Wednesday, July 6, 2016

መጥምቁ ዮሐንስ ከዘመኑ እሳት አወጣኝ


አጸደ ማርያም እህታችን በአዲስ አበባ አንድ ጭፈራ ቤት ውስጥ በዘፋኝነት ትሰራ ነበር የስራ ባልደረባዋ በኤችአይቪ በሽታ ተይዛ
ወደ ሸንኮራ ጸበል ትሄዳለች አጸደ ማርያም እህትዋን ለመጠየቅ ሸንኮራ ወርዳ ሳለ የዮሐንስን ታሪክ አንገቱም በዘፈን ምክንያት እንደተቆረጠ ትሰማለች ይልቁንም ጉዋደኛዋ ያቀረበችላት የተመርመሪ ጥያቄ ያስጨንቃታል አዲስ አበባ መጥታ ስትመረመር የHiv ቫይረስ በደምዋ ይገኛል ደጋግማ ከ3ወራት ቆይታ በሁላ ስትመረመር ለውጥ የለም በመጨረሻ ወደ ሸንኮራ ዮሐንስ ጸበል በመምጣት ንስሐ ገብታ ጸበልዋን ለ1 አመት ስትከታተል ቆይታ ድጋሚ ለምርመራ ስትመጣ ደምዋ ንጹህ እንደሆነ ይነገራታል በስእለትዋ መሰረት ስጋ ወደሙ ተቀብላ ከቀደመው ህይወትዋ እራስዋን አግላለች መጥምቁ የፈወሳት በሽታዋ ብዙ ነው ከዘፋኝነት 13 አመት ሲጋራና ጫት ስትወስድም ነበር ከዝሙት መንፈስ ከጥንቁልና አምልኮ ተላቃለች ያቁዋረጠችውን ትምህርት ቀጥላ ሸንኮራ ባወቀቻት እህት እርዳታ ድግሪዋን ይዛ ትዳር መስርታ ልጅም ወልዳ አዲስ አበባ ቃሊቲ አካባቢ ትኖራለች ያችም ቀድማ የታመመች እህታችን በሽታዋ ድና ሰሜን ወሎ አንድ ገዳም ውስጥ በምናኔ ትኖራለች ክብር ለዮሐንስ


ለክርስትና ስጦታ መተት በአሻንጉሊት ተቀብሮ የተሰጣት እናት - ድንቅ ተዓምር

Friday, June 17, 2016

የሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ጠበል ድንቅ ተአምር


እባክሆን ይህን ያላመነ የሚያምንበት ያመነ የሚፅናበትን ተአምር ለወዳጅ ዘመድዋ ያድርሱል...!!!
በስመአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
ደዌ ለፈተናም በ ሀጢያት ምክንያትም በብዙ ብዙ ምክንያት ይመጣል እግዚአብሄር አምላክ ፈቅዶ በቸርነቱ ይህን አደረገልኝ እንጂ እንደኔስ ሀጢያት ሌላም በተገባኝ ነበረ ለበሽታዬ ምክንያት ሀጢያት እንደሆነ ስለገባኝ እግዚአብሄርን እየተመላለስኩ በ እንባ ይቅርታ መጠየቅ ጀመርኩ።
ያልሄድኩበት ፀበል ያልያዝኩት ሱባኤ አልነበረም ነገር ግን (የ እግዚአብሔር ምህረት በጊዜዋ ነው ብሎ ነብዩ ቅዱስ ዳዊት እንደተናገረ ሁሉ በመጨረሻ የ ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤልን ታምር እና ዝና ሰምቼ ወደ ሽንቁሩ መጣሁ እንደቦታው ስርአት ንስሀ ገብቼ ፀበሉን ተጠምቄ መጠጣት ስጀምር ፀበሉን ከጠጣሁ ቡሀላ ባሉ 5 ደቂቃዎች ውስጥ ከሆዴ ውስጥ በስርአት የተከተፈ ስጋ
የሚመስል ነገር ይወጣ ነበር።



በሁኔታው ስደናገጥ በቦታው የቆዩ ፀበልተኞች አይዞህ ይሄ የሚወጣው መርዙ ነው በርታ ይሉኛል ቆይቶ አረንጉዋዴ ፈሳሽ ከሆዴ ወጣ ከዛቡሀላ ከበሽታዬ ሙሉ ለሙሉ ተፈውሻለሁ እኔን የረዳ እናንተንም ይርዳ አሜን።

ይህ የምትመለከቱ ምስል ወንድማችን ባለፈው የሽንቁሩን ደብረ መድሀኒያአለም ቅዱስ ሚካኤል ቦታ ጠይቆኝ በሙሉ እምነት በመሄድ ዕፀበሉ ቦታ በመሄድ ንሰሃ ገብቶ ካንተ በቀር ማንም የለኝ ብሎ በበሽታው ሲጨነቅ ሲጠበብ ይሄው እንደምታዩት ለዘመናት ሲያሰቃየው የነበረውን በሽታ በቅዱስ ሚካኤል ሀይል ፀበሉን በመጠጣት ይሄን ከሆዱ ውስጥ አውቶለታል።

እውነት እንደ ዛሬ የተደሰትኩባት ቀን የለችኝ የሰው ልጅ ስቃይ ሲፈታ ከማየት የበለጠ ምን ደስታ አለ።እንግዲህ እኛ የምናመልከው የምናምነው ፀበል ይሄ ነው ታምሩ ኦርቶዶክስ በማንኛውም በምታደርገው ነገር አትሳሳትም።
ወንድሜ ከዚህ በላይ ታምሩን ለመናገር ያብቃ ለእርሱ የደረሰ አምላክ ስንት በየቤታችን የሚሰቃዩ ያልጋ ቁራኛ ሆነው የሚሰቃዩ እህት ወንድሞች አሉን በምህረቱ አይን ይጎብኝልን።
ታምሩን ሼር በማድረግ ይተባበሩን ሁላችንም ለደጁ አብቅቶ ታምሩን ለመስከር ያብቃን ይችን ቀን በጉጉት እጠብቃት ነበር በእውነት ለእግዚአብሄር የሚሳነው ነገር ምን አለ።

የቅድስት አርሴማ ተአምር

እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይድረሰው የሰማእቷ የቅድስት አርሴማ ተአምር ለኔም አርጋልኛለች ላገኘሁት ሉ ተአምራቷን መሰክራለሁ ፍሬሕይወት ለማ እባላለሁ ምኖረው ለንደን ነው ቤተሰቦቼ ይርጋለም ነው ሚኖሩት በየጊዜ እነሱን ለማየት ስሄድ ፀበሏን እየተጠመኩ ነው ምመጣው ብዙ ነገሮችን አርጋልኛለች የአህኑ ተአምር ግን እናቴ ታመመችብን ስራ ፍቃድ ብጠይቅ አልተሰጠኝም ጠዋት ማታ በፀሎት አምላኬን እየለመንኩ እናቱን እመቤቴን አማልጅኝ እያልኩ ሰማእቷን እየለመንኩ ልክ ፋሲካ እሁድ ሊሆ ሁለት ቀን ሲቀረው ፍቃድ ተሰጠኝ እናቴም አዲስአባ ቤቴል ሆፒታል ለሁለትሳምንት ከትቆየች በሗላ ወደይርጋለም ተመልሳ ቤት ተኝታለች ቅኝ እጇና እግሯ እይቀሳቀስም ቤት ሆኗ ፀበሉን ህክምናውንም እየተከታተለች ነው እኔም ለ20 ቀን ፍቃድ ተሰጥቶኝ ልክ የፋሲካ እለት ማታ ተሳፍሬ ሰኞ ጠዋት አዲሳባ እንደገባህ ቀጥታ ወደይርጋለም ሄድኩ አርሴማ ፀበል እናቴን ይዠ የተወሰነ ቀን ተጠመቅን መሄጃዪ ደረሰና ልክ አውሮፕላን እንደተሳፈርኩ በቀኝ በኩል ጎኔ ላይ ጠዘጠዘኝ ስነካው ብጉር ይመስላል አበጥ ብሎአል በማግስቱ በጣም አበጠ ህመሙ ህይለኛ ስለነበር ፋርማሲ ቅርቤ ስለነበረ ሄጄ ሳሳያቸው ሆስፒታል ሂጂ አለኝ እኔም ስራ መግባት ስላለብኝ ወደቤቴ ተመልሼ ከይርጋለም አርሴማ ያመጣሁት ማር ነበረኝ ቅብት አድርጌው ፕላስተር ለጥፌበት ስራዪ ሄድኩ ህመሙ የት ደረሰ ሳልል ጠፋ ቀኑን ሙሉ ምንም ህመም ሳይሰማኝ ዋለ ስነካው ግን እብጠቱ እንዳለ ነው ህመሙ ስለተወኝ አርሴምዬን በልቤ እያወደስኩ ስራ ጨርሼ ማታ ቤቴ ገብቼ ፀሎቴን አድርሼ ፕላስተሩ አነሳሁትን ያበጠውን ነካ ሳረገው ነፍስ ያለው የሚንቀሳቀስ ነጭ ትል ተፈትልኮ ወጣ

የወጣበት ቁስል





አርሴምዪ በፀበሏ ቀጥቅጣ በማሯ ፈንቅላ በሽታዬን አወጣችልኝ ለእናቴ ሄጄ እኔ ተፈውሼ መጣሁ የቅድስት እርሴምዬ ገድሏ ታምራቷ ብዙ ነው የወጣውን ትል ቪድዮና ፎቶ ለብቻው ልኬአለሁ የሰማእቷ በረከት ይደርብን