Friday, March 25, 2016

የእመቤታችን መቃብርና ያረገችበት ጣራ - Tomb of The Virgin Mary

ትውልድ ሁሉ ብፅእት የሚላት በተለይ እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ነብሳችን የምንሳሳላት የእናታችንና የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ መካነ መቃብርና የተነሳችበት/ያረገችበት ቅዱስ ጣራ ከታች በፎቶ እንደምታዩት ይህን ይመስላል። የሚገኘውም እየሩሳሌም ውስጥ በቄድሮን ሸለቆ አካባቢ ነው።የእመቤታችን ምልጃና ፀሎት በረከትና ረድኤት ከኛ ከምንወዳት ልጆቿ ጋር ለዘላለም ይኑር! በረከቱ ለእናንተም ይድረስ። 


ድንግል በእውነት ተነስታለች ምስክሩም ይኸው ያረገችበት ቅዱስ ጣራ በቄድሮን ሸለቆ (Kidron Valley) ይህን ይመስላል። ይህንን ቅዱስና ድንቅ ቦታ ለሌሎች ሼር በማድረግ እናንተም የበረከቱ ተካፋዬች ሁኑ! እኛ የድንግል ልጆች ስለምናምነው ቀጥተኛና እውነተኛ የተዋህዶ ሀይማኖት ትክክለኛ መረጃና ከልብ ስለምንወዳት ድንግል ማርያም የማንጠራጠርበት ምክንያት አለን። በዚህ ለማያምኑትና አማላጂነቷን ለሚክዱ እመቤታችን ልቦናቸውን ትመልስልን!!! 



የቅድስት ድንግል ማርያም በዘይቱን መገለጽ - በአማርኛ ትርጉም


Monday, March 21, 2016

መልዐከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ከገጠመኛቸው

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፡፡
.
መልዐከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ከገጠመኛቸው አንዱን ሲናገሩ በሬድዮ አቢሲንያ ቁጥር 22 ካስተማሩት የተሰደ…
.
አንድ ቦታ ላይ አከራዩኝ ብየ ኪራዩ እንደ ጠያቂ ሆኜ ሄድኩኝ፡፡ ከገባሁ በኋላ ዕቃየን አጓጉዤ፡፡ አንድ መኪና ሙሉ አጓጌዤ ማለት በፒክ አፕ ገባሁና ቤት አገኘሁ ብየ ነው፡፡ ለዛዉም እኮ ደግሞ ደግሞ አንድ ክፍል ናት፡፡ በጣም አስቸጋሪ ናት ደግሞ በዛ ላይ ጥበትዋ፡፡ ግን ትበቃኛለች እኔ ምን አለኝ ገብቸ መዉጣት ነው፤ ጸሎት ማድረስ ነው ብየ መሬት አደላድየ አንጥፌ ምን ብየ ጥዋት ለአገልግሎት ልብሴን ለብሼ፤ መጸሐፌን በሻንጠየ ይዤ ስወጣ፡፡ የት ነው የሚሄዱት? አለችኝ ሴትየዋ፡፡ ወደ መሪ አቦ፡፡ እንዴ፤ እንዴ፤ እንዴ መሪ አቦ ሰው የሚያንጫጩት እርስዎ ነዎት? አለችኝ፡፡ አዎ ነው እናትየ፡፡ እኔ ደግሞ በቅን የምታይ መስሎኝ ነው፡፡ እ..ም… አለች፡፡
.
አረረረ..በቃ ሐበሻ እንዲህ ሲል ችግር አለ ማለት ነው፡፡ ሆዴን እየቆረጠኝ ነገሩን እየበላሁ እ..ም… የምትለዋን ቃል ይዤ መጓዝ ጀመርኩ፡፡ እንግዲህ እ..ም… ማከት በሐበሻ ነገር የመብላት ዋዜማ ወይም በልቡ ዉስጥ የቆረጠው ነገር በቅፅበት አለ ማለት ነው፡፡ ይህቺ ነገር ሳስተምር ሁሉ ሆዴን ትበላኛለች፡፡ ስመለስ መጡ እንኳን ደህና መጡ፡፡ ስጠብቆት ነበረ፡፡ ገና ምሳ ሳልበላ፤ አረፍ ሳልል ቤት ይፈልጉ፡፡ ልጄ ከአሜሪካ ትመጣለች ስልክ ተደዉሎልኛልና ሰሞኑን ቤቱን አፀዳድቼ፣ ቀለም ቀብቼ ልጄ ልጠብቃት ስለሆነ ዛሬዉኑ ቤት ይፈልጉና በሦስት ቀን ውስጥ እንዲወጡ እባክዎትን ይተባበሩን አሉና ቁጭ፡፡
.
ጉድ ፈላ፡፡ ይህ ሁሉ ታድያ ይቺ ቀሚሴ አይደለች ጉድ ያፈላች አልኩና ቀሚሴ ላይ አፈጠጥኩ ሳቅ…፡፡ ወይ ቀሚሴ አልኩ በቃ፡፡ ወይ ይቺ የቤተክርስትያን ቀሚስ ይገርማል አልኩና፡፡ ከዛ ደግሞ ስሜ ነው አንዱ ችግሩ ደግሞ የሚያንጫጫው ከተማውን የሚለው ደግሞ የተለመደ ነው እስከ ቅርብ ግዜ ድረስ፡፡ እንደዉም የሚያሳዝነኝ እስካ አሁን ድረስ በጣም አሁንም የምያሳዝነኝ እንዲህ አይነት ጭዋታ፤ እንዲህ አይነት የእርግማን መንፈስን የሚያስፋፉ በቤተ ክርስትያን ያሉ ጉብል ሰባኪዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ጉብልዎቹ፡፡ አዳዲስ ጉብልዎቹ ሰባኪዎች እስካ አሁን ድረስ አሁን አሉ መጸሓፍ መውጣቱን እንኳ አላወቁም፡፡ መጥተው የዳነዉን ህዝብ፤ የዳነዉን ህዝብ አይጠይቁም፡፡ አሁን በያዙት ቦታና በተመደቡበት ቦታ ላይ እስካሁን ድረስ እኔን እያሳደዱ ነው፡፡ ለምሳሌ በሳሊተ ምህረት ሲኤምሲ ይሰብካሉ፤ በጥንት የነበረው በጣም የታወቀው ቦታ ላይ የካ ሚካኤል ይሰብካሉ፡፡ ግርማ የሚባል አስማተኛ ከተማ በጠበጠው እያሉ ሰሙኑን ሁሉ ይሰብካሉ፡፡ የካ ሚካኤል ትልልቅ ሰው ባለበት፤ አባቶች የሚባሉ ባሉበት በዛ ቦታ ላይ ትልልቅ ደህንነት፤ ዓይነ ስዉር በበራበት ቦታ ላይ ሲያሽካኩ መድረኩን ሲጫወቱበት ይዉላሉ፡፡ ህዝቡ አይ የምታውቁት ነገር የለም ዝም በሉ እስኪላቸው ድረስ የሚያሳፍር ነው በጣም፡፡ እና የሚያሳፍሩ ናቸው፡፡
.
እና እነዚህ አዳዲሶቹ ጉብልዎች የፈጠሩት ችግርና በዓውደ ነገስቱ ዓለም ይኖሩ የነበሩት አባቶች የንስሐ ልጆቻቸውን እያወገዙ እርሱ ጋር ከሄዳችሁ የተረገማችሁ ናችሁ፤ እርሱ ጋር ከሄዳችሁ ውጉዝ ከመ አርዮስ እያሉ ህዝበ ክርስትያኑን ብጥብጥ አድርገው ትልልቅ የሆኑ ውርደቶችን እያስተላለፉ ከቤተ እግዚአብሔር ያሉት አባቶች ናቸው፡፡ እነርሱ ባደረጉት ትግባርና በቀሰቀሱት ቅስቀሳ መኖርያ ቤት እምከራየው ቤት እስከማጣ ድረስ፡፡ ከዛ በኋላ በኋላ ሴትየዋ አጣደፈችኝ፡፡ በሦስት ቀን እለቅሎታለው አልኩኝ፡፡ አሁንም ፍለጋ ጀመርኩ፡፡ ስንፈልግ፤ ስንፈልግ እኔን ከሚያውቁኝ ደላላዎች ጋር ስንፈልግ እባካችሁ ጉባኤ ላይ ተናገርኩ እባካችሁ የቤት ደላላዎች የላችሁም ብየ ሰው ፊት ተናገርኩ፡፡ መጡ እኔ አውቃለሁ አለ፡፡ ከዛ በኋላ እስኪ ቤት ፈልግልኝ አልኩ፡፡ አሁንም ስንፈልግ ሄድን አሁንም አንድ ቦታ ተገኘ አለ፡፡ ትልቁ ቤት ላይ ሳሎን አለ፡፡ ከሳሎኑ ኋላ ያለቹው ጓሮ ነው ያከራየው፡፡ አሷም ደግሞ 500 ብር አለችኝ፡፡ እሺ ጥሩ ችግር ለም አልኩ፡፡ ያኔ ምንም የለንም፡፡ በጣም ተወዶብኛል፡፡ ሆኖም ከቤተሰብ ጋራ ማለት ነው፡፡ ደሞዝ የለም ምን የለም፡፡ እሺ በ 500 ብር ተስማማሁ ወዴት ልሂድ ታድያ ለመሪ ቅርብ ነው፡፡ ከዛ በኋላ ሄድንና ሰዉየው ሲያዩኝ ምነው የሚከብዱ ይመስላሉ?፡፡ እንዴት?፡፡ ሳዮት ከበድበድ ያሉ ነዎት ለኛ ቤት አይመጥንም፡፡ እንዴ ለመኖርያ ቤትዎ ለዚህ ለሚያከራዩኝ?፡፡ አይ ማለቴ የኛ ቤት ለርስዎ የሚሆኖት መስሎ አልታየኝም፡፡ ተለቅ ያሉ ሰው ነዎት ማለቴ ነው፡፡ አረ እኔ የምታዩኝ ምን ለራሴ ኩርማም ጭባጥ እማልሞላ፡፡ አይይ ግድ የሎትም የኛ ቤት አይመጥንዎትም ለፊቴ ደግሞ እርስዎ ከብደዉኛል አለና ቁጭ፡፡ ከሸፈ ይሄም ከሸፈ፡፡
.
በኋላ አንዱ ጉባኤ ላይ አረ እባካችሁ በመኖርያ ምክንያት ለቅቄ ልሄድ ነው እንዴ አዲስ አበባ ትቻቹ ልሄድ ነው ስል፡፡ አይ የኔ እናት ታማለች በዛው እገዛ እያደረግክልን ትቀመጣለህ አለኝ እና አንድ ወንድም፡፡ እዛ ቤት ገባሁ፡፡ ከዉስጧ የተከፈለች ነች፡፡ በከፊል ደግሞ ለሌላ የጸሎት መገልገያ የምትሆን ቦታ አደረግኩና ቁጭ አልኩ፡፡
.
በነሱ ላይ የመተተችባቸው ሴት ደግሞ በጓሮ በኩል አለች፡፡ በዛ ስወጣ ስገባ መተተኛ መጥፎ ደሮ ትላለች ደሮዋን እያየች እኮ ነው፡፡ ኮቴሸን መስበር ነበረ እያለች የገዛ ደሮዋን በኔ እያሳበበች አኔን ትራገማለች፡፡ ልክ መውጭያ ሳዓቴን ታውቃለች የታባትዋ ይህችን ደሮ እዚህ ከገባች ጀምሮ እንዲሁ አታክልቱ መሬቱን ቦታው ሁሉ ተግማማኮ ትላለች፡፡ እኔ ጸሎት ሳደርስ እንግዲህ ዕጣኑ እየሸተታት ነው መሰለኝ፡፡
.
እንደገና በሌላው ቀን ደግሞ ቆይ አንቺን ከዚህ ሳላጠፋ ይህቺን ደሮ የሚያርድልኝ እንደዉም ምንም ሰውና ቢላዋ ላጣ ነው ትላለች፡፡ የፈረደባት ደሮ ግን ደሮዋ የለችም፡፡ እኔ ነው ደሮው ሳቅ ሳቅ…፡፡ የሚገርም ነው እንዲህ ያለች እያለች ደግሞ ከቤት ውስጥ ደግሞ አንድ መንፈስ ያለባት ልጅ አለች፡፡ ለሷ መንፈስ ነፃ እንድወጣ ስታገል ደግሞ የሷ መንፈስ እሷን ገለበጠና ደግሞ እሷ ከጎኔ ነበረች፡፡ ግድግዳዉን ትደበድባለች፡፡ የታባቱ ይሄ ሰዉየ ከዚህ ካተነቀለ የአባቴን ቤት ይዞ፤ የአባቴን ቦታ፤ ይዞ እናቴን እያስቸገረ እያለ ደግሞ እሱ ደግሞ ሌሊት ከእንቅልፍ ይከለክለኛል፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ አይጦቹ ይንጋጋሉ፡፡ በመጨረሻ አንድ አይጥ ጣቴን ስጋ ያገኘ መስሎት ቦድሶ ለቀቀው፡፡ አባቶች አይጥ ሲነክስህ ያሰብከው ይሳካል ይላሉ፡፡ ዎው አልኩና ቢቸግረኝ በጣም ተስፋ አደረግኩኝ ሳቅ ሳቅ…፡፡ ምክንያቱማ አይጥ ሲበዛ በረከት ይመጣል ይባላልና የቀደሙ አባቶች የሚናገሩት ነው፡፡ አይጥ ምቀኛ ነው፡፡ ምቀኛ ሲበዛ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ሆኖ በረከት ይሰጣል እንደ ማለት ነው ትርጉሙ፡፡ ጎሽ እንግዲህ አባቶች የተናገሩት የአይጥዋ ድርሻ በእጄ ላይ ስላረፈ እግዚአብሔር አንድ ነገር ያደርጋል ብየ ጠበቅኩኝ፡፡ እዛው ቤት እንዲሁ መንከራተት፤ መንከራተት በአንድ በኩል ሌባውም ደጅ ሲጠና፡፡ አንዳንድ ዕቃዎችን ደግሞ ከዛ አሽሼ ዘግቼ ወደ ዝዋይ ወደ ቤተሰብ ሄጀ ስመለስ፤ መጣ እንዲህ ይቺ መጥፎ ደሮ ስባል ምን በቃ እንግዳው ሲመጣ ደሮ እንግዲህ ይግበሰበሱ ጀመር እነዚህ ግብስብሶች መምጫቸው መሄዳቸው የማይታወቅ ድራሻቸው ይጥፋ ስንባል፡፡ ልክ እንግዳው ሲመጣ ያቺ መታችዋ በጎረቤት በኩል ትጮሃለች ኡ ኡ ነው የምትለው፡፡ እንግዳው ሲመጣ ትራገማለች፤ ትታገላለች፡፡ ይሄ መተተኛ ደብተራ ትላለች፡፡ ከዛ እንግዶች ሁሉ፡፡
.
በጣም የሚያሳዝነኝ ደግሞ ሞራሌን የነካው፡፡ አንድ ሴት አሜሪካ ቪሲዲዉን ተለቆ ነበር ያን ግዜ ደግሞ፡፡ አይታ ልጅዋን ልታድን ወደኔ ትመጣለች፡፡ ደህና ሰው ተብሎ እንግዲህ የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦለት ተብሎ በሷ አስተሳሰብ እንግዲህ በጣም የተሻለ ቤት፣ የተሻለ ኑሮ ብላ ነው የምትጠብቀው፡፡ ከዛ መጣች ሳጥን ሰጠኋት መቀመጫ፡፡ ወንበር የለኝም፡፡ እኔ እዚህ የምጸልይበት ቦታ መሬት አለች እዛች ላይ ቁጭ አልኩኝ፡፡ ልጇን ይዛ መጣች፡፡ ቤቱን ታያለች፡፡ እንዲህ እንዲህ ብላ ወደ ላይ ጣራዉን ታያለች፤ ግድግዳው ታያለች፡፡ ግድግዳው ጭቃ ነው በአንድ በኩል ከኋላ በኩል ደግሞ ጭቃው ተገርስሶ አፉ ከፍተዋል፡፡ አንዳንዴ ዝናብ ሲመጣ በዛ በኩል ይመጣል፡፡ ከነካሁት ሊፈርስ ነው፡፡ ይወድቅና እንደገና ደግሞ ኦና ሊሆን ነው፡፡ እና ዝም ብየዋለው ምን ላድርግ ሲወድቅ ድረስ፡፡ ከዛ ግድግዳዉን ከአሁን ከአሁን አትውደቅ እያልኩ እቀመጣለውና መጥታ ሳጥን ላይ ቁጭ አለች፡፡
.
ቤቱን ታያለች፤ ታያለች፤ ታያለች ይሄው የመጣሽበት ጉዳይ እንግዲህ ልጅሽ ነው ጸሎት እናድርስ ስል፡፡ እየፈፋት ነው ቤቱ እሷ ከአሜሪካ ነው የመጣችው፡፡ በማቴርያልም ጭምር ያመልካሉ፡፡ እንግዲህ ይሄ በዓለም የታወቀ ሰዉየ ይዚህ ቆሻሻ መንደር ውስጥ ምን ያደርጋል ብላ ነው እሷ፡፡ ስለዚህ የመጣሁት ወደ ጠንቋይ ሰው ነው ብላ ነው የገመተቹው በቃ፡፡ ያው ቤቱ ደግሞ የጸሎት ዕጣን ስለሚደረስበት እሷ የምታውቀው አይነት ባይሆንም ዕጣን ዕጣን ይሸታል፡፡ አሃ ብላ በስጋት ዓይን ታየኛለች፡፡ ከዛ ልጅቱ ላይ ያለው መንፈስ ተያዘ፡፡ ቡዳ፣ መተትና ዓይነ ጥላ ነበረ፡፡ ይሄ መያዙ አላስገረማትም፡፡ ያስገረማት የምኖርበት ቤት የቀፈፈው መሆኑ ነው፡፡ እና አላስደሰታትም፡፡ ከዛ ይሄው ይሄው ተያዘልሽ አልኩኝ፡፡ ቅር እያላት ሳይ በኋላ እየጸለይኩ ከመንፈሱ ጋር እየታገልኩ በስዕሉ መስታዎት ሳያት ላይ ጣራ ጣራዉን ታያለች፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ አይጥ በላይ በጣራው በኩል ስትመጣ በርግጋለች፡፡ ዘንዶ የተቀመጠ መስሏታል፡፡ ይሄው በቃ ተይዘዋል ስላት፡፡ ተያዘ እንዴ? ይሄ ነበረ ችግርዋ አለችና እግዚአብሔር ይስጥለኝም አላለችም ቀስ ባላ ሹልክ ብላ ስትሄድ እንዴ ገረመኝ፡፡ ምን መሆኗ ነው የሷ ደንብሮ ነው እንዴ ብየ በኋላ ሳስተዉለው ቤቱ ቀፏት ነው፡፡ የምኖርበት ቤት ቀፏት ነው፡፡ በስልክም ያለችው ነገር የለም፡፡ እኔ ታግየ ብቻ ከልጂቱ ጭንቀትና ችግር ጋር ተካፍየ ነው ሂጂ በቃ እና ነገ ትመለሻለሽ፡፡ እንግዲህ ተመልከት ስትቀር ስጠብቃት ስልክ ስደዉል ዝግት ታደርገዋለች፡፡ ለልጂትዋ አስቤ እናትየዋ እንግዲህ ለልጂትዋ ማሰብ አቅትዋት ነው፡፡ ያንን የመሰለ ዉርደት፣ ያን የመሰለ ክፉ መንፈስ ለዘመናት ያደቀቃት ልጂቱን የጎዳት እንዳታገባ ዓይነጥላው አለ፤ እንዳትወልድ ዓይነጥላው አለ፤ ሥራው እንዳትሰራ መተቱ አለ፡፡ እቤት ጉልት ልጅ ይዛ መንፈሱ ተጋልጦ በዛች ኮሳሳ ቤት ምክንያት ቀረች፡፡
.
ከዛ በኋላ እሷ ላመጣች እናት ስደዉልላት ምን አይነት ፍንጭ ሰጠችኝ፡፡ የሚኖሩበት ቤት ዓይን የማይገባ ነው፡፡ እንደተባለው ሰዉየው አስማተኛ ሳይሆኑ አይቀሩም አለችና ቁጭ፡፡ ብላለች የሚለው መልዕክትን እንደገና፡፡ በቃ በቃ አልኩ ይህን ለተናገረችው ሴት ስልኩም አጠፋሁ የሷንም ይዚህችኛዉም አጠፋሁና፡፡ ወይ ጉድ ብየ ጸሎቴን ጸልየ፤ ለእግዚአብሔር ተናግሬ የዛን ቀን ያለምኩት ህልም ምን ግዜም የማይረሳኝ ነው፡፡ በደንብ ለአምላኬ ተናገርኩና መቼ ነው ከኢኮኖሚ ነጻ የምታወጣኝ፡፡ ከኢኮኖሚ ባርነት ከዚህ ከቤት ክፉ አገዛዝ፤ ከመኖርያ ቤት፤ ከእርግማን መቼ ነው የምታወጣኝ፡፡ ጠንቋዩና ቃልቻው እዚህ ባለ ሦስትና ባለ አራት ፎቅ ሆኖ የአዲስ አበባ፡፡ የአዲስ አበባ ህዝብ ለጠንቋይና ለቃልቻ ቤት የሚሰራ፡፡ ለመተተኛና ለሟርተኛ ህንፃ የሚገነባ ህዝብ ለኔ አንድ ንፁህ የምከራይበት ቤት አጣሁ ብየ ለእግዚአብሔር ተናገርኩኝና፡፡ ከሌሊቱ አስር ሰዓት ተኩል ለጸሎት ልነቃ ስል የተለየ የጸሎት ቤት ቦታ ያለው፡፡ እጅግ ሰፋ ያለ ብዙ ክፍሎች ያለት እና እጅግ በጣም ብዙ የበረከት ምንጭ ያለው ቤት የሚመስል ራዕይ አየሁና ብንን አልኩ፡፡ በጣም ደስ አለኝ፡፡ በቃ ራዕየይ አመንኩት፡፡ እግዚአብሔር ተናገረ፡፡ ትላንት ባለቀስኩት ዛሬ መልስ ሰጠኝ ብየ እንደገና ጸሎቴን አድርሼ ወደ ቦሌ መድኃኔ ዓለም ሄጄ ተሳልሜ ዙርያዉን ዞሬ ክብርህ፣ ደስታህ፣ ኃይልህ ከኔ ጋር ይን ብየ ደስ ብሎኝ ስጠብቅ፡፡
.
ያው ከአሜሪካ አንድ ታላቅ በሃገሩ መንግስት የታወቀ ፕሮፌሰርና ሳይንቲስት ወደ ኢትዮጵያ መጣ፡፡ በስድስት ወር ውስጥ እኮ ነው፡፡ ከዛች ቤት በነገራችን ላይ ከአንድ ከተወሰነ ወራት በኋላ ወጣሁኝ፡፡ ለሦስት ዓመት አራት ወር የቀረው ኖሬበታለሁኝ ማለት ነው እዛች ቦታ ደሳሳ ጭቃው ሁሉ እየገባ፤ ዉሃ እየተከላከልን ዙርያዉን እየገደልን ዉሃው ሲመጣ አንዳንዴ ውሃ እንዳይስደን እየተጠነቀቅን ቦይ እያወጣንለት እዛ ቆየን፡፡ ይህንን በማድረጋቸው እግዚአብሔር ይስጣቸው፡፡ እነርሱም ታላቅ ውለታ ነው እንጂ አዲስ አበባ ለቅቄ ለመውጣት ሞክሬ ነበረ፡፡ በዚች ሃገር ውስጥ የተለየ አስማተኛ እንደሆንኩ ተደርጎ የሚነገረው የንስሐ አባቶች ድምፅ በከፍተኛ ትንቅንቅ ነበር፡፡ ዲያብሎስ የተዋጋኝ በነሱ በኩል ነበር፡፡
.
ያው ዛሬ በአያት ምድር ላይ አሉ ከሚባሉ አንዱ ቤት ውስጥ እገኛለው፡፡ ያ ሳይንቲስትና ባለቤቱ ቤቱን ገዝተዉልኝ ደስ ብሎኝ እግዚአብሔር ይመስገን ከመንከራተት ድኜ እግዚአብሔር ስሙ የተመስገን ይሁን፡፡ ጸሎቴን በአንድ ቀን ውስጥ ምላሽ ሰጠ እግዚአብሔር፡፡ እዚህ ያለው ህዝብ እንዲህ ሲያደርገኝ ለኔ የሚግዘኝን ከዉጪ አመጣኝ፡፡ ዛሬም የሚለወጡት እዚህ ያሉት በብዛት አይደሉም፡፡ ከዉጪ ያሉት ናቸው የሚለወጡት፡፡ እግዚአብሔር መባረክ ጀመረው የውስጡ ሳይሆን የዉጩዉን ነውና እግዚአብሔር አምላክ ለዘልዓለም ስሙ የተመስገን ይሁን፡፡ ይህንን የሚመስል ብዙ የተንከራተተ ህይወት አሳልፍያለው፡፡ ዘፋኝ ብሆን እኮ እሸለም ነበረ፡፡ ሬድዮ ጣብያዉም፤ ቴሌቪዥኑም፤ ካድሬዉም ትልልቁም ትንንሹም ያጨበጭብልኝ ነበር፡፡ ግን እግዚአብሔር በተረገመበት፤ እግዚአብሔር የለም በተባለበት ሃገር ውስጥ እግዚአብሔር አለ የሚል ከሆነ፤ እግዚአብሔር ቅዱስ ነው የሚል ከሆነ አንተ እርኩስ ነህ የሚለው ነው የሚበዛውና እውነታው ይሄ ነው፡፡ ይሄን የሚመስል ሁኔታ ውስጥ ነው ያሳለፍነው፡፡ አልጋ በአልጋ የሆነ መንፈሳዊ ህይወት የለም፡፡ አልጋ በአልጋ የሚሆነው ለአርቲስቶች ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔር ማስተዋሉን ይስጠን፡፡

Thursday, February 25, 2016

ድንቅ ተዓምር በ ለጀት ኪዳነምህረት

ማክሰኞ 16/06/2008 ዓ.ም የመቤታችንን ክብረ በዓል ለማክበር ወደ ለጀት ኪዳነምህረት ሂጀ ሳለ ትልቅ ተዓምር አየሁ ። እግዚዐብሔር ይመስገን ደስ ይበላችሁ ። ስሟ ቃልኪዳን የምትባል ሰው ታማ ያልሄደችበት ሐኪም ፀበል የለም እና አሁን ሰልችቷት እቤቷ ዋድ አካባቢ ነበር ያለች። የህመሙ አይነት ከሆዷ ከጉልበቷ አካባቢ ሁሌ የሚቆርጣት ሳይታይ ደም ይፈሳት ነበር።የፈሰሰው/የተቆረጠው/ ለምጡ አሁንም አለ።ነገር ግን ዛሬ ታሪክ ተለወጠ ክብር ለናታችን ቅድስት ድንግል ማረያም።አንድ በፀበል የምታውቃት ጓደኛዋ ደውላ ዛሬ ኪዳነምህረት ንግሷ ስለሆነ ነይ አክብሪስትለት እሷም ከዋድ መጣች።መጥታ ታቦት እንደገባ ፀበል እንድትጠጣ በትንሽ ሀይላንድ ስጥተዋት ከቤተክርስትያን አጥር ወጥታ ስትጠጣ በትውኪያ 2/ሁለት/ምላጭ ወጥቶላታል። ክብርምስጋና ለአምላክ እናት።ስለ ታምሩማወቅ የሚፈልግ። 0911593144 ይደውሉ።በበለጠ መሔድ የሚችል እሁድ እቦታው ሒዶ ታምሩን ይስማ። ኦርቶዶስ ለዘላለም ትኑር

አንዲት እህት ከሆዷ ውስጥ ጥቁር ወፍ ወጣላት




የኪዳነ ምሕረት ተዓምር

የካቲት 16/2008 ዓም ኪዳነ ምሕረት በዓል ቀን አረብ አገር የምትኖር እህታችን የተደረገውን ተዓምር እንዲህ አቅርባዋላች:: ከሆዷ የወጣላት አውሬ ምስል ከነድምጹ አቅርባለች:: ድንቅ ስራውን ይመስከሩ::

የሸንኮራ ቅዱስ ዮሃንስ ወልደ ነጎድጓድ ጸበል ታምር 

 

Wednesday, February 24, 2016

መምሕር ግርማ ከአገልግሎት የታገዱበት ደብዳቤ

መምህር ግርማ ወንድሙ
ከ ላይፍ መጽሄት ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ
የኤልያስ መንፈስ በኤልሳ እንዳደረ ሁሉ የፈለገው ሁሉ ያገኛል፡፡ እኔም የማስተምረው እኮ ክርስቲያኑ ራሱን ችሎ እንዲቆም ነው፡፡ እኔ ነገ የማልፍ ሰው ነኝ ዘላለም አልኖርም ግን ክርስትያኑ ጠላቱን እንዲጋፈጥ ፤ ክፉ መንፈስ እንዲያሸንፍ ፤ የዲያቢሎስ ትውልድ መሆኑ እንዲቆም ፤ ከዚያም በላይ የመንፈስ ቅዱስ ስራ የእግዚአብሔር ክብርና ኃይል እየጨመረ እንዲመጣ ፤ የአለም ጥበብ የእግዚአብሔር ልዩ አሰራር አውቀው ክርስቲያኖች በረከት ውስጥ እንዲገቡ ነው፡፡ ፍላጎቴ ግን እግዚአብሔር በተረገመበት፤ እግዚአብሔር የያድንም የለም በተባለበት ሃገር ውስጥ እግዚአብሔር አለ የሚል ከሆነ፤ እግዚአብሔር አዳኝ ቅዱስ ነው የሚል ከሆነ አንተ እርኩስ ነህ የሚለው ነው የሚበዛውና እውነታው ይሄ ነው፡፡ ይሄን የሚመስል ሁኔታ ውስጥ ነው ያሳለፍነው አሁንም እያሳለፍን ያለነው
ያደረጉት ቃለ ምልልስ..
ላይፍ፡- ሁላችሁም የእግዚአብሔር ቃል የእመቤታንን በረከት የምታስተምሩበት ቤተክርስቲያን ለምን እንዲህ አይነት መከፋፈል መጣ ብለው ያስባሉ ?
መምህር ግርማ፡- በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ እንክርዳድ በስንዴው መሀል እንደሚዘራው ሁሉ ያም በቤተክርስቲያን ውስጥ አለ፡፡ ገበሬው መልካም ስንዴን ዘራ የሚለው ከውጭ አይደለም፡፡ ዘሩ እዚያው ቤተክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ በቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ህይወትና በልቦና ውስጥ መጀመርና በስጋ ህይወት መጀመር ልዩነት አለው፡፡ አምኖ መጀመርና ሳያምኑ መጀመር የእዚያን ያህል ነው፡፡ ሰሞኑን ወደ ቤተክርስቲያን ገብተው የሚኖሩ በጣም ብዙ ናቸው፡፡ እነዚህ ከተለያዩ የአስማት ስራ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ሲጠጉ ብዙ መልካም ነገር አይጠበቅባቸውምና ይህንን የሚመለከት ‹‹በማለዳ መያዝ›› የሚለው መጽሀፌ ላይ ሰፋ ባለ መልኩ አስቀምጬዋለሁ፡፡ ንጹህ የአምልኮት ፍላጎትና እንዲሁ ደግሞ በደብዛዛው በሚመላለሱ ሰዎች መካከል ዲያቦሎስ በደንብ ይሰራል፡፡ በተለይ ኦርቶዶክስ እምነት ላይ ሰይጣን ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል፡፡ ከታሪክ እውነታም አንጻር እነዚህ ሰዎች ህይወት ውስጥ የተለየ እድል አለ፡፡ ገብቶ ይቀመጥና በጎው መጥላት መልካሙን እንደክፉ ማየት ማሳደድ ያለው መናፍቆች ላይ ሳይሆን እኛ ጋር ነው ያለው፡፡ ይህ ደግሞ የሃይማኖቱ አንዱ በረከት ነው፡፡ ለምን ፈሪሳውያንን ክርስቶስ በመጣ ጊዜ እምነቱን ተራ ወግና ተራ የሆነ የይስሙላ አድርገውት ነበር፡፡ ያ ሂደት ደግሞ እንደዚሁ በቆየን ቁጥር የአዲስ ኪዳንንም ህይወት እንደዚያ ነው የሚሆነው፡፡ ወደ ፈሪሳውያን ጠላት ይሄዳል፡፡ በዚህ ጊዜ እውነቱ እየጠፋ በቤተክርስቲያን ውስጥ ጣልቃ ይገባሉና ያንን ለመለየት የመንፈስ ቅዱስ ስራም የአጋንንት የቅንነትም ስራ ስለሚያስፈልግ ዛሬ ያ ቅንነቱ እና በጎነቱ በክፋት በተንኮል በምቀኝነት የተሞላ ስለሆነ ያ ሂደት ሊያደርገን አልቻለም፡፡
ላይፍ፡- ብዙ ሰባኪያን ወደ እርስዎ ፕሮግራም የማይመጡት ለምንድነው?
መምህር ግርማ፡- ይህንን የፈውስ ሂደት ስላለመዱት ልክ እንደ መተት እንደ ጠንቋይ አሰራር አድርገው እስከዛሬ ድረስ ሲያወሩ እንደቆዩ ያው የተለመደ ነገር ነው፡፡ስላልተለመደ እንግዳ ነገር ነው የሆነው፡፡ በተለይ በግለሰብ ጸጋ አልተለመደም፡፡ ይህንን ያልተለመደ ነገር እንዲህ ሲወጣ ሁሉም እየተረባረበ ማጨለም ነው የሚፈልገው፡፡ የእግዚአብሔር ስራ ደግሞ ስለማይጨልም ሂደቱን ጠብቆ ይበራል፡፡ ከዚህም በፊትም የተደረጉብኝ ዘመቻዎች ብዙ ናቸው ይህ ብቻ አይደለም፡፡ ይህ እንዲያውም የመጨረሻው ደካማ ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ሰዎች መንፈሳዊ አንድነታቸው በክፉ ሰዎች መንፈስ ተመቷል፡፡ በራስ እይታም ተመቷል፡፡ የምቀኝነት መንፈስ አጠናክረው በመያዛቸው ምክንያት የእግዚአብሔር ጸጋ በረከት መለያ መንፈስ አጥተዋል፡፡ አንድነትና ተስማምቶ መዝለቅን በዚህ ዘመን ውስጥ የምንጠብቀው ጉዳይ አይደለም፡፡ ግን እውነት ዞሮ ዞሮ ደረጃዋን ጠብቃ ስለምትወጣ ያን ያህል አስጊ አይደለም ማለቴ ነው፡፡
ላይፍ፡- እርስዎ አለኝ የሚሉት የፈውስ ጸጋ ከየት የመጣ ነው ይላሉ ?
መምህር ግርማ፡- ይህ እኮ አንድና ሁለት ነው እንደሚባለው አይነት ፎርሙላ ወጥ አድርገህ የምታሳየው ነገር አይደለም፡፡ ይህ በጸሎት በስግደት በቅዱስ ቁርባን በመመጽወት ከሰማይ የሚለቀቁት እንጂ ከማንኛውም ሰው የምትገዛው ወይም የምትለውጠው ትርፍ ያለው ነገር አይደለም፡፡ ይህ ከሰማይ የሚሰጥ እንጂ በስጋዊ ጥበብባ ዘዴ ወይም ምርምር ወደ ላብራቶሪ የሚመጣና የሚገኝ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሔር አሰራር ነው፡፡ የእግዚአብሔር አሰራር ደግሞ አለምም ሆነ ስጋውያን አያውቁትም፡፡ መንፈሳውያንም ተቸግረዋል፡፡
ለዛ ነው እምያሳድዱኝ በዚህ ዘመን ያሉ የገዛ አባቶቼ እንኳን ሳይቀሩ ይህንን መንፈሳዊ ጸጋ ለመቀበል በጣም ይቸገራሉ፡፡ ምክንያቱም ከእኛ በኩል ካፈሰሰ ነው እኮ አሁን ችግሩ፡፡ ከእኔ በኩል ካልፈሰሰ እንዴት በዚህ ዘመን ከእግዚአብሔር ይመጣል ፤ የሚል ዋጋ ቢስ እና ተስፋ አስቆራጭ የመንፈሳዊ ህይወት ጉዞን የለመዱት ባህሪ ለማንጸባረቅ ሲሞክሩ ነው አሁን ነገሮች ወደዚህ አይነት አጣብቂኝ ውስጥ የሚገቡት፡፡
ላይፍ፡- እርስዎ ተሰጥቶኛል የሚሉት የመንፈስ ጸጋ ስያሜ ሰጥተውታል ?
መምህር ግርማ፡- እንደዚህ ያለ ነገር የለም እንጂ ምን ስያሜ ይሰጠዋል ? ክፉ መናፍስን የሚቃወም የእግዚአብሔር መንፈስ ነው፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስና ክፉ መንፈስ ደግሞ አይገናኙም፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ስጦታ ደግሞ ክፉውን መለየት ፤ ክፉው ማስወገድ ነው፡፡ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ አጋንንትን አወጡ ይል የለም እንዴ? በአሁኑ ዘመን አጋንንት አስገቢ ቢባል ሁሉም ይወደኛል፡፡ አጋንንት ማስወጣት እኮ ነው የተለየ ጠንቋይ ያደረገኝ፡፡
ላይፍ፡-አለኝ የሚሉት የመንፈስ ጸጋ ወደ ሌላ ሰው ማስተላለፍ ይችላሉ ? ወይስ እርስዎ ጋር ነው ሊቀር የሚችለው ?
መምህር ግርማ፡- የኤልያስ መንፈስ በኤልሳ እንዳደረ ሁሉ የፈለገው ሁሉ ያገኛል፡፡ እኔም የማስተምረው እኮ ክርስቲያኑ ራሱን ችሎ እንዲቆም ነው፡፡ እኔ ነገ የማልፍ ሰው ነኝ ግን ክርስትያኑ ጠላቱን እንዲጋፈጥ ፤ ክፉ መንፈስ እንዲያሸንፍ ፤ የዲያቢሎስ ትውልድ መሆኑ እንዲቆም ፤ ከዚያም በላይ የመንፈስ ቅዱስ ስራ የእግዚአብሔር ክብርና ኃይል እየጨመረ እንዲመጣ ፤ የአለም ጥበብ ከእግዚአብሔር ልዩ አሰራር አውቀው ክርስቲያኖች በረከት ውስጥ እንዲገቡ ነው፡፡ ፍላጎቴ
ላይፍ፡- አባቶች እርስዎ የሚሰጡት መንፈሳዊ ጉባኤ ተገኝተው በረከት ይሰጡ ነበር ወይ ? መምህር ግርማ፡- እኔ በማገለግለው ላለመገኝት ብዙዎች ይሸሻሉ ተሰልፈው ዝቅ ብለው የህዝብን ችግር ለማየት እስከ አሁን በጎ ህሊና አላገኝሁም፡፡ እንደ አቡነ እስጢፋኖስ የጅማው ኃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አይነቱ በተደጋጋሚ የህዝቡን ችግር ተረድተው በተደጋጋሚ ወደዚያ እየሄድኩ ሳገለግል መንፈሳዊ ድጋፋቸውን ለህዝቡ ካለው ችግር ለልማቱም ከማሰብ ቢርሌ የሰጡት ቦታና ስራ አለ፡፡
ላይፍ፡- አባቶች እርስዎ የሚሰጡት መንፈሳዊ አገልግሎት አስተያየታቸው ምንድነው ? መምህር ግርማ፡- ብዙዎች ይህንን መንፈሳዊ ድርሻ ለመወጣት በማደርጋቸው ጥረቶች ላይ በጎ ድጋፍ የላቸውም፡፡ ከተለያዩ አይነት መንገድ ለመዳንም ይሰጣሉ፡፡ ነገር ግን አንዳዶች እንዲያውም የሸናሻም መተት ይህን ያደርጋል፡፡ የሸናሻም አስማት ይህንን ይሰራል እያሉ ለአስት አሰራር ትልቅ ድጋፍና የሰይጣን አሰራር ትልቅ ሞራል ሲሰጡ ነው የሚሰማው፡፡
ላይፍ፡- ይህንን እርስዎ የሚያደርጉትን መንፈሳዊ አገልግሎት ሌሎች አባቶች ያምኑበታል ?
መምህር ግርማ፡- እኔም በጣም ግራ የሚገባኝ ዲያቢሎስ የሚያደርገው ጥቃት በመጽሀፍ ቅዱስ በረጅሙ እና በስፋት ጥልቀት ባለው ሁኔታ ገልጿል፡፡ ሐዋርያት አጋንንትን እያወጡ የሰዎችን ደህንነት ሲያበለጽጉ ይታያል፡፡ በቤተክርስያንም እደዚሁ በመንፈሳዊ አገልግሎት በመንፈስ ቅዱስ ስራ እንደሚሰራ ይታወቃል፡፡ እንግዲህ ሰዎች በክፉ መንፈስ አሰራር ወይም አያምኑም አልያም በእግዚአብሔር አሰራር አያምኑም፡፡ ይናገሩታል ያስተምሩታል ግን ይህው እግዚአብሔር አዳነ ሲባል ግን አያምኑትም በዚህ መንታ መንገድ ላይ መታየት አሁን አይቻልም፡፡ ምክንያም የእግዚአብሔር ሕዝብ በዲያቢሎስ ተጠቅቷል፡፡ ወይ ዲያቢሎስ እንዲበላ ማድረግ ነው አልያም በቤተክርስቲያን መንፈስና ጸጋ ህዝቡ ችግር ውስጥ ገብቶ ችግሩን ማየት ነው፡፡ ገለልተኛ ሆኖ መኖር አሁን አሁን ጊዜው አይደለም፡፡ ስለዚህ ያምናሉ አያምኑም የሚለው ነገር እርሳው እኔን ቢረዱኝ ደስ ባለኝ፡፡ በተሰጣቸው ጸጋ ክፉ መንፈስ ነው ካሉ የእኔን መንፈስ ማወጣት መቻል፡፡ ሁሉም ቢተባበሩኝ መልእክት አስላልፋለሁ ፡፡ እንዲያውም በቤተክርስቲያን ይኖር የነበረ አስማተኛ መንፈሱን አስወጣንለት ብለው ለአለም ዜና ቢያቀርቡ ደስ ባለኝ ነበር፡፡
ላይፍ፡- ቤተክርስቲያኗ ወታደርና ነጋዴ የቤተክርስቲያን አገልጋይ አይሆንም የሚል ሕገ ደንብ አላት፡፡ እርስዎ ግን መንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ከመግባትዎ በፊት ወታደር እንደነበሩናይውራል ስለዚህ ምን ይላሉ ?
መምህር ግርማ፡-ዛሬ ሰማዕቱ ሀገር ጠባቂ የምንለው ቅዱስ ጊዮርጊስም የመቶ አለቃ ወታደር ነበር፡፡ ግብጽ ውስጥ ያሉ ብዙ ታላላቅ አባቶችም እንደዚያው ናቸው፡፡ በአሁንም ዘመን ያሉ ብዙ መነኮሳቱ እስከ ጳጳሳቱ ወታደር የነበሩ ናቸው፡፡ ወታደር ማለት የእግዚአብሔርን ስራ አይሰራም ማለት አይደለም ፡፡ እኔ ደግሞ ልቀድስ ላቁርብ አላላኩም ፤ በተሰጠኝ ጸጋ ላገልግል ነው ያልኩት፡፡ ይህንን እንደ አንድ እንደ ትልቅ ነገር ማንሳት በራሱ ምንን ያመለክታል ፤ ምቀኝነትን ነው ፤ ያው ከደማችን ውስጥ የተለመደ ምቀኝነት ስላለ እንጂ ከነዚህ ሁኔታዎች በሙሉ የእግዚአብሔር ስራ እንዳይሰራ የሚያደርጉት አይደለ። ፡፡ ዘፋኝ ብሆን እኮ እሸለም ነበረ፡፡ ሬድዮ ጣብያዉም፤ ቴሌቪዥኑም፤ ካድሬዉም ትልልቁም ትንንሹም ያጨበጭብልኝ ነበር፡፡ ግን እግዚአብሔር በተረገመበት፤ እግዚአብሔር የያድንም የለም በተባለበት ሃገር ውስጥ እግዚአብሔር አለ የሚል ከሆነ፤ እግዚአብሔር አዳኝ ቅዱስ ነው የሚል ከሆነ አንተ እርኩስ ነህ የሚለው ነው የሚበዛውና እውነታው ይሄ ነው፡፡ ይሄን የሚመስል ሁኔታ ውስጥ ነው ያሳለፍነው፡፡ አልጋ በአልጋ የሆነ መንፈሳዊ ህይወት የለም፡፡ አልጋ በአልጋ የሚሆነው ለአርቲስቶች ብቻ ነው፡፡
ላይፍ፡- እርስዎን አስማተኛ እና ጠንቋይ ናቸው የሚሉዎት ሰዎች ምላሽ ምንድነው ?
መምህር ግርማ፡- እኔ አስማተኛ ከሆንኩ እኔ ጋር መጥተው አስማቱን ማውጣት ነው፡፡ እኔ ጋር መጥተው አስማቴ የት ጋር እንደተቀበረ ፈልገው ማውጣት ነው፡፡ ክንዴ ላይ ወይም እግሬ ላይ ወይም ጭንቅላቴ ላይ እንዳለ ደንበኛ ራጅ ይዘው መጥተው ፈልገው ማውጣት፡፡ ወይም መንፈስ ከሆነ ያስወጡልኝ፡፡ ቢረዱኝ እኮ ለእኔም ደስ ይለኛል፡፡ ግልግል ነበር፡፡ እስቲ አስማቴን ኑ እና አስወጡልኝ እባካችሁ ስለ እግዚአብሔር ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ብዬ እለምናችኋለሁ፡፡እንኳን እኔ ይልቅ እና እኔ ባስተማርኩት መስረት እንኳን ብዙዎች ሲፀልዩ ጎደኞቻችው እየራቅዋቸው እንደሆነ ይነግሩኛል 2ተኛው የመምህር ግርማ አስማተኛ የሚባል ቅፅል ስም ይሰጣቸዋል ለምን የመንፍስ አንድነት የላቸውም እርኩሱ ከ ቅዱሱ እንደማይስማማው ሁሉ መባረክ ስትጀምር ለእግዚአብሔር መንበርከክ ስትጀምር ለማይንበረከኩት በቃል ብቻ ለሚኖሩት እራስ ምታት ትሆንባቸዋለህ ይሄ ነው እውነታው!





ኢትዮጵያዊ 350 ሺህ ብር ከኦስትሪያ ለወደቁትን አንሱ የአረጋውያንና የአእምሮ መርጃ ማዕከል ድጋፍ አደረጉ! ድጋፍ ያደረጉት መንበረ አብርሃም የተሰኙ ኢትዮጵያዊ ከኦስትሪያ ሲሆን ከዚህ ቀደም መምህር ግርማ ወንድሙ ለበጎ አድራጎት ድርጅት ድጋፍ ያደረጉትን ፕሮግራም ከተመለከቱ በሆላ እንዲሁም በአባታችን አስተባባሪነት የአባታችን የወንጌል ተማሪ የሆነችው በተወካያቸው በአቶ ታሪኩ ተገኝ አማካይነት ተናግረዋል፡፡ በዚህም አማካይነት 350ሺህ ብር የሚያወጣ ዘመናዊ 65 አልጋዎችን ከነሙሉ ፍራሾች ለአረጋውያኑ ተወካይ በዛሬው ዕለት አስረክበዋል!






ዝቅ ብሎ መምሕር ግርማ ወደ አገልግሎት የተመለሱበት ደብዳቤ ይታያል:: በቅርብ ግን ይህ አገልግሎታቸው በ አባ ማቲያስ 30-06-2008 የተጻፈ የ እገዳ ደብዳቤ እንደሚከተለው ነው::




መምሕር ግርማ ወደ አገልግሎት የተመለሱበት ደብዳቤ

መምህር ግርማ ወንድሙ በደርሰባቸው ክስ ምክኒያት አገልግሎት ተቋርጦ እንደነበር የሚታወስ ነው:: መምህር ግርማ በወስ ጥቅምት 30/2008 ከተለቀቁ በኃላ የካቲት 9/2008 ከ ከደቡብ ም እራብ ሸዋ ሀገረ ስክበት የሥራ ምደባ ተደርጎላቸዋል:: በዚህም ምክኒያት የካቲት 19/20 በ ጀሞ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን አገልግሎት ይሰጣሉ::

ጥቅምት 30 ፣ 2008 ከደቡብ ምእራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት የካቲት 9/2008 የተጻፈላቸው ደብዳቤ እንደሚያሳየው ወደ አገልግሎት ተመልሰዋል::

Wednesday, February 10, 2016

በንብና ነብር የምትጠበቀው ሥዕለ ማርያም “ወይኑት”

ኅዳር 10 ቀን 2006 ዓ.ም. 
በእንዳለ ደምስስ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታላላቅ ገዳማት መካከከል በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ውስጥ የሚገኙት የመርጡለ ማርያም እና ደብረ ወርቅ ገዳማት በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ፡፡ ሁለቱም ገዳማት ጥንት መሥዋዕተ ኦሪት ይከናወንባቸው የነበረና ታላላቅ ታሪካዊ ቅርሶችንም ለትውልድ በማስተላለፍ ረገድ ትልቁን ድርሻ ከያዙት ቅዱሳት መካናት መካከል ይመደባሉ፡፡

መስከረም 29 ቀን 2006 ዓ.ም. በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ማርቆስ ጥሪ መሠረት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የሚመራና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የሚገኙበት የልዑካን ቡድን መርጡለ ማርያም ገዳም አዲስ ለሚሠራው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን የመሠረት ድንጋይ ለማኖር፤ እንዲሁም በደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም የተገነባውን መንበረ ጵጵስና ለመመረቅና ለዘመናዊ ትምህርት ቤት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ለማኖር ከሄደው ልዑክ ጋር ተጉዣለሁ፡፡
በመርጡለ ማርያም ገዳም የነበረን ቆይታ አጭር በመሆኑ መረጃዎችን ለማሰባበሰብ የጊዜ እጥረት ስላጋጠመኝ አልተሳካልኝም፡፡ በደብረ ወርቅ ገዳም ቆይታዬ ከቋጠርኳቸው መረጃዎች መካከል ቅዱስ ሉቃስ ከሣላቸውና ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ቅዱሳት ሥዕላት መካከል በንብና ነብር የምትጠበቀው ሥዕለ ማርያም /ምስለ ፍቁር ወልዳ/ “ወይኑት” ስለተሰኘችው ሥዕል ጥቂት ላካፍላችሁ፡፡ ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳምን ላስቀድም፡፡

ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም
ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በእናርጅና እናውጋ ወረዳ ከአዲስ አበባ 290 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ የኦሪት መሥዋዕት ሲሰዋባቸው ከቆዩት ቅዱሳት መካናት አንዷ ናት፡፡ በተለይም ከ250-351 ዓ.ም. መሥዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባት እንደቆየች የጽሑፍ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

የጎጃም አፈ ጉባኤ በነበረው ምሑረ ኦሪት ያዕቆብ አማካይነት መሥዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባት የቆየ መሆኑን በገዳሟ የሚገኙ የኦሪት ሥርዓት ማከናወኛ የነበሩ እንደ መቅረዝ፤ ስንና ብርት የመሳሰሉ ቅርሶች ከመመስከራቸውም በላይ በገዳሟ ውስጥ የሚገኘው የቤተ ክርስቲያኗ የታሪክ መዝገብ ያስረዳል፡፡

weyenuteእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ጋር ወደ ምድረ ግብፅ ስትሰደድ ካረፈችባቸው ቅዱሳት መካናት መካከል አንዷ ደብረ ወርቅ መሆኗንም በድርሳነ ኡራኤል ላይ ተጽፎ ይገኛል፡፡ በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያ የነገሡት ወንድማማቾቹ አብርሃና አጽብሃ ክርስትናን እያስፋፉ ከቦታ ቦታ ይዘዋወሩ በነበረበት ወቅት መርጡለ ማርያምን አቅንተው ክርስትናን መሥርተው ወደ ደብረ ወርቅ በመምጣት ከምሁረ ኦሪት ያዕቆብ ጋር ተገናኝተዋል፡፡ ያዕቆብን ክርስትናን አስተምረው የአዲስ ኪዳን ሥርዓትን በመመሥረት “ያዕቆብ ኤጲስ ቆጶስ ዘኢየሩሳሌም ደብረ ወርቅ” ብለው ሾመውታል፡፡

አብርሃና አጽብሃ ደብረ ወርቅ ላይ ቤተ ክርስቲያን ሳይሠሩ ዐረፍተ ሞት ስለገታቸው በእግራቸው የተተካው ዐፄ አስፍሐ ያልዝ በ351 ዓ.ም. ወደ ደብረ ወርቅ በመምጣት ቤተ ክርስቲያኗን አሰርቷል፡፡ የደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም በዮዲት ጉዲት በመቃጠሏ በ1372 ዓ.ም. በዐፄ ዳዊት የገንዘብ ድጋፍ አባ ሰርፀ ጴጥሮስ በተባሉ አባት አማካይነት በድጋሚ ተሠርታለች፡፡ ከጊዜ በኋላም ቤተ መቅደሷን ዐፄ ገላውዴዎስ በኖራና ድንጋይ ሲያሠሯት፤ ቅኔ ማኅሌቷ ደግሞ በስክ እንጨት ካለምንም ምሥማር በዐፄ ተክለ ጊዮርጊስ ተሠርታለች፤ በ1963 ዓ.ም. ዐፄ ኃይለ ሥላሴም አሳድሰዋታል፡፡

ቤተ ክርስቲያኗ 44 ቆመብዕሴ/አምድ/፤ የውጪና የውስጥ 11 በሮች፤ 36 መስኮቶች ሲኖሯት የግድግዳ ላይ ሥዕሎቹ ዐፄ ዮስጦስ /1704 ዓ.ም./፤ 1873 ዓ.ም. የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ልጅ የሆኑት ራስ ኃይሉ አስለውታል፡፡ በቤተ ክርስቲያኗ ዘመናዊ ሙዚየም ውስጥ በርካታ ታሪካዊና ጥንታዊ ቅርሶችም ይገኛሉ፡፡

“ወይኑት” ቅዱስ ሉቃስ የሣላት ሥዕለ ማርያም
ዐፄ ዳዊት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተሰቀለበት መስቀል ጋር ወደ ኢትዮጵያ ካመጧቸው የቅዱስ ሉቃስ ሥዕላት መካከል “ወይኑት” የተሠነችው ሥዕል አንዷ ስትሆን ዐፄ ዘርዓweyenute 2 ያዕቆብ ለደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም አበርክተዋል፡፡ እስከ ዛሬ ድረስም ተጠብቃ ትገኛለች፡፡ በ1660ዎቹ ዓ.ም. በዐፄ አእላፍ ሰገድ /ፃድቁ ዮሐንስ/ ለወይኑት ማስቀመጫ እቃ ቤት ይሆን ዘንድ ባለ ሁለት ፎቅ ሕንፃ በድንጋይና በኖራ በማስገንባት ጣሪያውን የሣር ክዳን በማልበስ አሠርተውላታል፡፡ ፎቁ ላይ ትናንሽ 8 መስኮቶችም ይገኛሉ፡፡

ሥዕለ ሉቃስ “ወይኑት”ን የሚጠብቁ ነጫጭ ንቦች የሚገኙ ሲሆን ጥቋቁር ንቦቹ ደግሞ ከመስኮቶቹ እየወጡና እየገቡ መመልከት የተለመደ ነው፡፡ ንቦቹ ከሕንፃው መሠራት ጋር እንደገቡ የሚነገር ሲሆን ማሩ እስካሁንም ተቆርጦ አያውቅም፡፡ ወይኑት በዓመት ለሦስት ጊዜያት ሕዝቡን ለመባረክ ወደ ቤተ መቅደስ ትወሰዳለች፡፡ መስከረም 21፤ ጥር 21 እና ነሐሴ 16፡፡ ሥዕሏ ወደ ቤተ መቅደስ ሥትወሰድ ንቦቹ አጅበዋት የሚሄዱ ሲሆን ስትመለስም አብረዋት ይመለሳሉ፡፡ ንቦቹ ሕዝቡን የማይተናኮሉ እንደመሆናቸው በተንኮል ወይም ለሥርቆት የመጣ ሰው ካለ ግን እየነደፉ እንደሚያባርሩ ከዚህ በፊት ከተደረጉት ገቢረ ተዓምራት በመነሳት ይገለጻል፡፡

ወይኑትን የሚጠብቁ ከንቦቹ በተጨማሪ ነብሮችም በሕንፃው ጣሪያ ላይ ይገኛሉ፡፡ ቀን እዚያው ተኝተው የሚውሉ ሲሆን ምሽት ላይ ምግብ ፍለጋ እንደሚወጡ ይነገራል፡፡ በአካባቢው የሚገኙ በጎች ወደ ቤተ ክርስቲያኗ ቅጥር ከገቡ ከነብሮቹ ጋር እንደሚጫወቱና እንደማይተናኮሏቸው የዓይን እማኞች ያስረዳሉ፡፡

የዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ወታደር ሥዕለ ሉቃስ /ወይኑትን/ ለመሥረቅ ሞክሮ ንቦቹ ነድፈው እንዳባረሩት፤ እንዲሁም ዐፄ ዮሐንስ ከደርቡሽ ጋር ባደረጉት ጦርነት ሥዕለ ማርያምን /ወይኑት/ ይዘው ለመዝመት ባደረጉት ጥረት ንቦቹ ወታደሮቻቸውን- በመንደፍ አስጥለዋታል፡፡ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዳልሆነ የተረዱት ዐፄ ዮሐንስ ሥዕሏን ወደነበረችበት መልሰው እንደዘመቱ የቤተ ክርስቲያኗ የታሪክ መዝገብ ያስረዳል፡፡ የፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት የደብረ ወርቅ ማርያም ገዳምን ለመዝረፍ ዕቃ ቤቱን ሰብረው ለመግባት ያደረጉት ጥረት እንዳይሳካ በማድረግ ጠባቂ ንቦቹ ወታደሮቹን በመንደፍ እንዳባረሯቸው መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ 

ይቆየን

Friday, February 5, 2016

Monday, January 4, 2016

ፃድቃኔ ማርያም - ድንቅ ተአምር

ዛሬ ፃድቃኔ ማርያም ሄጄ በአይኔ ያየሁትን ተአምር ልፅፍላችሁ ወደድኩኝ፡፡ ቀኑ ቅዳሜ ነው ፤ ሰዎች አብዛኛውን ጊዜ ወደ ፃድቃኔ ለመሄድ የሚነሱበት ቀን ስለሆነ መጀመሪያ የሚወጣው አውቶቡስ እንዳያመልጠን ከባለቤቴ ጋር በጠዋት ነበር አውቶቡስ ተራ የደረስነው ፤ ነገር ግን ሰው እዛ ያደረ ይመስል 12፡00 ላይ አውቶቡሱ ሞልቶ መንቀሳቀስ ጀምሮ ነበር፡፡ ባለቤቴም ‹‹አይ በዚህም ሰዓት ደርሰን አመለጠን ይገርማል ተወው ባክህ እመቤቴ እንደፈቀደች›› አለችኝና ሁለተኛው አውቶቡስ ላይ ገባን፡፡ ይህኛው ደግሞ ቀጥታ ዘላቂ ሰው ስላጣ የመንገድ ሰዎችንም በመጫን ነበር የሞላው፡፡ ጉዞ ወደ ፃድቃኔ ማርያም ፤ ውዳሴዋን ደግመን ጉዞ ጀመርን፡፡ መኪናው ሲያወርድ ፤ ሲጭን 9፡00 አካባቢ ደብረ ምጥማቅ ደረስን ፤ እዚህ እንውረድና በአቋራጭ እንሂድ ተባብለን ሰላ ድንጋይ ሳንደርስ ወረድን ፡፡ እቃችንን ለአንድ የሀገሬው ሰው አሸክመን አቋራጩን ተያያዝነው ፡፡ ልጁ እንዲህ አለን ‹‹ ዛሬ ግን ማደሪያ የምታገኙ አይመስለኝም በጣም ብዙ ሰው ነው የመጣው አለን›› :: ‹‹ችግር የለውም ውጪ አንጥፈን እናርፋለን ለመተኛት መች መጣን›› አልነው፡፡

ደጇን ስንረግጥ ልጁ ያለው አልቀረ የወንዶች ማረፊያ ሁለቱም አዳራሽ ከአፍ እስከ ገደቡ ሞልቷል ፤ በረንዳውን ላይ ብናይ የበረንዳው ይብሳል ፡፡ የኔን ማረፊያ ውጭ አነንጠፍንና የእሷን ለማየት ወደ ሴቶች ማረፊያ እያቀናን ሳለ ፤ አንዲት መንፈስ ያደረባት ሴት ፤ እጇም እግሯም በሰንሰለት ታስራ እንዲ እያለች የእመቤታችንን ማዳን ትመሰክራለች ‹‹ ዛሬ ደግሞ ኪዳነምህረት ድንቅ ነገር ሰርታለች ሂዱነና እዩ›› እያለች ለሰዎች ስትናገር እንደ አጋጣሚ እኔም ሰማሁ፡፡ እሷ የጠቆመችን ቦታ ላይ ስንሄድ አንዲት የ12 ዓመት ህፃን ልጅ እና እህትየዋ አንድ ላይ ቆመው ተመለከትን ፡፡ ጠጋ ብለን ምን ተደርጎላቸው ነው ስል ስጠይቅ ‹‹ የዚች ህፃን አይኗ በራላት›› ሲሉ ነገሩን፡፡ ለኔ የተደረገልኝን ያህል ደነገጥኩኝ፤ በጣምም ደስ አኘኝ፡፡ እህትየዋ የምትይዘውን የምትጨብጠውን ነገር አጥታ ነበር ፡፡ ታናሽ እህቷ የተደረገላትን ነገር እያየች ከአእምሮዋ በላይ ስለሆነ እና ደስታው ፈንቅሏት ታለቅሳለች ፤ እኛም ገርሞን ማደሪያችንን ትተን ልጅቷ ጋር ረዥም ደቂቃዎች ስለሁኔታ ለመስማት እዛው አረፍ አልን ፡፡ እህትየዋም ሰዎች ጥያቄዎችን ሲጠይቋት እንዲህ አለች ፡-

‹‹ ቤት ውስጥ ከእኩያዎቿ ጋር ስትጫወት የበረንዳ ብረት አይኗን መታት ፤ ለጊዜው ከማበጥ ውጪ ምንም አልሆነም ነበር ፤ ነገር ግን በጊዜ ሂደት አይኗ እያበጠ መጣ ፤ እይታዋንም ጋረዳት ፤ ትምህርቷንም አቋርጣ ለ6ወር ያህል ህክምና ፍለጋ አሉ የተባሉ የአይን ስፔሻሊስቶች ጋር ብራችንን አውጥተን ሄድን ፤ መፍትሄ ግን ሊመጣ የልጅቷም አይን ማየት ግን አልቻለም ፤ ቤተሰባችን ጭንቅ ውስጥ ገባ ፤ በመጨረሻ እመቤቴ እንዳደረገች ታድርጋት ብይ እዚህ ይዣት መጣሁ ዛሬ ሶስተኛ ቀናችን ነው ፤ ለሶስት ቀን ያህል ፤ ጠዋት ተሸክሜአት ጸበል እወስዳታለሁ ፤ እምነቱን ከፀበል ጋር ደባልቄ አይኗ ዙሪያው ላይ እቀባታለሁ ፤ ይህው እናንተ እንደምታዩት እግዚአብሄር ፈቅዶ ዛሬ አይኗ ሊያይ ችሏል›› ብላ ለቅሶ፡፡

‹‹ሁሉን የምትገዛ ጌታ አምላክ ሆይ፥ ሥራህ ታላቅና ድንቅ ነው›› ዮሀንስ ራዕይ 15 3-4 ፤ ‹‹ይህች ከእግዚአብሔር ዘንድ ሆነች፥ ለዓይናችንም ድንቅ ናት።›› መዝሙረ ዳዊት118፥23 ከማለት ውጪ ሌላ ምን ይባላል፡፡አምኖ የመጣ እንዲህ ይደረግለታል ፤ ብዙዎቻችን ግን እግዚአብሔር ቤት ስንሄድ በሁለት ልብ ሆነን ነው ፤ ስንመለስም ከሁለት ያጣ የምንሆነው ለዚህ ይመስለኛል፡፡
ያየነውን ነገር ማመን እስኪያቅተን ድረስ እየተገረምን ማረፊያ ፍለጋ ስንንቀሳቀስ ሰዎች ተሰብስበው አየን ፡፡ ሁሌ ማታ 11፡00 ላይ በወንዶች ማረፊያ አካባቢ እና በሴቶች ማረፊያ አካባቢ አዲስ ለመጡ ሰዎች የቦታውን ስርዓት ፤ ምን እንደሚደረግ ፤ ምንስ እንደማይደረግ አባቶች ለ30 ደቂቃ ያህል ያስረዳሉ፡፡ ጠጋ ስንል ተረኛው አባት እንዲህ ሲሉ ነገሩን፡-

‹‹ ይህውላችሁ ልጆች ሀገር አቋርጣችሁ ከተለያየ ቦታ እዚ የመጣችሁት እናንተ ፈልጋችሁ ብቻ አይደለም ፤ እግዚአብሔርም ፈቅዶላችሁ ጭምር ነው፡፡ ስለዚህ እሱ ፈቅዶ እና ወዶ እስካመጣችሁ ድረስ የመጣችሁበትን አላማ የሚያስተጓጉል አንዳች ነገር ማድረግ የለባችሁም ፤ ይህ ቦታ የምህላ ፤ የፀሎት ፤ የሱባኤ ቦታ ነው ፤ እዚህ ቦታ ላይ ከእናንተ የሚጠበቅባችሁ ነገር አለ እርሱም ፡- ወደ ገዳም ስትወርዱ ጫማችሁን አድርጋችሁ መግባት አይቻልም ፤ ሴቶችም ወንዶችም በገዳም ውስጥ ስትመላለሱ ክርስትያናዊ አለባበስ መልበስ አለባችሁ ፤ በማደሪያችሁም ሆነ ገዳም ስትወርዱ ጮክ ብሎ መነጋገር አይቻልም ፤ ብዙ ሰዎች አርምሞ ስለሚይዙ እነሱንም መረበሽ ስለሆነ ይህ አጥብቆ የተከለከለ ነው ፤ የቻለ በቀን ሰባት ጊዜ ፀሎት ማድረስ አለበት፤ ካልቻለህ ግን ሶስቱን ጸሎት ማስተጓጎል የለበትም ፤ ከሰኞ እስከ አርብ ድረስ በሽተኛ ካልሆነ በቀር ምግብ 12 ሰዓት ላይ ነው መብላት የሚቻለው እስከዚያ ሁሌ ጾም ነው(ከበዓለ 50 በቀረ) ፤ የተፈቀዱት ምግቦች ቆሎ ፤ባቄላ ፤ ጥጥሬዎች እና በሶ ከሰኞ እስከ አርብ ሲሆን ቅዳሜ እና እሁድ ዳቦ መብላት ይፈቀዳል ፤ እንጀራ እና ወጥ ገዳም ውስጥ ባላችሁበት ጊዜ መብላት አይቻልም ፤ ጸበል ጠዋ በ11 ይከፈታል ከዚያ በፊት ጸበል መውረድ አይቻልም እስከ ሰባትም ስንትም ሰዓት ይቆያል ፤ እዚህ ቦታ ላይ በዓመት 1ጊዜ ብቻ ነው ቅዳሴ ያለው ፤ ጠዋት ሊነጋ ሲል 11 ሰዓት ላይ ኪዳን ማድረስ ፤ ሲነጋ ትምህርተ ወንጌል መሳተፍ ፤ከ ሰዓት ከ9፡40 ጀምሮ ምህላ ማድረስ አለባችሁ የዛኔ ነው የመጣችሁበትን አላማ እና እናንተ የምትገናኙት ›› እያሉ ብዙ ነገር ነገሩን መከሩን፡፡

እኛ እንኳን ለ3 ቀን ነው የመጣነው ገዳም ውስጥ የሚኖሩ መነኮሳት ይህን ሁሉ ችለው ነው የሚኖሩት? ይገርማል ፤ እግዚአብሔርም አለምን ትተው እሱን ብለው የመጡትን ያስችላቸዋል:: በመጨረሻም ፀሎት አድርገውልን ወደ ማደሪያችን ሸኙን፡፡ ይህን ስመለከት ብዙ ቦታዎች ስንሄድ የቦታውን ስርዓት ሳናውቅ የምናጠፋ ሰዎች እንበዛለን ፤ ልክ እንደ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም ቀን በቀን ሳይሰለቹ እንደዚህ አይነት ነገሮች ሁሉም ቦታ ቢለመድ ጥሩ የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡

የሚቀጥለው ቀን ጠዋት
ለሊት ኪዳን አድርሰን ወረፋው እንዳይበዛ ፀበል ወረድን ፤ ፀበል ተጠምቀን ስናበቃ ለመጠጣት አንዱ ልጅ ጋር ጠጋ ብዬ ቁጭ አልኩ ፤ ጎንበስ ብዬ ሳየው አንዳች ነገር ጉልበቱ ላይ ትልቅ እጢ ቋጥሮ ተመለከትኩኝ ፤‹‹ወንድሜ ምን ሆነህ ነው›› አልኩት፡፡ እሱም ‹‹ ተወኝ ባክህ ልቤ ደንድኖ አልሰማ ብዬ ነው እንዲ የሆንኩት አለኝ››፡፡ አልገባኝም አልኩት ‹‹ሰው ንስሀ ገብቶ ወደ በፊቱ ምግባሩ ከተመለሰ የባሰውን ነው የሚሸከመው አለኝ›› ይባስ ግራ አጋባኝ፡፡ ቀስ ብለህ ልታስረዳኝ ትችላለህ አልኩት፡፡ እርሱም፡-
‹‹ ትውልዴ አዲስ አበባ ነው የ22 አካባቢ ልጅ ነኝ ፡፡ይህውልህ የዛሬ 2 ዓመት በፊት እጠጣለሁ ፤አጨሳለሁ ፤ እጨፍራለሁ ብቻ ምንም ከሀጢያት የቀረኝ ነገር የለም ሁሉን አደርጋለሁ ፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ ሳለሁ የዚያን ጊዜ ጉልበቴ ላይ ከዚህ በፊት ሆኖ በማያውቅ በልክ ትልቅ እጢ ወጣብኝ ፤ ብዙ ቦታ ብሄድ ኦፕራሲዮን መሆንን ነበር እንደ መፍትሄ ያስቀመጡልኝ ፤ እሱን ደግሞ እኔ አልፈልገውም ፡፡ እናቴ እስኪ ፃድቃኔ ሂድ አለችኝ ፤ ‹‹ምን ማለትሽ ነው ዶክተሮች ኦፕራሲዮን እያሉ እዛ ምን ልሰራ ነው የምሄደው›› ብዬ ከእሷ ጋር ተጣላን ፤ ውዬ አድሬ ሳስበው መሄድ እንዳለብኝ ውስጤ ነገረኝ ፡፡ ከአዲስ አበባ ተነስቼ በሶ እና ቆሎ ብቻ በመያዘ ቀጥታ እዚህ ቦታ መጣሁ ፤ አንድን አባት አግኝቼ ችግሬን ስነግራቸው በደንብ አደመጡኝና ‹‹በል አሁን ጸበል እንዳትጀምር ፤ ንስሀ ግባ፤ ቀኖናህን ስትጨርስ መጠመቅ ትችላለህ›› አሉኝ፡፡ እሺ ብዬ ንስሀዬን ከራሴ ላይ አወረድኩኝ ፤ ቀኖናዬን ጨረስኩ ፤ከዚያ ጸበል መጠመቅ ስጀምር ሰዎች እምነት ሲቀቡ ተመለከትኩኝ ፤ ለምን እኔስ አልቀባም ብዬ ጸበሉን ከእምነት ጋር እየደባለኩ ቁስሉን መቀባት በጀመርኩኝ በሶስተኛው ቀን ተሸክሜ የመጣሁትን እጢ በመግል መልክ ከሰውነቴ ወጥቶ አለቀ ፤ ተሸሎኝ ወደቤቴ ስመለስ እማዬ ስታየኝ ማመን አልቻለችም ነበር ፤ አለቀሰች ፤ እመቤቴን ወላዲተ አምላክን ማመስገኛ ቃላት አጣች ፤ እኔም ለአንድ ዓመት ያህል ከቤተክርስትያን አልራኩም ነበር ፡፡ የሆነ ጊዜ ላይ ግን ከቤቱ ጠፋሁ ፤ ወደ ቀደመ ምግባሬ ቀስ እያልኩ ገባሁበት ፤ የተደረገልኝን ነገር ዘነጋሁ ፤ ይህው አሁን ደግሜ የዛሬ ሁለት ዓመት ይዥው የመጣሁትን እጢ አሁን ተመልሶ መጣብኝ ›› ብሎ ሲነግረኝ ሰውነቴን አንዳች ነገር አራደኝ፡፡

ስንቶቻችን ነን ገብተን የወጣን ፤ ውለታውን የዘነጋን ፤ የተደረገልንን ነገር የረሳን ፤ ከሞት አፋፍ ከጠላት ወጥመድ ጠብቆ አሳልፎን ዛሬ ላይ ከቤቱ ሸርተት ያልን? ቤት ይቁጠረው ፡፡ እኔ አይኔ የልጁ እጢ ላይ ነው ፤ ልጁ ደግሞ አይኑ እኔ ላይ ነው ፡፡ ‹‹ አሁን አኮ ቀንሶ ነው ያየህው›› አለኝ ፡፡ ‹‹ሳይቀንስ ባየው የቱን ያህል ነበር?›› ብዬ ራሴን ጠየኩኝ፡፡እንዲህ ሲል ቀጠለልኝ ‹‹ ትላንት ምልክት አይቻለሁ በጥቂት ቀናት ውስጥ አፍስሳ ትጨርስልኛለች ፤ በአውራ ጣቴ በኩል በቢጫ ፈሳሽ መልክ ትንሽ ትንሽ ሲወጣ ተመልክቻለሁ ፤ ከአሁን በኋላ ግን ወደ በፊቱ ማንነቴ እንዳልመለስ እግዚአብሔር ይጠብቀኝ ፤ እርግጠኛ ነኝ አሁን እድናለሁ አለኝ፡፡›› የልጁ እምነት ገረመኝ፡፡ ስንቶቻችን ነን አፋችንን ሞልተን በእምነት ‹‹እድናለሁ›› ማለት የምንችል ፤ እንዲህ ለማለትም ፍጹም እምነት ያስፈልጋል፡፡ የመጣሁበትን ጉዳዬ እረስቼ ቁጭ ብለን ስለራሱ ፤ አዛው ቦታ ላይ ስላየው ተዓምር ሲነግረኝ ሰዓቱ መዝለቁን አላስተዋልኩም ነበር፡፡ መጨረሻ ላይ ‹‹በል እመብርሀን ወላዲተ አምላክ ትርዳህ ፤እግዚአብሔር በምህረቱ ይጎብኝህ›› ብዬው ወደ ማረፊያየ ለመሄድ ብድግ አልኩ ፡፡መሬት መሬት አቀርቅሬ ፤ የነገረኝን ታሪክ ከራሴ ጋር እያቆራኝውት እንደ ውሻ የተፋሁትን ነገር ደግሜ የላስኩበትን ሁኔታዎች ሳወጣ ሳወርድ ምንም ሳላውቀው ማረፊያዬ ጋር ደረስኩኝ፡፡

የ ኪዳነ ምሕረት ተአምር

የወላዲተ አምላክ ድንቅ ተአምር