Wednesday, February 8, 2017


ዛሬ የአባታችን የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ የድህነትን ስጦታ ስለተቋደሰች እህታችን ላይ የተፈፀመውን ድንቅ ታምር ላውጋችሁ፣ ከስር ፎቶው ላይ የምትመለከቷት እህታችን በጡት( thoracic cancer) ካንሰር ደዌ ተይዛ ለዘመናት በመፍቴህ አልባ እንቅስቃሴ የአለም ሆስፒታሎችን በር በማንኳኳት ስትዳክር ቆይታለች ።ከሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ ባሉ ስመጥር የህክምና ዶክቶሮች ዘንድ በመቅረብ ለችግሯ መፍቴህ የሚሆናትን መንገድ ስታፈላልግ ብትደክምም አንዳቸውም ከስቃይዋ ሊያሳርፏት አልቻሉም ። ባላት ሙሉ አቅም መነካት እና መደረስ አለበት የተባሉትን ሁሉ ብትነካም የበሽታው ህመም እና ስቃይን እንዳያድግ ከማድረግ አላገዳቸውም ።ኑሮዋ በስቃይ ላይ ስቃይ በህመም ላይ ህመም የሆነላት ይህች እህታችን ግን በአንድ ወቅት ከአንድ ወዳጇ ታምራዊ ፀበል ከወደ አርባምንጭ እንደፈለቀ እና ብዙዎች በመጠመቅ እንደተፈወሱ በመንገር አይኗን ገልጣ ሞትን ከመጠባበቅ እድሏን እንድትሞክር ይነግሯታል።እሷም ይህን ጥሪ ችላ ለማላት ባትፈልገውም ልሞክረው በሚል ሃሳብ ወደ ስፍራው (ዝጊቲ አርባምንጭ) ትመጣላች ።በተፀበለችው ቀናት ሁሉ በሽታው ከሚያደርስባት ስቃይ እና ህመም ማገገም እና ማረፍ ጀመረች ።ከጥቂት ሱባኤ በሃላ የልዑል እግዚአብሄር የማዳን ፍቃድ በአባታችን አቡዬ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፀበል ላይ በመስፈፍ እህታችንን ሙሉ በሙሉ ከበሽታዋ እንድትድን እና እንድትፈወስ አደረጋት። ይህንንም በአለም የህክምና ምርመራ በማረጋገጥ የአቡዬን ድንቅ ስራን ለአለም በመስበክ ምስክርነቷን በተለያዩ ጉባኤዎች ላይ ሰጥታለች ።ይህን የአባታችንን ውለታ የማይረሳ ልብ ያላት እህታችን ከሞት ፅልመት በፈውሳቸው ጎትተው ላወጧት አባታችን ውለታ በማሰብ የደብሩን ህንፃ ቤተክርስትያኑን ብቻዋን በአዲስ መልክ ለመስራት በማቀድ እና በማሰብ የ20 ሚሊዬን ብር የቤተክርስትያን ዲዛን በማሰራት እና ግንባታውን በመጀመር በስራ ላይ ትገኛለች ።
 

Tuesday, February 7, 2017

የቁልቋል በር ማርያም ቤተክርስቲያን


እነሆ ከተወለደ ጀምሮ 15 ዓመት ሙሉ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ ይኖር የነበረ ወንድማችን በእናታችን ጸበል እነሆ ከደዌው ተፈውሷል እንዲሁም ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ታምራት በእመቤታችን ተደርጓል የእናታችን የቁልቋል በር ማርያም ወዳጆች እንደሚታወቀው የእናታችን ቤት ለመጨረስ የተለያዩ ገቢ ማሰባሰቢያ እያደረግን እንገኛለን የተለያዩ ጉዞዎች ፣ ትኬቶችን በመሸጥ ላይ ነን፤ ይህን መልካም ስራ ለመስራት እናቴ ቤትሽ በፍሶ እኔ እንዴት በተደላደለ ቤት እኖናራለን ብለን ከሀገርም በውጪም የምንኖር እጆቻንችን ዘርግተናል በመዘርጋት ላይም ነን ታዲያ ቤተክርስቲያኑ በአሁኑ ሰዓት ስራው የጀመረ ሲሆን ነገር ግን አሁን ሙሉ ለሙሉ ስራውን ለመስራት እነዚ ነገሮች ይጎድላሉ እንደ አሽዋ ሲሚንቶ ፌሮ፣ እና ህንፃ ቤተክርስቲያኗን ለመጨረስ የሚያስፈልጉ ነገሮች በጣም ይጎድላሉ ከዚህ በተጓዳኝ ደግሞ ይህን ስራ የሚሰሩ ሳተኞች የሚከፈላቸው ብር ሙሉ ለሙሉ ባለመገኘቱ በተወሰነ ሰራተኛ ነው አሁን ስራው የተጀመረው በሀገርም በውጪም የምንገኝ እህት ወንድሞቼ አንዳችን ባንችል እንኳ ሁለት ሦስት ከዛ በላይ በጋራ በመሆን ያለንን በማዋጣት የእናታችን የቁልቋል በር ማርያምን ቤት እንስራ ከዛ ባሻገር ደግሞ ብዙ ምህመን እንደዚ ያለ ቤተክርስቲያን የለም እናንተ በስሟ ልትነግዱ ነው የሚል ሃሳብ ነበር ነገር ግን እውነታን ቦታው ድረስ ሄዳችሁ ያያችሁ እህት ወንድሞቼ ምስክር ናችሁ ከእናታችን ጎን በመሆን እጅ ለእጅ ተያይዘን የጀመርነው ከግብ እናድርስ፤ እማማ ወላዲተ አምላክ ያሰብነውን መልካም ነገሮች ሁሉ በምልጃዋ ታስፈጽምልን የባንክ አካውንት ቁጥሩ kuli kual ber d/m/k mariam b/k commercial bank of Ethiopia Acc/no 1000167540949 ለበለጠ መረጃ ደግሞ በህነዚህ ስልክ ይደውሉ 09 38 59 49 03/0911 76 28 72 / 0913 67 78 91 ደውለው ስለ ቤተክርስቲያኗ ያለችበት ሁኔታ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ ፡፡
‹‹ በእውነቱ ይህ ቤት ፈርሶ እናንተ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ልትኖሩ ጊዜው ነውን? ›› ሀጌ 1፡4

Monday, February 6, 2017

ፃድቃኔ ማሪያም ድንቅ ታምር

የእናታችን የፃድቃኔ ማሪያም ድንቅ ታምር ትላንት ለሊት እለተ ቅዳሜ ከለሊቱ 8:--- ገደማ እህታችን ጉሮሮዬን ተናነቀኝ ብላ መፀዳጃ ቤት ሄደች አብረዋት ያሉትም ሰዎች ተከትለዋት ይወጣሉ ታዲያ ያልታሰበ ክስተት ተፈጠረ አነቀኝ ባጠጠኝ ያለችው ይህ የምታዩት ቁወቱ አንድ ስንዝር የሚሆን እባብ ከሆዷ ወጣላት የድንግል ማሪያም ስም ይመስገን ክብር ለስሟ ይሁን ይህ ድንቅ ታምር የተደረገው በትላንትናው ለሊት እለተ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ከለሉቱ 8:19 /26/5/2009 ነው እኔም ድንግል ማሪያም የዘረያእቆብ እመቤት ስውሯ ፅላት የአይን ምስክር ስላደረገችን ድንቅ ታምሯን እንድመሰክር ስላደረገችኝ ምስጋና ይድረሳት ለተጨነቅነው ሁሉ ትድረስልን አሜን