Tuesday, November 4, 2014

ተዓምረኛው በሻሌ ንቡ ቅ/ሚካኤል እና ሰማዕቱ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
“የእግዚአብሔርን ሥራ በምድር ያደረገውን ታምራት እንድታዩ ኑ” መዝ. 45፡8
በንብ መንጋ የተከበበው የበሻሌ (ንቡ) ቅ/ሚካኤል፣ ቅ/እስጢፋኖስ እና ወአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ቤተክርስቲያን አመሰራረትና ገቢረ ተዓምራት አጭር መግለጫ
ቤተክርስቲያኑ ከመመስረቱ በፊት በቦታው ላይ ሲከናወኑ የነበሩ ልዩ ልዩ ታምራት፡-
1. ለብዙ ዓመታት ከተለያየ ቦታ ተጣልተው የነበሩ ምዕመናን ቦታው ላይ እየመጡ እርቀ ሰላም ሲፈጽሙበት ኖረዋል፤
2. ቤተክርስቲያኑ ከተተከለበት ቦታ ትልቅ የጽድ ዛፍ ላይ የሚወጣው ሙጫ እንደ እጣን ጢስ ሽታ ለብዙ ዓመታት አካባቢውን መዓዛው (ሽታው) ያውድ ነበር፡፡
3. በዚሁ ቦታ ላይ ሌሊት ሌሊት የመላዕክት ዝማሬ (ጣዕመ ዜማ) የከበሮ ድምጽ ይሰማ እንደነበረ በዕድሜ የገፉ የአካባቢው አዛውንቶች ተናግረዋል፡፡
4. በአካባቢው ከሚኖሩ ምዕመናን መካከል በመልካም ስራቸው የታወቁና ከ90 ዓመት በላይ ዕድሜ የነበራቸው እናት የቅዱስ ሚካኤል ታቦት (ጽላት) እንደሚተከል በተደጋጋሚ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ይናገሩ ነበር፡፡
5. ቀደም ሲል በእነ አብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት አካባቢ ጀምሮ ከተለያየ አካባቢ የሞቱ አባቶች አስከሬናቸው እየመጣ
በቤተመቅደሱ ስለሚገኘው የንብ መንጋ አገባብ (አመጣጥ)
እግዚአብሔር አስቀድሞ ቦታውን ስለመረጠው፡-
1. ሕዳር 12 ቀን 2002 ዓ.ም የቅዱስ ሚካኤል በዓል ሲከበር በዋዜማው ሊቃውንቱ በአገልግሎት ላይ እንዳሉ ማለትም ሕዳር 11 ቀን 2002 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ገደማ ከምስራቅ አቅጣጫ የንብ መንጋ መጥቶ የቃል ኪዳኑ ታቦት በሚገኝበት በመንበሩ ውስጥ ገብቶ ካደረ በኋላ በነጋታው ታቦቱ ወጥቶ በሚከበረበት ጊዜ ንቡ ከመንበሩ ወጥቶ እንደ ደመና ረቦ ካሉት ምዕመናን ጋር ታቦቱን ዙሮ አክብሯል፡፡ በዕለቱም ይህን አስደናቂ ታምር ያዩና የተመለከቱ ምዕመናንም በከፍተኛ ድምጽ እግዚአብሔርን አመስግነዋል፡፡
2. ሕዳር 11 ቀን 2004 ዓ.ም የድንግል ማርያም ዕለት ካህናቱ ቅዳሴ ገብተው በሚቀድሱበት ጊዜ ቅዱስ ወንጌል ሲነበብ የንብ መንጋ መጥቶ ከቤተክርስቲያኑ ጉልላት ላይ የመስቀል ምልክት ሰርቶ ከሰፈረ በኋላ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ ተነስቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ወደ ቤተልሔም ውስጥ ገብቶ እስከአሁን ድረስ ሰፍሮ ይገኛል፡፡
3. ታህሳስ 9 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት የንብ መንጋ መጥቶ ከቤተክርስቲያኑ ጎን ላይ ከሰፈረ በኋላ ከቀኑ 11፡30 ተነስቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ወደ ግብር ቤት ገብቶ እስከአሁን ድረስ ሰፍሮ ይገኛል፡፡

Saturday, October 25, 2014

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምና የአርባ ሓራ መድኃኒዓለም ተዐምር

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምና የአርባ ሓራ መድኃኒዓለም ተዐምር
   ከጌታቸው ገብሬ እንግዳ
       አንድ አምላክ በሚሆን በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም በቅድሚያ መንፈሳዊ ሰላምታዬን አቀርባለሁ። ኗሪነቴ በዋሽንግተን ዲሲ ከእመቤታችን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አጠገብ ነው። ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነኝ።ጥቅምት 18 ቀን 2005 .. እምሽቱ ላይ በሥራ ገበታ ላይ እያለሁ ራሴንና መላ ሰውነቴን ስላመመኝ አለቃዬን አስፈቅጄ ወደ ቤቴ ሄድኩ። ቤቴም እንደደረስኩ የቤቴን በር ለመክፈት ስታገል ስልክ ተደወለልኝ። ከዚህ በኋላ የሆነውን ብዙውን ስለማላስታውስ በባለቤቴ በወ/ ታሪክ አንደበት የተተረከውን ላቅርብላችሁ።

        ባለፈው ጥቅምት ወር የቅዱስ ገብርኤል ዋዜማ ዕለት ከምሽቱ አምስት ሰዓት ላይ ባለቤቴ ከሥራ ከሚመጣበት ከተለመደው ሰዓት አንድ ሰዓት ቀደም ብሎ በራችንን ለመክፈት የሚታገል ሰው እንዳለ ስለሰማን እኔና ልጆቼ የምናደርገው ቢቸግረን ለባለቤቴ ስልክ ደወልንለት። ስልኩንም እንደደወልን እቤታችን በር ላይ የባቤቴ ስልክ ሲያቃጭል ሰማን። በዚህም በሩን ለመክፈት የሚታገለው ባለቤቴ እንደሆነ አወቅን። ወዲያውም እኔና ልጆቼ ተሯሩጠን ሄደን በሩን ስንከፍት ባለቤቴ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደ ራሱን ችሎ መቆም አቅቶት አየነው። ግራ ተጋብተን ምን እንደሆነ እንኳ ሳንጠይቀው ዝም ብለን ደግፈነው ወደ ቤት አስገባነው። ኃይለኛ ራስ ምታት እንዳለበት ሲነግረን ይሻለዋል ብለን የራስ ምታት መድኃኒት ሰጥተን አስተኛነው። በማግስቱም የቅዱስ ገብርኤል ዕለት በዋሽንግተን ኃይለኛ አውሎ ነፋስ ይነፍሳል ተብሎ ስጋት ስለነበር /ቤት ሁሉ ዝግ እንደሚሆን በመገናኛ ብዙኃን ተነግሮ ነበር። እኔም አጋጣሚውን በመጠቀም ቤተሰቡ በሙሉ ቁርስ አብረን እንድንበላ ልጆቼን ቀሰቀስሁና አባታቸውን አስነስተው ወደ ገበታው እንዲቀርቡ ነገርኳቸው። ባለቤቴ ከመኝታው ተነስቶ ከተጣጠበ በኋላ ወደ ገበታው ለመቅረብ ሲመጣ መራመድ አልቻለም። ዝልፍልፍ አለ። ሁላችንም ተደናገጥን። ልጆቼም ስልክ ደውለው አምቡላንስ ጠሩ። ባለቤቴም በአስቸኳይ ለሕክምና ወደ ዋሺንግተን ሆስፒታል ማዕከል ተወሰደ። እዚያም እንደደረሰ ሐኪሞቹ በሚያውቁት መንገድ ሁሉ መርምረው ምንም ሕመም ሊያገኙ አልቻሉም። ሊነጋጋ ሲል ጧት ላይ ለሕመሙ ማስታገሻ ብለው መርፌ ሲወጉት አንቀጠቀጠውና ደካከመው። መተንፈስ አቃተው፣ አንደበቱም ተያዘ።እንደሞተ ሁሉ ሰውነቱ ቀዘቀዘ በዚህን ጊዜ በመሳሪያ ኃይል እንዲተነፍስና ደሙም እንዲጣራ አደረጉ። ሆዱን ከፍተው ለማየት ቢሞክሩ ሰውነቱ ከፍሎሪዳ እንደመጣ ገና ከማቀዝቀዣ እንደወጣ ሥጋ ድርቅ ብሎ ስለት የማይደፍረው ሆነ። ሐኪሞቹ የሚያደርጉት መላው ጠፋቸው። አንድ ጊዜ ሳንባው ተቃጥሏል፣ ትንሽ ቆይተው ጉበቱ ተበላሽቷል፣ ከዚያም ኩላሊቱ አይሠራም ሲሉ ጥቂት ቀናት አለፉ።



አንድ ቀን ከሐኪሞቹ አንደኛውበኛ በኩል ምንም ልንረዳው የምንችለው የለም፤ ወደ ማገገሚያ ቤት ሄዶ በእዚያ ቢቆይ ነው የሚሻለው፤ ስለዚህ ወደዚያ እንድንልከው ፈርሚ አሉኝ።እኔምአልፈርምም፤ በእናንተ በኩል ምንም ዕርዳታ ማግኘት ካልቻለ እዚያስ ሄዶ ምን ያደርጋል? ለመሞት ለመሞት እዚሁ ሆኖ ቢሞት ይሻላል አልኳቸው። ይህንን የሰሙ ወዳጆቻችን በጣም አዘኑ። አንዳንዶቹ ለሚቀርቡት ታቦት ተሳሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ ኢትዮጵያ ለሚገኙ ለበቁ አባቶች በፀሎታቸው እንዲራዱ በስልክ አሳሰቡ። የሚጨነቁልን የሚያውቁን ብቻ ሳይሆኑ ባጋጣሚ ሁኔታውን የሰሙ የማያውቁንም ነበሩ። አንድ ቀን ባለቤቴ ከተኛበት ክፍል ውጭ በእንግዶች ማረፊያ ቤት ተቀምጨ እያለሁ አንዲት እናት ጋር እየተጨዋወትን እያለን ስለባለቤቴ ጭንቀቴን ስነግራቸው አንዲት የጸሎት መጽሐፍ (የሰኔ ጎልጎታ የእመቤታችን ፀሎት መጽሐፍ በክታብ መልክ የተዘጋጀች) ከቦርሳቸው አወጡናእንቺ በዚህ አሻሺው፤ እመቤታችን ታድነዋለችአሉኝ። እኔም ተቀበልኳቸውና ባለቤቴ ወደተኛበት ክፍል ገብቼ (በገባሁ ቁጥር እየፈረምኩ ነው። ቁጥጥሩ ጥብቅ ነው። ዝም ብሎ እንደፈለጉ መግባት መውጣት የለም።) ሴትየዋ እንደነገሩኝ ባለቤቴን ላሻሸው ብዬ መጽሐፏን ገና ግንባሩ ላይ ሳስነካ የመተንፈሻውና ደም የማጣሪያው መሣሪያ ሁሉ ይንጫጫ ጀመር። እኔ ወደ ማሽኑ አልደረስኩም። ማሽኑ ጋር የተያያዘ ገመድ አልነካሁም። ግን ማሽኑ ያለማቋረጥ እሪታውን ቀጠለ። ሕብረ-ቀለማት እያወጣ ተብለጨለጨ። ሐኪሞቹና ነርሶቹ እየተሯሯጡ መጡናማሽኑን ለምን ነካሽ?” ብለው ተቆጡኝ። እኔም የሆነውን ነገርኳቸው። እነሱም የጸሎት መጽሐፏን እንዳሳያቸው ጠየቁኝና ሰጠኋቸው። አገላብጠው አዩና ሳቁብኝ። ውሸት የነገርኳቸው መስሏቸዋል።እመቤቴ ሆይ አታሳፍሪኝ፤ ኃይልሽን ግለጪላቸውብዬ እነሱም እንዲሞክሩት መጽሐፏን ሰጠኋቸው። እነሱም የጸሎት መጽሐፏን ወደግንባሩ ሲያስጠጓት ማሽኑ ተንጫጫ። እነሱም ተደናገጡ። በሁኔታው ግራ ተጋቡ። ከአቅማቸው በላይ የሆነ የማይመረመር ኃይል አጋጠማቸው። አንደኛውም ሐኪምበኛ በኩል ምንም ልንረዳው እንደማንችል ገልጸንልሻል። ትልቅ እምነት አላችሁ። በእምነታችሁ ተስፋ የምታገኙ ከመሰላችሁ እሱን ሞክሩ። የሚጸልይላችሁ ከሌለ እኛ እናመጣላችኋለንአለኝ።የሚፈቀድልን ከሆነማ የራሳችንን ቄሶች አስመጥተን እናጸልያለን አልኩት። በልቤሌላማ ከእምነቴ ውጭ የሆነ መጥቶ አይዘባርቅብኝምአልኩ። ይህንን የእመቤታችንን ተዐምር የሰሙ ሰዎች ወደ ሆስፒታሉ መጉረፍ ጀመሩ። ከላይ እንዳልኩት ጸሎቱ በያለበት ተጠናከረ። ከኡራኤልም የሚጸልዩልን ቄስ መጡ። እሳቸው የመጡ ዕለት።ማሽኑ መሥራት አቁሟል፤ ሕመምተኛው አርፏል፤ ከዚህ በላይ የምንነግራችሁ የለም። አስከሬኑን እስከምናስረክባችሁ እኛን ምንም ነገር ልታነጋግሩን አትችሉምብለውን እየተላቀስን ነበር። በመላቀስ ላይ እያለን ቄሱ ለቅሷችንን አስቆሙንና የሚያጽናናንን የእግዚአብሔር ቃል ተናገሩ። እሳቸውምአትዘኑ፣ ለእግዚአብሔር የሚሳነውነገር የለም። አልአዛርን በሞተ በአራተኛው ቀን ያስነሳ አምላክ ወንድማችንንም ሊያስነሳ ይችላል። ባይነሳም እንኳ ማዘን አይገባም። ክርስቲያን ሞተ አይባልም። ያውም ዘር የተካ፣ ማስታወሻ ትቶ የሄደ ወንድም ሞተ አይባልም።እያሉ ሲናገሩ አንደኛዋ አስታማሚ መጣችናእስቲ ተረጋጉ፣ መሣሪያው መስራት ጀምሯል። ሕመምተኛውም ትንፋሹ ተመልሷል። አታልቅሱ እስቲ መጨረሻውን ጠብቁአለችን። ቄሱምእግሬን ለምለም ያድርገው፤ እግዚአብሔር ፍጻሜውን ያሳምረውብለው ሄዱ።  


ከዚያ በፊት አንድ ቀን ቀደም ብሎ አንዲት ጓደኛዬ (ከኔ ጋር አብራ ስትጨነቅ፣ እኔን ታበረታታ የነበረች) “ዛሬ ትልቅ ሕልም አየሁ።እግዚአብሔር ጠባቂ መልአኬን እልክለታለሁ፤ አይሞትምየሚል መልዕክት ሰማሁብላ ነግራኝ ነበር። ላምናት ግን አልቻልኩም። በማግስቱ የጥቅምት መድኃኒዓለም በሚውልበት ዋዜማ ሲመሻሽ (እርግጠኛ ነኝ በኢትዮጵያ የመድኃኒዓለም ማኅሌቱ ደምቋል።) አንዲት ጓደኛዬ ደውላጸሎት የሚያደርጉ ካህን አንዲት ልጅ ይዛቸው እየመጣች ነውና እበሩ ድረስ ሄደሽ ተቀበያቸውአለችኝ። እኔም እንደተባልኩት እውጭ በር ድረስ ሄጄ ብጠብቅ ቄሱንና ልጅቱን አላገኘኋቸውም። ተመላላሹ ሰው ብዙ ስለሆነ እንኳን የማላውቃቸውን የማውቃቸውንም ለማግኘት ይከብድ ነበር። ከብዙ ጥበቃ በኋላ ተስፋ ስቆርጥ ለጓደኛዬ ደውዬ ልጅቱን ላገኛት እንዳልቻልኩ ነገርኳት። እሷምእስካሁን እንዴት አልደረሱም?” ብላቆይ ልደውልላትና እሷ እንድትደውልልሽ አደርጋለሁአለችኝ። እኔም ብዙ ጠበቅሁ፤ ግን ስልክ ሳይደወልልኝ ቀረ። በኋላ ላይ ጓደኛዬ ደወለችልኝናለምን እንደሁ እንጃ ስልኳን አታነሳም። መልዕክት ትቸላታለሁ ለእኔ ወይም ላንቺ ትደውላለችአለችኝ። እኔም ተመልሼ ወደ ባለቤቴ ክፍል ስሄድ ቄሱ ከሌሎች ሰዎች ጋር ሆነው ይጸልያሉ። ብዙ ከጸለዩ በኋላ ከአርባ ሓራ በመጣው ቅቤ ባለቤቴን ግንባሩን ሲቀቡት ዓይኑን ገለጠ። ቄሱም ጥያቄ ሲጠይቁት በዓይኑ ይመልስላቸው ጀመር። አምላካችንን አመሰገንን። ምስጋና አንዲት ናት። የሱ ግን ቸርነት ብዙ ነው። እሱ ሌላ አይፈልግም፤ ምስጋና ብቻ። ግን ምስጋና ያንሰዋል። መድኃኒዓለም በዕለተ ቀኑ ባለቤቴን ከሞት መለሰው። የባለቤቴ የሰውነቱ ሙቀት ተመለሰ። ሐኪሞቹም በማግስቱ መጥተው ሲያዩት ዓይኑን ቁልጭ ቁልጭ ሲያደርግ አላመኑም። በራሱ መተንፈስ ይችል እንደሁ ብለው የተሰካካውን ገመድ ነቀሉለት። ያለ መሣሪያው መተንፈስ ቻለ። ተቃጥሏል ያሉት ሳንባ ይሰራል። ኩላሊቱም ደሙን ማጣራት ይችላል። ሌሎቹም እነሱ ተበላሽተዋል ያሏቸው የሰውነቱ ክፍሎች በሙሉ ንጹሕ ሆነው አገኟቸው። ባለቤቴን እግዚአብሔር እንደገና ፈጠረው። ይህን ድንቅ ለሠራ፣ ከዚያ ከባድ ጭንቀት ለገላገለኝ አምላክ አንዲት ምስጋና ብቻ እንዴት ትበቃዋለች? የሆኖ ሆኖ፣ አሁን እኔ ለሌላም ተርፌአለሁ።


 አንዲት ሴትእህቴ አትናገርም፣ እጇም በድን ሆኗልብትለኝ ትንሽ የተረፈችኝ ከአርባ ሓራ የመጣች ቅቤ ነበረችኝ እሷኑ ሰጠኋት። ያችን ተቀብታ እጇንም ማንቀሳቀስ፣ መናገርም እንደጀመረች እህቷ አበሰረችኝ። ክብር ምስጋና ለመድኃኒዓለም ይሁን። እኛ ልባችን ጠጣር ሆኖ ብናስቸግረውም በምህረቱ እየጎበኘን፣ ቸርነቱን እየገለጸልን ይገኛል። ባለቤቴ ስለመዳኑ ሕልም ያየችውም ጓደኛዬ አርባ ሓራ መድኃኒዓለም (መንዝ ማማ ምድር) ድረስ ሄዳ ስዕለቷን አግብታ ተመልሳለች። ይህ ከዚህ በላይ  ቀረብኩላችሁ ባለቤቴ የዘገበችውን ታሪክ ነበር። ይኸ ሁሉ ሲሆን እኔ ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም። እኔ የነበርኩት በደስታ ዓለም ውስጥ ነበር። በሀገራችን ኦጋዴን አካባቢ እንዳለው ዓይነት ጣራውም ግድግዳውም በአፈር በተሠራ ቤት ውስጥ በተከመረ የስንዴ ምርት ላይ ስሮጥ ነበር የቆየሁት። ቤቱ ብዙ በሮች ስላሉት በአንዱ በር ገብቼ በሌላው እወጣለሁ። እንደገና ተመልሼ እገባና በእህሉ ላይ እሮጣለሁ። ቤቱ ውስጥ ደማቅ ብርሃን አለ። ብርሃን ከየት እንደሚበራ አይታወቅም። መቆም የለም መሮጥ ብቻ። እረፍት አልነበረኝም። ሆኖም ከደስታ በስተቀር ድካምአይሰማኝም ነበር። ከነቃሁ በኋላ ወደ ቤቴ እንዲወስዱኝ ነበር የጠየቅሁት። በሆስፒታል አልጋ ላይ መቆየቱ ደስ አላለኝም። ከደስታ ዓለም ተመልሼ እንደገና ወደ ጭንቀት መግባት አልፈለግሁም። በእግዚአብሔር ደግነት ፍጹም ጤነኛ ሆኜ ከሆስፒታል ከወጣሁ በኋላ አሁን ወደ ሥራዬ ተመልሻለሁ። ቢገርማችሁ በቀን እስከ አስራ ስድስት ሰዓት ድረስ እየሰራሁ ነው።



በቅዱሱ ሥፍራ በአርባ ሓራ መድኃኒዓለም ገዳም ተገኝቼ እግዚአብሔርን ለማመስገን እንድበቃ በዝግጅት ላይ  እገኛለሁ። ሐኪሞቹ በኔ ነገር እስከ አሁን ድረስ ግራ እንደተጋቡ አሉ።ምን ዓይነት እምነት ነው ያላችሁ!” በማለት  በተደጋጋሚ ይደነቃሉ። የመንፈስ ቅዱስን ሥራ ሊመረምሩትና ሊደርሱበት እንደማይችሉ የታወቀ ነው። አንድ ከፍተኛ  ትምህርት ግን አግኝተዋል ብዬ እገምታለሁ። ሳይንስ ሊደርስበት የማይችል የመንፈስ ቅዱስ ኃይል እንዳለ። ሰው ከሞተ  በኋላ እንደገና መነሳት እንደሚችል። እግዚአብሔር አልዐዛርን በሞተ ከአራት ቀናት በኋላ ያስነሳው ከሞት ስለመነሳቱ  ተጠራጣሪዎች ጥያቄ እንዳያነሱ ነበር። አልዐዛርን እንደሞተ ዕለቱን ቢያስነሳው ኖሮአልሞተም፣ መች ሞተና ነው?” ብለው ይከራከሩ ነበር። እኔንም እግዚአብሔር የመለሰኝ (ያስነሳኝ) በሐኪሞች ግምት እንደገና በሕይወት ለማንሰራራት  ከማልችልበት ሁኔታ ነው። እግዚአብሔር በኔ በኃጢአተኛው አድሮ ክብሩ

Monday, October 20, 2014

ድንቅ ተአምር በአቡነ መልከ ጸዴቅ ገዳም

በአቡነ መልከ ጸዴቅ ገዳም የተደረገውን ተዓምር ብጹእ አቡነ ዲዮስቆሮስ እንዲህ ይመሰክራሉ::




የሚዳ አቡነ መልከ ጼዴቅ ገዳም (Mida Abune Melketsedek Monastry)

Tuesday, September 30, 2014

በልበሌቲ ጽጌ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን

በልበሌቲ ጽጌ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከአዲስ አበባ 418 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ቦታውም ለመድረስ ከአዲስ አበባ በናዝሬት፣ አሰበ ከዛም በበዴይሳ አድርገው ወደ ገለምሶ ይጓዛሉ በመጨረሻም ቤተክርስቲያኑ የሚገኝበት በልበሌቲ መሻገር ይኖርቦታል። መንገዱ ለማንኛውም መኪና ምቹና ቤተ ክርስቲያኑም መንገድ ዳር በመሆኑ ምንም እንግልትና የእግር ጉዞ የለውም።

ይህ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘው በምዕራብ ሐረርጌ ሐብሮ ወረዳ በልዩ ስሙ በልበሌቲ በመባል በሚታወቀው መንደር ሲሆን ለምዕራብ ሐረርጌ የመጀመሪያው ቤተክርስቲያን ነው። የተተከለውም በእምዬ ምንሊክ በፊታውራሪ ዘመንፈስ በ1870 ከአርሲ እያስገበሩ ሲመጡ በምዕራብ ሐረርጌ ሲያልፉ እንደተከሉት ይነገራል። ቤተ ክርስቲያኑ ሲዘዋወር አሁን ያለበት ቦታ ሰባተኛው ሲሆን እምዬ ምንሊክ ለቤተ ክርስቲያኑ የሰጡት ርስት 18 ጋሻ መሬት ቡሩሪ በሚባል ቦታ ህንጻውም ባለ ደርብ(under ground) የሆነ ነበር። በጣልያን ወረራ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ በመቃጠሉ ከተሰጠው ርስት በመነሳት በሽሽት ቀርጫ የሚባል ጫቃ ውስጥ ለ 5 ዓመት ስብሐተ እግዚአብሔር ሲደርስ ቆይቷል። በዚህ ወቅት ያ 18 ጋሻ መሬት የለውም እዛ ቦታ ላይ ሌሎች ሁለት ቤተ ክርስቲያን ታንጸው እሱ የሚገኘው ሌላ አዲስ በተመራው ቦታ ላይ ነው። በዚህ ቤተ ክርስቲያን የሚነግሱ ታቦታት ሶስት ሲሆኑ እነሱም ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚያዚያ 23ና ጥር 18፣ ኪዳነ ምህረት በየካቲት 16፣ ሩፋኤል በጷግሜ 3 ይነግሳሉ።

ደብሩን ምን ልዩ ያደርገዋል

ስለት ሰሚነቱ
በአገር ውስጥም ከአገር ውጪም ባሉ የአካባቢው ሰዎች የበልበሌቲው ጊዮርጊስ አንተው ስለቴን ፈጽምልኝ ብለው የተሳሉ ሁሉ ላመኑት ክርስቲያኖች ብቻ ሳይሆን ከክርስናው ውጪ ላሉትም ሰዎች እንኳ ሳይቀር ስለታቸው ደርሶላቸው በድብቅ (ሰው በመላክ) በግልጽም (ራሳቸው በመምጣት) ስለታቸውን ይልካሉ። በሐኪም እንደማይወልዱ የተነገራቸው፣ ትዳር ያጡ፣ በህመም የሚሰቃዩ፣ ውስብስብ ችግር የገጠማቸው፣ ብዙ ብር ጠፍቶባቸው የነበሩ ሌሎች ሌሎችም የህይወታቸው እንቆቅልሽ ተፈቶላቸው አምላከ

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ?

የኢንተርኔት አገልግሎት ፈጣን ባልሆነበት ቦታ በአማራጭነት ይህንን በጽሑፍ መልክ ያንብቡ:: ረጅም ትምሕርት ሲሆን በተቻለ መጠን በቂ መልክቱን በጽሑፍ አቅርበናል:: የቃላት ግድፈት ካለ እያረሙ እንዲያነቡ እንጋብዛለን::
የጸሎት ቦታ እንዴት ላዘጋጅ?

ክፉንና ደጉን ለመለየት አምልኮ ያስፈልጋል:: አምልኮ የሌለበት ህይወት አለም ላይ የወደቀ ነው ስለዚህም የአምልኮት ራእይ አንድ ክርስቲያን ሊኖረው ይገባል:: ማምለክ ማለት እግዚያብሔርን ከልብ መውደድ: ቃሉን በልቦና ማኖር: እና መጠበቅ: እርሱን ተስፋ ጉልበታችንን ማድረግ ነው:: በተግባር ደግሞ ኑሮን ጠባይን ለእግዚያብሔር መስጠት: ውስጣዊ ህይወታችንን ለክብሩ የተዘጋጀ ማድረግ :: ስለ ሐጢአታችን ንሰሐ ገብተን ሥጋውና ደሙን መውሰድ: እለት እለት ስለበደላችን ስለሐጢአታችን ለእግዚያብሔር መንገር:: እለት እለት እግዚያብሔርን የምናመሰግንበትን ግዜ ካገኘን የአምልኮት ሕይወት ገበና አለን ማለት ነው:: ሰብአ ሰገል ክርስቶስን በፍቅር ፈልገው እንደመጡ አንድ ክርስቲያንም ክርስቶስን ፈልጎ መምጣት አለበት:: በአምልኮት ባሕርይ ሔሮድስን ማለፍ ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ነው:: ሔሮድስ ማለት የዚህ አለም ነገሮች ናቸው እነዚህም :የአለምን ሰዎች እውቀት: ሳይንስ እግዚያብርሔን የሚከለክል : የድንግል ማርያም ልጅ ክርስቶስን የሚከለክል ነው:: ሔሮድስ ማለት ሐብት : ስልጣን: ማዕረግ የመሳሰሉት እነዚህ ሁሉ የሔሮድስ መንገድ ጠቋሚ ናቸው:: ሰዎች የጥፋት ሞት ውስጥ የሚገቡት የአምልኮት ሕይወት በማጣት ነው:: እግዚያብሔርን የሚፈልጉ ሰዎች ሔሮድስ ጋር መቅረት የለባቸውም:: ኮከቡን ማየት አለባቸው ኮከቡም ያለው በሰማይ ነው::

ብዙ ክርቲያኖች ወደ እግዚያብሔር ቤት አይሔዱም ወይም ወደ ሰማይ ቀና አይሉም:: በዚህም ወደ ልባቸው የሚሔድባቸው መጣባቸው:: ሰይጣን ወደ ቤታቸው ወደ ኑሮአቸው ወደ ሕይወታቸው መጣ:: በዚህ ዓለም ገለልተኛ ሆኖ መኖር አይቻልም:: በዚህ አለም ሁለት ነገር ነው ያለው:: ጽድቅና ኩነኔ: ጨለማና ብርሃን: ሓጢአትና ጽድቅ: ሰላምና ጦርነት::ከፈለክ ወደ ብርሃን ካልፈለክ ወደ ጨላማ: ከፈለክ  እውነት ካልፈለክ ሐሰት: እንዲህ በጥንድ የተያያዘ ነው:: የእግዚያብሔርን በቅድምያ ከሰማን የእግዚያብሔር ጽድቅ ይገለጥልናል: የሰዎችን ከሰማን ሁል ግዜ እንደተደናገግርን ተስፋችንን በአልሆነ አቅጣጫ እየጠበቅን እንኖራለን:: ሔሮድስ ክፉ መሆኑን የምናውቀው ስናመልክ ነው::

የጸሎት ቦታ
የጸሎት አቅጣጫ ምስራቅን የተመለከተ መሆን አለበት:: በመንበርከክ በግንባር ልክ የእመቤታችን የቅዱስ ሚካኤል የቅዱስ እና የቅዱስ ገብርኤል በግራና ቀኝ : በመቆም ልክ የስላሴ የመድኃኔአለም ስእል ይደረጋል:: ከስእሉ ራቅ የሚባለው ክፍተቱ የመጽሐፍ መግለጫ ያህል ነው:: ስእሎቹ ተጸልዮባቸው ቅባ ቅዱስ ይቀባሉ ቢቻል ቤተ ክርስቶያን ተባርካው በቅዳሴ ግዜ ቅባ ቅዱስ ተቀብተው መሆን አለበት:: ስእሎቹ በጥሩ ፍሬም የተሰሩ ስእሎች መሆን አለባቸው:: ከስራቸው የጸሎት ወሃ : እጣን: እምነት:የወይራ ዘይት: የመጽሀፍ ማስቀመጫ: የምንጠቀምባቸው እንደ ሽቶ ዎች ካሉ አጠገብ መሆን አለባቸው:: ሽቶ የሚወዱ ዛሮች አሉ:: ተጸልዮበት ሽቶ ብንጠቀም ሽቶ የሚወዱ ዛሮችን መከላከል ይቻላል : የመንበርከኪያ ቦታ ደረቅ ያለ የጥጥ ፍራሽ ቢሆን ይመረጣል:: ግልበት በሚሰግድበት ግዜ መመቻቸት አለበት ነገር ግን በጣም የሚመች ሥፕንጅ መሆን የለበትም: ስንፍና እንዳይሰማው: የሚሞቅ ነገር መሆን የለበትም መቀዝቀዝም የለበትም:: በሚሰግድበት ግዜ በስእሎቹ ፊትለፊት  መስገድ ሲጀምር የሚከተሉትን ምልክቶች ያያል:- መዛል:መድከም መልፈስፈስ :: በሚጸልይበት ግዜ ከስእሎቹ የሚወጣ መንፈሳዊ እሳት አለ:: በሰውነቱ ላይ ከስእሎቹ ተጠግቶ ሲጸልይ መውረር መቅበጥበጥ:ማቃጠል የሚታይበት ይሆናል:: አንዳንዱም መንፈሱ ወዲያው መገለጥ ጠባይ አለው:: መንፈሱ ጸሎት በከፍተኛ ሁኔታ ጸሎት እየከለክለው የሚያጠቃው ከሆነ የቅዱስ ሚካኤልን ስእል በፍሬም በጥሩ ሁኔታ ሰርቶ  መሬቱ ላይ አድርጎ እጁ ላይ እና ሰይፉ ላይ በሚሰግድበት ግዜ መንፈሱ ሊጥለው ይችላል:: በዚህ ግዜ መቁጠርያ ያስፈልጋል::ጸጥ በል በጌታየ በየሱስ ክርስቶስ ስም ብሎ ሲመታው ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እሰርልኝ ሲለው  በስእሉ ፊት ያለው ሐይል እየተገለጠ ቅዱስ ሚካኤል ሊያስርለት ይችላል:: ሰውየው እየሰማም እያወቀም መንፈሱን ሊያስርለት ይችላል:: በዚህ ግዜ ፕሮግራም ይዞ ወድ  እኔ ደውሎ አንዳንድ መረጃ እንለዋወጣለን:: የሚደክም ከሆነ ይደክማል የሚሸኝም ከሆነ ይሸኛል:: ሆኖም ግን  እነዚህን ልምምዶች በቀላሉ የሚመጡ  አደሉም:: ሰውየው በጥሩ የበረከት መንፈሳዊ ህይወት ለማለፍ እራሱን ማዘጋጀት አለበት:: ጸሎትን እንደ ደስታ አምላክን እንደማማረርያ ጎዳና ሳይሆን "ሁል ግዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ:ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ::ገርነታችሁ ለሰው ሁሉ ይታወቅ::" እንዲል ገራገር መሆን አለበት:: "ጌታ ቅርብ ነው::በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ::" ፊልጵስዮስ 4:4-6

ራእይን ምሪቱን ለማግኘት ደግሞ የጸሎት ቦታችን ላይ ለባልና ሚስት የመኝታ ያህል መኖር አለበት: ቤተሰብ ካለው ከሌለው