Wednesday, February 1, 2017

"የጎጆዋ አርሴማ" - ድንቅ ነገር


☞ እንሆ በአዲስ አበባ በቦሌ ቡኒ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነ ድንቅ ነገር !!!!!! እንዲህ ሆነ በ ጥር 10 2009 ዓ ም የጥምቀት በዓለ ክብር ከተራውን ፈጽመን እንሆ በ 13 የቅዱስ እግዚአብሄር አብ , ቅድስት ኪዳነምህረት ,ተክልዬ, አና አርሴምዬን አጅበን ወደ መንበረ ክብሩ ደረስን ስርአተ ቤተክርስቲያኑን አከናውነን በእግዚአብሔር ፈቃድ እና በአባቶች ራዕይ ጽላቷ የመጣችው ቅድስት አርሴማ በድጋሚ ከገዳማውያን አባቶች የተነገሩትን መልእክት በአውደ ምህረት ተናገሩ እንዲህ አሉ "ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ጥንታዊ ለዛ ያለው ጎጆ ቤተክርስቲያን ሰርታችሁ በዛ አስገቡኝ " ብላለች ብለው ራዕዩን ተናገሩ ፡፡





ከዚህ በኀላ ማሳረጊያ ጸሎት ተደርጎ ታቦታቱ ወደመንበረ ክብራቸው ሲገቡ የቅድስት አርሴማን ያከበሩት አባት ተፍገመሙ ምን አልባት እረጅም መንገድ ስለተጓዙ ይሆናል በሚል ሌላ ካህን ተቀየሩ እንዲሁ እኒህ አባት ተንቀጠቀጡ በዚህ ጊዜ ምዕመናን በለቅሶ በዋይታ ተንበርክከው ማልቀስ ጀመሩ በዚህ ጊዜ ካህኑ ወደ ኀላ መልሳቸው እኛም ታቦቱን በማጀብ በእግዞታ ተከተልን በቅጽረ ቤተክርስቲያኑ ውስጥ በስተ ምስራቅ በኩል በጣም ቆንጆና ደልዳላ ቦታ ላይ ስትደርስ ካህኑን አቆመቻቸው በዚያች ቦታ ጸሎት ተደርጎ መሰረት ተጣለ ፡፡ ከዚህ በኀላ በነባሩ ቤተክርስቲያን በረንዳ ላይ ድንኳን ተጥሎ ታቦቷ በዛ አደረች እስካሁን በዛው ትገኛለች ፡ በአለቱ በተገኘው ገቢ እና በበጎ አድራጊዎች ታግዞ ጎጆ ቤትዋ በመሰራት ላይ ትገኛለች እንግዲህ በሰማዕቷ መልካም ፈቃድ በቀን 28/05/09 ዓም ጸሎተ ምህላ አድርሰን ቅዳሴ ቤቷን ለማክበር በዝግጅት ላይ እንገኛለን የሰማዕቷ ወዳጅ የሆነ ሁሉ በቤቷ እንድትገኙ ጥሪዋን ታስተላልፋለች ፡፡ታዋቂው እና ፈዋሹ የሰማዕቷ የማር ጸበል እንዳያመልጣችሁ ይህም ከመቅደሳ የተገኘ ነው ፡፡እንዲሁም ሀብተ ፈውስ ባላቸው አባት በመምህር አብርሃም የጸበል አገልግሎት ይሰጣል ፡፡ አድራሻ ከጎሮ ወደ ቱሉዲምቱ በሚወስደው መንገድ ላይ ሁለተኛውንና ትልቁን ድልድይ ሳይሻገሩ አስፋልቱ ዳር ላይ ይገኛል እግዚአብሔር አብ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ፡፡ለበለጠ መረጃ 0913511802 ወይም 0936451511ይደውሉ፡፡ በተጨማሪ ☞መንፈሳዊ ጉዞ የምታዘጋጁ መንፈሳዊ ማህበራት አና የቤተክርስቲያን ልጆች ወር በገባ በ 6 ወደዚህች የበረከት ደብር በሆነች ምዕመናንን እንድታስጎበኙልን እና ምዕመናንን የበረከቱ ተካፋይ ታደርጓቸው ዘንድ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች ቤተክርስቲያናም ማንኛውንም መንፈሳዊ ተግባራት ታከናውናለች ፡፡የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ በረከት ይደርብን አሜን፡፡
ጸሐፊ ዲ/ን ኤርምያስ ግርማ


የቅድስት አርሴማ አዲስ ፀበል


Wednesday, January 4, 2017

የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፀበል

ይህ የምታዩት የተአምረኛው የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፀበል ነው። ይህ ፀበል ብዙ ድውያንን ከተለያዩ ሀገራት ዝናውን ታሪኩን በመስማት እየመጡ ከበሽታቸው ፀበሉን በመጠመቅ፣በመጠጣት ብዛት ያላቸው ሰወች ከስቃያቸው ተፈውሰዋል።

ፀበሉ የሚገኝበት አካባቢ በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን  በቋራ ወረዳ በበርሚል ቀበሌ ይገኛል። ሽር በማድረግ በሰማዕቱ ስም ይተባበሩን የሰማዕቱ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።

Tuesday, December 27, 2016

በሻሌ ንቡ ቅ/ሚካኤል - Video

ዋካ ቅድስ ጊዮርጊስ ገዳም

በ15ክ/ዘመን የተመሰረተው አብነ ጵጥሮስ የቀደሱበት የባረኩት በደመና የመጣ ታቦት ቀድሞ ከ15ክ/ዘመን በፊት/ መንዝ ዋካየአብይ ገብረመንፈስቅድስ ገዳም/ ሲሆን 15ክ/ዘመን ላይ ዋካ ቅድስ ጊዮርጊስ ገዳም ተብላል፡፡በጣም ስለት ሰሚ ነው፡ጣልያን በወረረን ግዜ ቦንብ ጥለው ቤተክርስቲያኑን ሊያቃጥሉ ቢወረወሩ ቤተክርስቲያኑ አልቃጠል ሲላቸው ሰውን ፡ካህኑን እየገደሉ ቤተክርስቲያኑ አልቃጠል ሲላቸው የታቦቱን መጎናጸፍፊያ ለብሰው ሲሂድ ከዋካ ከቦታ አልፈው ሂደው ጉርሙኝ ቆላውየ4ሰዓት መንገድ ልብሱን ለብሶ ለብሰው ጣሊያኖቹ ሲሂድየአካባቢው ሰው /አቶ ተገኝ/የሚባሉ ሰው ይህ በምታዩት ጋሻ በመከት ጣሊያኖቹን በመግደልና ገደል በመክተት የጊዮርጊስ መጎናጸፊያ አስመልሰው መጎናጸፊያው(ልብሱ ):በዋካ ጊዮርጊስ ይገኝል፡፡

 




አቶ ተገኝ ጀግና ተብለው የደጃዝማች መሀረግ ሲሰጣቸው ቁረብ ሰጋወ ደሙ ተቀበሉ ሲላቸው በመንዝ አካበቢ ጀግና ሲሞት ቀረርቶ ;ይሸለላል;ይፎከራል ይህ ሳይደረግ ጀግና አይቀበርም፡፡እና አቶ ተገኝ ቁረብ ሲባሉ እኔን ጊዮርጊሰ ጀግና አርጎ ጠላቱን ገድይ ልብሱን አስመልሻለሁ እና ቁርባኑን ሰጋ ደሙን ጊዮርጊሰ ያቀዋል፡ሳይሸለልልኝ ሳይፋከርልኝ ብለው በ110አመታቸው ሞቱ፡፡ የሚገርሙአባት ናቸው በጀግና አሟሟትየተፋከረ፡እየተሸለለ በጀግና አቀባበር በ110አመታቸው አርፈዋል፡፡ስለት ሰሚው ዋካ ጊዮርጊስ የዱሮው ቤተክርስቲያንሳይፈርስ ሌላ ቤተክርስቲያን በመሰራት ላይ ሲሆን መርዳት ለእግዚአብሔር ማበደር ሲሆን ስለት ሰሚውን ዋካን በምንችለው አቅም እንርዳ የቤተክርስቲያኗ መሰረቱ በመሠራት በመውጣት ላይ ነው፡፡በረከቱ በያለንበት ከጊዮርጊሰ ይደርብን፡፡አሜን
ቦታው-+መንዝ ዘብር ገብርኤል ከአ/አ 260ኪሜ ሲሆን ከዘብር የ4ሰዓት መንገድ ሲሆን 4wdመኪና ቦታው ድረስ ይገባል ሜዳ ቀላል መንገድ ነው፡፡