስጥ የጶሊካርፕ ጸሎት ከፍ ባለ ድምጽ ይሰማል፤ እንዲህ ሲል፡- ታላቅ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ አንተ የተወደደው ልጅህ የኢየሱስ ክርስቶስ አባት ነህና በእርሱም አንተን እናውቅህ ዘንድ ተሰጥቶናልና ተመስገን፡፡ ስለዚህች ቀንና ሰዓት እባርክሃለሁ ምክኒያቱም ከሰማዕታት አንደ አንዱ ሰለተቆጠርሁኝ አንተ እውነተኛ እና ታማኝ አምላክ ነህ፡፡ ላንተ ከአሁን እስከ ዘላለም ድረስ ክብር ይሁንልህ አሜን!›. የእሳቱ ወላፈን እና ብርታት ወደ ላይ እየተንቀለቀለ ይታያል፤ ነገር ግን በዚያው ቅጽበት ፖሊካርፕ በሞት ፊት የነበረው ድፍረትና ጥንካሬ በስደት ላይ ለነበሩት ክርስቲያኖች ክርስቶስን በታመን እንዲኖሩና እንዲጸኑ ተጨማሪ ብርታትን ይሰጣቸው ነበር፡፡
ቤሪያ ጋዜጣ
ቁጥር 1 1996

Monday, May 25, 2015

ሸጎሌ [ሚዳቋ] ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አህዱ አምላክ አሜን!
(ሸጎሌ [ሚዳቋ] ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን፤ አድራሻ አዲስ አበባ፤ ከአዲሱ ገበያ -» ጽዮን ሆቴል -»ሽጎሌ ኪዳነምሕረት/ድልበር -»15 ደቂቃ )
" የፃድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል"
መዝ 111:6
የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም ያስራት ያደራ ልጆች የፃድቃን ሰማእታት ባለሟሎች በወደደን እንስከሞት ድረስ ባፈቀረን በ አንድያ ልጁ በእየሱስ ክርስቶስ ፍፁም ፍቅር በሆነ ሰላምታ እንደምን ቆያችሁ
ምስጋና የባህሪውን የሆነ ያባቶቻችን አምላክ ዛሬ በእኛ አንደበት ነገም በፍጥረታት ሁሉ የተመሰገነ የከበረ ይሁን። የ ሀዲስ ኪዳን ኪሩብ እናትና ድንግልናን አስተባብራ የያዘች ቤዛይት አለም የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም ልመናና ፅሎቷ አይለያችሁ አሜን አሜን አሜን።

እኔ በስፍራው በነበርኩበት 2006 አመት ምህረት ላይ ድንቅ ተአምር በእኔና በሎሎች ምእመናን ላይ ሲደረግ አይቻለው የተደረገላቸው ምስክርነት ሲሰጡ ሰምቻለው አጋንንት ሲቃጠሉ ከተለያየ ሀገር የመጡ ሰዋች ከሆዳቸው የተለያየ ነገር ሲወጣ የእግዚአብሔርን ድንቅ ተአምር ሲገለጥ ማየት የተለመደበት ሰፍራ ነው የ ሰማእቷን ተአምረኛ እምነት ተቀብተው ከነበረባቸው ደዌ ሲፈቱ እንዲሁም በህይወታቸው የተለያየ ጥያቄ እና አስቸጋሪ ፈተና የገጠማቸው ደጇ መተው አርምሞ /ብቻቸውን እየፆሙ እየሰገዱ እየፅለዩ እና በቀን 1 ጊዜ ብቻ እየበሉ/ መልሳቸው ተመልሶላቸው ጭንቀታቸውን በደስታ ተቀይሮላቸው ሲሄዱ ተመልክቻለው ።

እናም የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እግዚአብሔር ለምህረት በተለያየ መንገድ ይጠራናል እናም ሄደን ንስሀ ገብተን ፅበሏን ጠጥተን እምነቷን ተቀብተን ከነበረብን ደዌ ተፈተን የአለም ጭንቀታችንን እረስተን የሰማእቷን በረከት እንድትካፈሉ በልኡል እግዚአብሔር ስም እጠይቃለው። በሰው አገር ያላችሁ እንደኔ ቤተሰቦቻችሁን ልካችሁ እምነት ፅበል አስመጥታችሁ ተጠቀሙ
የሰማእቷ በረከት አሁንም እኔ ባለውበት እምነቷ ለብዙ ጓደኞቼ ፍትሁን መድሀኒት እየሆነ ተአምር እየሰራነው። እንዲሁም ቦታው ከተመሰረተ ብዙ የቆየ ባይሆንም የልማት ስራው ግን እንደምታዩት በ መሳርያና በ ገንዘብ እጦት ቆሟል እናም ይህን የበረከት ስፍራ መንከባከብና እና ማገዝ ስላለብን ሁላችንም እንድንሳተፍ በልኡል እግዚአብሔር ስም እጠይቃለው።

ዛሬ እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ አንድ ድንቅ ተአምረኛ የፅበል ስፍራ ብዙ ያልተጠቀምንበት የሰማእቷ የቅድስት አርሴማ....የ ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ...የመጥምቁ ዬሐንስ.....እንዲሁም የእመቤታችን የቅድስት ኪዳነምህረት....ፅበሎች በአንድነት የሚገኙበት ለአጋንንት ምድራዊ ሲኦል የሆነ ድንቅና ተአምረኛ ሰፍራ ነው።

በፅበሉ ሰፍራ የምትገኝ ሚዳቆ ከፅበሉ ቦታ የማትጠፋው                           የፀበሉ መሄጃ መንገድ እጅግ ተአምረኛ ስፍራ















አድራሻ
አዲስ አበባ የ ጉጃም በር በመባል የሚታወቀው ሱሉልታ መንገድ
 
ላይ አዲሱ ገበያ{ፁዬን ሆቴል } ከዛ በታክሲ በመያዝ አዲስ የተሰራ ያለው መለስ ፓርክ በሩላይ ወይም ባለታክሲውን አርሴማ ፅበል በሩላይ አውርደኝ ብትሉት በሩ ላይ ይጥላችሀል።

ለበለጠ መረጃ በቦታ የሚገኙት የሚያገለግሉ ካህን አባ ኪደነ ማርያም +251920225390 በቫይበር ማግኝት ትችላላችሁ

"እግዚአብሔር ፃድቃንን ይወዳል እግዚአብሔር ስደተኞችን ይጠብቃል"  መዝ.145፤6