Friday, April 1, 2016

ምድር ውስጥ ያለችው የታች ጋይንቷ ሰጎዳ ማርያም

አርብ ገበያ ነን፡፡ አርብ ገበያ የታች ጋይንት ወረዳ ዋና ከተማ ናት፤ አዲስ አበባ ከአርብ ገበያ 775 ኪሎ ሜትር ትርቃለች፡፡ የታች ጋይንት ብዙው የአየር ንብረት ወይና ደጋማ ነው፡፡ እንደ ቤተ ልሔም ያሉ ጥንታዊ መንፈሳዊ ስፍራዎች የሚገኙባት ወረዳ ከልዳ ጊዮርጊስ እስከ ደቃ ቂርቆስ አስደናቂ የሆኑ መንፈሳዊ መዳረሻዎች ቢኖሩባትም ብዙም አትታወቅም፡፡ ከራሷ ተሻግሮ የሀገር ልጅ ሊኮራበት የሚገባውን ቀደምት ቅርስ ፍለጋ መጥተናል፡፡ 
ሰጎዳ ማርያም ከአርብ ገበያ 11 ኪሎ ሜትሮች ያክል ትርቃለች፡፡ የደብሯ የጽሑፍ ሰነዶችና የሀገሬው ቃል ጥንታዊነቷን ይገልጻል፡፡ የተተከለችው በአብርሐ አጽበሐ ሲሆን የሰነዶቹ ምስክርነት በ330 ዓ.ም. እንደተሰራች ያትታል፡፡ አቡነ ሙሴ የተባሉ ከግብጽ የመጡ ቅዱስ አባት የተከሏት እንደሆነች ታሪኳ የሚያስረዳው ሰጎዳ ማርያም አስገራሚ በሚባል አሰራር የታነጸችና ከመሬት ተገናኝታ በልዩ ሁኔታ የተፈጠረች ደብር ናት፡፡
ዘመኗን ወደ ኋላ ቆጥሮ ከ 1600 ዓመታት በፊት ይህንን ትሰራ የነበረች ሀገር ለሰራቸው የምትሰጠው ቦታ ምን እንደሆነ ከሚያሳብቁ የሀገራችን መስህቦች አንዷ ናት፡፡ የተነጠፈ ዐለት ድንቅ ቤተ ክርስቲያን የሆነባት ሰጎዳ ማርያም ውስጧ በማህሌትና በመቅደስ የተከፋፈለ ነው፡፡


ምድር ውስጥ ብትሆንም ቀደምት ጥበበኞች የኪነ ህንጻ ጥበበኛነታቸውን ዘመን አሻግረው ማሳየት የቻሉበት አሰራርን ተላብሷል፡፡ ከአናትና በጎን በኩልና በላይኛው ክፍል ለብርሃን ማስገቢያ የተተው መስኮቶች አሉ፡፡ የእነኚህ መስኮቶች አቀማመጥና አቅጣጫ ትክክል መሆኑን በውስጠኛው ክፍል ያለውን በቂ ብርሃን በመመልከት ይደመሙበታል፡፡
የውስጥ ስዕሎቿ ከዐለቱ ህንጻ እኩል ዘመን ባይኖራቸውም እድሜ ያስቆጠሩ ናቸው፡፡ በርካታ ጥንታዊ ቅርሶች የሚገኙባት ሰጎዳ ማርያም የሚበልጠው መገለጫዋ ምንፍስና በመሆኑ ከነገስታት ስጦታዎች ይልቅ የቀደሙት የበቁ አባቶቿ መገልገያ ቁሳቁሶች በክብር ተይዘው የሚጠበቁባት ታሪካዊና መንፈሳዊ ስፍራ ናት፡፡



የኪዳነ ምሕረት ተዓምር 

በደሴ ቁስቋም ማርያም የተደረገ እጅግ ድንቅ ተአምር

 

Friday, March 25, 2016

የእመቤታችን መቃብርና ያረገችበት ጣራ - Tomb of The Virgin Mary

ትውልድ ሁሉ ብፅእት የሚላት በተለይ እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ነብሳችን የምንሳሳላት የእናታችንና የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ መካነ መቃብርና የተነሳችበት/ያረገችበት ቅዱስ ጣራ ከታች በፎቶ እንደምታዩት ይህን ይመስላል። የሚገኘውም እየሩሳሌም ውስጥ በቄድሮን ሸለቆ አካባቢ ነው።የእመቤታችን ምልጃና ፀሎት በረከትና ረድኤት ከኛ ከምንወዳት ልጆቿ ጋር ለዘላለም ይኑር! በረከቱ ለእናንተም ይድረስ። 


ድንግል በእውነት ተነስታለች ምስክሩም ይኸው ያረገችበት ቅዱስ ጣራ በቄድሮን ሸለቆ (Kidron Valley) ይህን ይመስላል። ይህንን ቅዱስና ድንቅ ቦታ ለሌሎች ሼር በማድረግ እናንተም የበረከቱ ተካፋዬች ሁኑ! እኛ የድንግል ልጆች ስለምናምነው ቀጥተኛና እውነተኛ የተዋህዶ ሀይማኖት ትክክለኛ መረጃና ከልብ ስለምንወዳት ድንግል ማርያም የማንጠራጠርበት ምክንያት አለን። በዚህ ለማያምኑትና አማላጂነቷን ለሚክዱ እመቤታችን ልቦናቸውን ትመልስልን!!! 



የቅድስት ድንግል ማርያም በዘይቱን መገለጽ - በአማርኛ ትርጉም