Sunday, March 26, 2017

ዘብር ቅዱስ ገብርኤል


በሰሜን ሸዋ በመንዝ በላሎ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ የመላዕኩ የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አለ ይህ ቤተክርስቲያን ዘብር ቅዱስ ገብርኤል ሲባል መስቀልና መቋሚያ ተቆሞ የሚፀለይበት አስደናቂ የፈውስ ቦታ ነው። በዚህ ቤተክርስቲያን ከ50 ዓመት በላይ ደብሩን ያስተዳደሩ የበቁ አባት የ103 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ኤኔታ አክሊሉ ይገኛሉ ። በዘመናችን እግዚአብሔር ካስቀመጠልን የፀሎት አባት የብቃት ደረጃ ላይ ከደረሱ አባቶች መካከል አንዱ ናቸው ። ኤኔታ አክሊሉ ኮርያ ከወንድማቸው ጋር ዘመተዋል በዚያም በጦር ሜዳ ከወንድማቸው ጋር ስዕለት ተሳሉ፤ስለቱም በሰላም ለሀገራችን ቃበቃህን ዕድሜ ልካችንን በድንግልና በክህነት እናገለግላለን ብለው ለዘብር ገብርኤል ተሳሉ እግዚአብሔርም ሰለታቸውን ሰምቶ እንቅፋት ሳይመታቸው እሾክ ሳይወጋቸው በሰላም ወደ ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጰያ ተመለሱ ። ኤኔታ አክሊሉም በስዕለታቸው መሰረት በክህነት ዘብር ማገልገል ጀመሩ ወንድማቸው ግን ስዕለቱን ወደ ጎን በመተው ሚስት አገባ ኤኔታም ወንድሜ ነው ዘር ይተካ ሳይሉ ወንድማቸውን ጠርተው ይህ በአንተ ዘንድ አይደረግ ስዕለትንም አትርሳ ብለው ወቀሱት ንስሀ ገብቶ አብሮ በክህነት እንዲያገለግል መከሩት እርሱ ግን አሻፈረኝ ብሎ እምቢ አላቸው ወድያውም ሚስቱ ሞተች ፤ እርሱም የጥፋት ሰው ነውና ድጋሚ ሌላ ሚስት አገባ ኤኔታም እጅግ አዝነው ተቆጡት ምክራቸውንም አልሰማ ሲል በመጨረሻ ወንድማቸው ራሱ ሞተ አባታችንም አልቅሰው ቀበሩት። ኤኔታ አክሊሉ በዘብር አገልግሎታቸውን ቀጠሉ በእጃቸው የተማሩ ከ55ሺ በላይ ሊቃውንት አፈሩ ፣ኤኔታ የማያውቃቸው የቤተክርስቲያን ሊቅ የለም በመላው ኢትዮጰያ ያስተማሯቸው ሊቃውት እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደምድር አሸዋ የበዙ ናቸው ፣አሁን ከ400 በላይ የቆሎ ተማሪ በስራቸው ይገኛል በዚህ ተጋድሎቸው የተመለከተው ጠቅላይ ቤተክህነት የጵጵስና ማዕረግ ሊሰጣቸው ጥሪ አቀረበላቸው እርሳቸው ግን በኮሪያ የገቡትን ቃል አስበው አልፈልግም ዕድሜ ልኬን ዘብር ገብርኤልን ላገለግል ስዕለት አለብኝ ብለው የክህነት ሹመቱን መለሱት፤ እውነተኛ አገልጋይ የቤተክርስቲያን ባለውለታ ድንቅ አባት ናቸውና ።

አንዴ እንዲ ሆነ ኤኔታ አክሊሉ ተማሪ በሚያስተምሩበት ጊዜ ተማሪያቸው እየሞተ ተቸገሩ ሀገሩ ላይ ታላቅ መቅፀፍት ሆነ በዚህም የተነሳ አባታችን ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደው የፃድቁ አባታችንን የአቡነ አብተማርያምን ታቦት ተሸክመው ወደ ዘብር ገብርኤል ይዘው መጡ ኤኔታ አክሊሉ የአብተ ማርያም ቃል ኪዳን መቅሰፍት አራቂነት ጠንቅቀው ያቃሉና ታቦቱን ከመንበሩ ቢያስቀምጡት መቅሰፍት ከአገሩ እርቆላቸዋል አንድም ተማሪ ከዚያ በኃላ ሞቶባቸው አያውቅም። ኤኔታ የሚሞቱበትን ቀን የሚያቁ ሲሆን ወደእርሳቸው የሚመጣውን ሰው ማንነት የማወቅ ፀጋ አላቸው ማህራችን ላይ ዘብር ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ከአዲስ አበባ እንደሚመጣና ቤተክርስቲያኑን በዓለም ደረጃ የሚያስተዋውቅ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን ትንቢታቸውም ተፈፅሞ በክብር ተቀብለሁን እኛም የማንጠቅም ባሪያ ስንሆን ገዳሙን በዓለም ደረጃ አስተዋውቀናል ኤኔታ አክሊሉ የፀሎት አባት ሲሆኑ ምግባቸውም አጥቢት እና አጃ ብቻ ነው እርሷን ለቁመተ ስጋ ነው የሚመገቡት፣ አንድ ጊዜ እርሳቸው ቤት ገብቼ አልጋቸው ላይ እንድቀመጥ አደረጉኝ ስለቤተክርስቲያኑ አንዳንድ ነገር ለመነጋገር በዚያ ጊዜ ብዙ ክርስቲያኖች በእጃቸው መስቀል ለመሳለም ቤታቸውን አጨናንቆት ነበር ቤቱ ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ ከአራት ሰው በላይ ማስተናገድ አይችልም ሰው ውስጥ ተጨናንቆ ገብቶ ቀሪው ውጪ ጋር ተራ እየጠበቀ ሰልፍ ይዟል በመሀል የወረዳው ፀሐፊ መርጌታ ጥላውን የሕዝቡን መጨናነቅ የቤቱን ጥበት ተመልክተው ከበር ሊመለሱ ሲሉ ኤኔታ አክሊሉ ሰው ሳይጋርዳቸው ግድግዳ ሳይሸፍናቸው ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ና አንተ የወረዳው አትመለስ ግባ ብለው መጥራታቸውን የወረዳው ፀሐፊ ደንግጠው የገቡበትን ቀን አረሳውም አርባራ መዳኒዓለም ቤተክርስቲያን ከሽቦ አጥር በኃላ ምንም ነገር አይነሳም አንዲት እህታች የሾላ ፍሬ አንስታ ቦርሳዋ ውስጥ ብትከት መኪናችን ሶስት ጊዜ ጎማ ፈነዳብን በዚህ የተነሳ በጣም ተጨንቀን ሳለ እህታችን የሾላ ፍሬ ከቦርሳዋ አውጥታ እኔ ከተከለከለ ቦታ አንስቼ ነው ብላሰጠችን እኛም ፀሎት አድርገን ምሕረቱን እንዲያደርግልን ተማፅነን ጎማችንን አስተካክለን ተነስተን ዘብር ገባን እኔም ወደ እኚ የበቁ አባት ጋር ለመባረክ አቀናው ወደያው ሲያዩኝ እየሳቁ አጠገባቸው እንድቀመጥ አድርገው የሆነውን ነገር ቦታው ላይ እንደተገኙ አድርገው የደረሰብንን መከራ ራሳቸው መናገር ጀመሩ እኔ እጅግ ደነገጥኩኝ እሳቸው አይዞ መላዕኩ ከእናንተ ጋር ነው ብለው አረጋጉኝ ይህንን ቀን መቼም ቢሆን አረሳውም በእውነት በእሳቸው እጅ መባረክ መታደል ነው ክብራቸው ቢረቅብን ከግሪክ ሀገር የክህነት ልብስ አስመጥተን ብሰጣቸው ለእናንተ ስል ለአንድ ቀን እለብሰዋለው ብለው አንድ ቀን ስለፍቅር ለብሰው በነጋታው የኬሻ ቆባቸውን አደረጉ። የዚህችን ዓለም ጣዕም ንቀዋልና አይናቸው ከፀሎትና ከእንባ ብዛት የተነሳ ደክሟል የፃድቅ ክብሩ የሚገለጠው ሲሞት ነውና ያልተነገረ ብዙ አለና ወደ ሀገራቸው ከመሄዳቸው በፊት በረከታቸውን እናግኝ መልክቴ ነው በቀጣይም ስለ በረሃው አባት አባ ላዕቀ ስለ ኢትዮጰያ የተናገሩትን እና ያጫወቱኝ ታሪክ ይዤላችሁ እቀርባለው አስከዛው ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን አሜን

Wednesday, February 8, 2017


ዛሬ የአባታችን የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ የድህነትን ስጦታ ስለተቋደሰች እህታችን ላይ የተፈፀመውን ድንቅ ታምር ላውጋችሁ፣ ከስር ፎቶው ላይ የምትመለከቷት እህታችን በጡት( thoracic cancer) ካንሰር ደዌ ተይዛ ለዘመናት በመፍቴህ አልባ እንቅስቃሴ የአለም ሆስፒታሎችን በር በማንኳኳት ስትዳክር ቆይታለች ።ከሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ ባሉ ስመጥር የህክምና ዶክቶሮች ዘንድ በመቅረብ ለችግሯ መፍቴህ የሚሆናትን መንገድ ስታፈላልግ ብትደክምም አንዳቸውም ከስቃይዋ ሊያሳርፏት አልቻሉም ። ባላት ሙሉ አቅም መነካት እና መደረስ አለበት የተባሉትን ሁሉ ብትነካም የበሽታው ህመም እና ስቃይን እንዳያድግ ከማድረግ አላገዳቸውም ።ኑሮዋ በስቃይ ላይ ስቃይ በህመም ላይ ህመም የሆነላት ይህች እህታችን ግን በአንድ ወቅት ከአንድ ወዳጇ ታምራዊ ፀበል ከወደ አርባምንጭ እንደፈለቀ እና ብዙዎች በመጠመቅ እንደተፈወሱ በመንገር አይኗን ገልጣ ሞትን ከመጠባበቅ እድሏን እንድትሞክር ይነግሯታል።እሷም ይህን ጥሪ ችላ ለማላት ባትፈልገውም ልሞክረው በሚል ሃሳብ ወደ ስፍራው (ዝጊቲ አርባምንጭ) ትመጣላች ።በተፀበለችው ቀናት ሁሉ በሽታው ከሚያደርስባት ስቃይ እና ህመም ማገገም እና ማረፍ ጀመረች ።ከጥቂት ሱባኤ በሃላ የልዑል እግዚአብሄር የማዳን ፍቃድ በአባታችን አቡዬ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፀበል ላይ በመስፈፍ እህታችንን ሙሉ በሙሉ ከበሽታዋ እንድትድን እና እንድትፈወስ አደረጋት። ይህንንም በአለም የህክምና ምርመራ በማረጋገጥ የአቡዬን ድንቅ ስራን ለአለም በመስበክ ምስክርነቷን በተለያዩ ጉባኤዎች ላይ ሰጥታለች ።ይህን የአባታችንን ውለታ የማይረሳ ልብ ያላት እህታችን ከሞት ፅልመት በፈውሳቸው ጎትተው ላወጧት አባታችን ውለታ በማሰብ የደብሩን ህንፃ ቤተክርስትያኑን ብቻዋን በአዲስ መልክ ለመስራት በማቀድ እና በማሰብ የ20 ሚሊዬን ብር የቤተክርስትያን ዲዛን በማሰራት እና ግንባታውን በመጀመር በስራ ላይ ትገኛለች ።
 

Tuesday, February 7, 2017

የቁልቋል በር ማርያም ቤተክርስቲያን


እነሆ ከተወለደ ጀምሮ 15 ዓመት ሙሉ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ ይኖር የነበረ ወንድማችን በእናታችን ጸበል እነሆ ከደዌው ተፈውሷል እንዲሁም ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ታምራት በእመቤታችን ተደርጓል የእናታችን የቁልቋል በር ማርያም ወዳጆች እንደሚታወቀው የእናታችን ቤት ለመጨረስ የተለያዩ ገቢ ማሰባሰቢያ እያደረግን እንገኛለን የተለያዩ ጉዞዎች ፣ ትኬቶችን በመሸጥ ላይ ነን፤ ይህን መልካም ስራ ለመስራት እናቴ ቤትሽ በፍሶ እኔ እንዴት በተደላደለ ቤት እኖናራለን ብለን ከሀገርም በውጪም የምንኖር እጆቻንችን ዘርግተናል በመዘርጋት ላይም ነን ታዲያ ቤተክርስቲያኑ በአሁኑ ሰዓት ስራው የጀመረ ሲሆን ነገር ግን አሁን ሙሉ ለሙሉ ስራውን ለመስራት እነዚ ነገሮች ይጎድላሉ እንደ አሽዋ ሲሚንቶ ፌሮ፣ እና ህንፃ ቤተክርስቲያኗን ለመጨረስ የሚያስፈልጉ ነገሮች በጣም ይጎድላሉ ከዚህ በተጓዳኝ ደግሞ ይህን ስራ የሚሰሩ ሳተኞች የሚከፈላቸው ብር ሙሉ ለሙሉ ባለመገኘቱ በተወሰነ ሰራተኛ ነው አሁን ስራው የተጀመረው በሀገርም በውጪም የምንገኝ እህት ወንድሞቼ አንዳችን ባንችል እንኳ ሁለት ሦስት ከዛ በላይ በጋራ በመሆን ያለንን በማዋጣት የእናታችን የቁልቋል በር ማርያምን ቤት እንስራ ከዛ ባሻገር ደግሞ ብዙ ምህመን እንደዚ ያለ ቤተክርስቲያን የለም እናንተ በስሟ ልትነግዱ ነው የሚል ሃሳብ ነበር ነገር ግን እውነታን ቦታው ድረስ ሄዳችሁ ያያችሁ እህት ወንድሞቼ ምስክር ናችሁ ከእናታችን ጎን በመሆን እጅ ለእጅ ተያይዘን የጀመርነው ከግብ እናድርስ፤ እማማ ወላዲተ አምላክ ያሰብነውን መልካም ነገሮች ሁሉ በምልጃዋ ታስፈጽምልን የባንክ አካውንት ቁጥሩ kuli kual ber d/m/k mariam b/k commercial bank of Ethiopia Acc/no 1000167540949 ለበለጠ መረጃ ደግሞ በህነዚህ ስልክ ይደውሉ 09 38 59 49 03/0911 76 28 72 / 0913 67 78 91 ደውለው ስለ ቤተክርስቲያኗ ያለችበት ሁኔታ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ ፡፡
‹‹ በእውነቱ ይህ ቤት ፈርሶ እናንተ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ልትኖሩ ጊዜው ነውን? ›› ሀጌ 1፡4