Friday, June 17, 2016

የሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ጠበል ድንቅ ተአምር


እባክሆን ይህን ያላመነ የሚያምንበት ያመነ የሚፅናበትን ተአምር ለወዳጅ ዘመድዋ ያድርሱል...!!!
በስመአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
ደዌ ለፈተናም በ ሀጢያት ምክንያትም በብዙ ብዙ ምክንያት ይመጣል እግዚአብሄር አምላክ ፈቅዶ በቸርነቱ ይህን አደረገልኝ እንጂ እንደኔስ ሀጢያት ሌላም በተገባኝ ነበረ ለበሽታዬ ምክንያት ሀጢያት እንደሆነ ስለገባኝ እግዚአብሄርን እየተመላለስኩ በ እንባ ይቅርታ መጠየቅ ጀመርኩ።
ያልሄድኩበት ፀበል ያልያዝኩት ሱባኤ አልነበረም ነገር ግን (የ እግዚአብሔር ምህረት በጊዜዋ ነው ብሎ ነብዩ ቅዱስ ዳዊት እንደተናገረ ሁሉ በመጨረሻ የ ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤልን ታምር እና ዝና ሰምቼ ወደ ሽንቁሩ መጣሁ እንደቦታው ስርአት ንስሀ ገብቼ ፀበሉን ተጠምቄ መጠጣት ስጀምር ፀበሉን ከጠጣሁ ቡሀላ ባሉ 5 ደቂቃዎች ውስጥ ከሆዴ ውስጥ በስርአት የተከተፈ ስጋ
የሚመስል ነገር ይወጣ ነበር።



በሁኔታው ስደናገጥ በቦታው የቆዩ ፀበልተኞች አይዞህ ይሄ የሚወጣው መርዙ ነው በርታ ይሉኛል ቆይቶ አረንጉዋዴ ፈሳሽ ከሆዴ ወጣ ከዛቡሀላ ከበሽታዬ ሙሉ ለሙሉ ተፈውሻለሁ እኔን የረዳ እናንተንም ይርዳ አሜን።

ይህ የምትመለከቱ ምስል ወንድማችን ባለፈው የሽንቁሩን ደብረ መድሀኒያአለም ቅዱስ ሚካኤል ቦታ ጠይቆኝ በሙሉ እምነት በመሄድ ዕፀበሉ ቦታ በመሄድ ንሰሃ ገብቶ ካንተ በቀር ማንም የለኝ ብሎ በበሽታው ሲጨነቅ ሲጠበብ ይሄው እንደምታዩት ለዘመናት ሲያሰቃየው የነበረውን በሽታ በቅዱስ ሚካኤል ሀይል ፀበሉን በመጠጣት ይሄን ከሆዱ ውስጥ አውቶለታል።

እውነት እንደ ዛሬ የተደሰትኩባት ቀን የለችኝ የሰው ልጅ ስቃይ ሲፈታ ከማየት የበለጠ ምን ደስታ አለ።እንግዲህ እኛ የምናመልከው የምናምነው ፀበል ይሄ ነው ታምሩ ኦርቶዶክስ በማንኛውም በምታደርገው ነገር አትሳሳትም።
ወንድሜ ከዚህ በላይ ታምሩን ለመናገር ያብቃ ለእርሱ የደረሰ አምላክ ስንት በየቤታችን የሚሰቃዩ ያልጋ ቁራኛ ሆነው የሚሰቃዩ እህት ወንድሞች አሉን በምህረቱ አይን ይጎብኝልን።
ታምሩን ሼር በማድረግ ይተባበሩን ሁላችንም ለደጁ አብቅቶ ታምሩን ለመስከር ያብቃን ይችን ቀን በጉጉት እጠብቃት ነበር በእውነት ለእግዚአብሄር የሚሳነው ነገር ምን አለ።

የቅድስት አርሴማ ተአምር

እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይድረሰው የሰማእቷ የቅድስት አርሴማ ተአምር ለኔም አርጋልኛለች ላገኘሁት ሉ ተአምራቷን መሰክራለሁ ፍሬሕይወት ለማ እባላለሁ ምኖረው ለንደን ነው ቤተሰቦቼ ይርጋለም ነው ሚኖሩት በየጊዜ እነሱን ለማየት ስሄድ ፀበሏን እየተጠመኩ ነው ምመጣው ብዙ ነገሮችን አርጋልኛለች የአህኑ ተአምር ግን እናቴ ታመመችብን ስራ ፍቃድ ብጠይቅ አልተሰጠኝም ጠዋት ማታ በፀሎት አምላኬን እየለመንኩ እናቱን እመቤቴን አማልጅኝ እያልኩ ሰማእቷን እየለመንኩ ልክ ፋሲካ እሁድ ሊሆ ሁለት ቀን ሲቀረው ፍቃድ ተሰጠኝ እናቴም አዲስአባ ቤቴል ሆፒታል ለሁለትሳምንት ከትቆየች በሗላ ወደይርጋለም ተመልሳ ቤት ተኝታለች ቅኝ እጇና እግሯ እይቀሳቀስም ቤት ሆኗ ፀበሉን ህክምናውንም እየተከታተለች ነው እኔም ለ20 ቀን ፍቃድ ተሰጥቶኝ ልክ የፋሲካ እለት ማታ ተሳፍሬ ሰኞ ጠዋት አዲሳባ እንደገባህ ቀጥታ ወደይርጋለም ሄድኩ አርሴማ ፀበል እናቴን ይዠ የተወሰነ ቀን ተጠመቅን መሄጃዪ ደረሰና ልክ አውሮፕላን እንደተሳፈርኩ በቀኝ በኩል ጎኔ ላይ ጠዘጠዘኝ ስነካው ብጉር ይመስላል አበጥ ብሎአል በማግስቱ በጣም አበጠ ህመሙ ህይለኛ ስለነበር ፋርማሲ ቅርቤ ስለነበረ ሄጄ ሳሳያቸው ሆስፒታል ሂጂ አለኝ እኔም ስራ መግባት ስላለብኝ ወደቤቴ ተመልሼ ከይርጋለም አርሴማ ያመጣሁት ማር ነበረኝ ቅብት አድርጌው ፕላስተር ለጥፌበት ስራዪ ሄድኩ ህመሙ የት ደረሰ ሳልል ጠፋ ቀኑን ሙሉ ምንም ህመም ሳይሰማኝ ዋለ ስነካው ግን እብጠቱ እንዳለ ነው ህመሙ ስለተወኝ አርሴምዬን በልቤ እያወደስኩ ስራ ጨርሼ ማታ ቤቴ ገብቼ ፀሎቴን አድርሼ ፕላስተሩ አነሳሁትን ያበጠውን ነካ ሳረገው ነፍስ ያለው የሚንቀሳቀስ ነጭ ትል ተፈትልኮ ወጣ

የወጣበት ቁስል





አርሴምዪ በፀበሏ ቀጥቅጣ በማሯ ፈንቅላ በሽታዬን አወጣችልኝ ለእናቴ ሄጄ እኔ ተፈውሼ መጣሁ የቅድስት እርሴምዬ ገድሏ ታምራቷ ብዙ ነው የወጣውን ትል ቪድዮና ፎቶ ለብቻው ልኬአለሁ የሰማእቷ በረከት ይደርብን

Thursday, June 16, 2016

የቅድስት አርሴማ ተአምር

የ ሰማዕቷን የቅድስት አርሴማ ተአምር ልንገራችወ ፎቶዉ ላይ የ ሚታይዋት ታላቅ እህቴ ፋቅረ ማርያም ትባላለች በዝህ አመት በ ቡዳ መንፈስ ስትሰቃይ ነበር ነገር ግን በ አለም ላይ የተወከለችዉ ሰማዕቷ እኛም ቤት መጣች በ ሚያዝያ ወር በ ቀን 9ከ ምሽቱ 4 ሰዓት አከባብ እህቴ ታመመች ቤት ዉስጥ ከ ታናሽ ወንድሜ አብሮን ልያድር ከመጣዉ ከ አጎቴ ልጂ እና ከ እኔ በቀር ሌላ ማንም አልነበረም ግራ ገባን ጎሬበት ተጠራ ሰዉ ተሰበሰበ ( ጠናዳም ግዛዋ...) አጠኗት መንፈሷ ወድያዉ መለፋለፋ ጀመረች የመጀመርያ ቃሏ ግን "አርሴማ ምታቃጥለኝ አንሶነዉ እናንቴ ምታቃጥሉኝ"የምል ነበር ካህን ተጠራ ተፀበለች የት እንዳየቻት በ ጥርሷ እንደገባች እና ማንነቷን ተናገረች የን ዕለት በማግስቱ ከ ረፋዱ10 ሰዓት ላይ እለካታለዉ ብላ ተገዝታ ወጣች በዝህ ሁኔታ እስከ ማክሴኞ ቀጠልን ዕረቡ ዕለት ልክ ከ እረፋዱ 10 ሰዓት ላይ ጀመራት ያለን አማራች ቦንጋ ሄዳ እንድትፀበል ማድረግ ነበር ለ እናታችን ተደዉል ተነገራት እና ለመጨረሻ ጊዜ ቤት ተፀብላ እናታችን ይዛት ወደ ቦንጋ ሄዱ ከዛም
አባታችንም እዛዉ ቦንጋ ክዳነምህረት ፀበል እየተፀበለ ስለነበር ከሱጋር እዛዉ እንድትፀበል ታስቦ በማግስቱ ወደዛዉ ሄዱ ከተፀበለች በዋላ ግን ክዳነምህረት ወደ ቅድስት አርሴማ ላከቻት ምክኛቱም ሁሉም ሰማዕታት የወከሏት እሷን ስለሆነ ነዉ ከዛንቀን ጀምሮ እዛዉ ሰማዕቷ ገዳም ገብታ መፀበል ጀመረች በየቀኑ ስንደዉል የ ምንሰማዉን ነገር ማመን ከበደን ለካ በ እህቴ ላይ አድራ ቤታችንን ልታፀዳልን ነበር በቅናት መንፈስ ተነሳስተዉ እህቴ እንድታብድ በተሰቦቻችን እንዳይስማሙ በ እያንዳዳችን ላይ ታስቦ የተሰራ ተንኮል ነበር ድመት ገለዉ በ 7 ምስማር ወጥረዉ በ ቤታችን ጓሮ እንደተቀበረ እና እሷ እንደምታወጣልን ሰማዕቷ በ እህቴ ተመስላ ነገረችን በዝህ ሁኔታ መፀበሏን ቀጠለች ከ ጥርሷ1ጠጠር ወጣ ከዛም እዛዉ እያለች ሰሞነ ህማማት ደረሰ ሰማዕቷ መንፈሷን ገዝታ በቀጠሮ ማለትም እሰከ ሰኔ ስድስት እንዳትመለስ አዘዘቻት ነገር ግን "ህማማቱን እስከ ስቅለት ልጄ ከነጋር ደጄ ትስገድ " አለች ሌላም ትዛዝ " ልጄ መነፅር ትጠቀም በዛ መነፅር ላይም ሀይሌ ያርፍበታል ሰኔ 6 ምዛን ዉሰዷት ቀርዉ 6 ጠጠር እዛ ይወጣል " የምል ነበር እኛም በቃሏ መሠረት ይደረግ የተባለዉን ሁሉ አደረግን ፀሎተ ሐሙስ ከ ሰአት በዋላ ወደበት ተመለሰች በ አሉን በሰላም አሳለፍን የ ቀጠሮዉን ቀን መጠባበቅ ጀመርን በ መሀል ግን ሰማዕቷ ብዙ ታምሯን በ እኛቤት አደረገች ቁልፍ ጠፍቶብን ስንጨነቅ ለ እህቴ በ ህልሟ መታ ቁልፉ የት እንደ ወደቀ ነገረቻት ቁልፉን ከተባለዉ ቦታ አገኝነዉ ብቻ ብዙ ታምሯን እያየን ግኔቦት 8 ደረሰ አሁንም ቤት ዉስጥ ማንም አልነበረም እንደልማ ዳችን ተሰብስበን ተለቪዥን እያየን የ አጎቴ ልጂ እግሩን ተንተርሳ የ ሰማዕቷን ፎቶ እያየች ማልቀስ ጀመረች ምን እደሆነች ስንጠይቃት ፍቅርተ እንዳል ሆነች እና መንፈሷ እተገረፈች እደሆነ ገረችን ደነገጥን ካህን ልንጠራ ስናስብ " ማንንም እንዳጠሩ ፀበልም ካህንም አታምጡ ሴማዕቷ በ ዘንባባዋ እየገረፈችኝ ነዉ" አለች ተረጋጋን ልክ 3 ሰዐት ስሆን ፀሎት አደረገች በ መጨረሻም ሰማዕቷ ተመስላመታ እንዳንፈራ ና ሁሌም ከቤታችን እንደሆነች ነገረችን በሚግስቲም ቀጠለ 12 ስሆን ምካኤል ገረፋት በ 13 ሰማዕቷ በ14 አቡነ 16 ክድዬ እያለ እስከ ቀን 4 ቆየ ልክ ከ ለልቱ 9 ሰዓት ላይ ተቀብሮ የ ነበረው የጠላት ስራ በ ሰማዕቷ ትዛዝ መሠረት እንደምታዩት ከነ ምስማሩ ወጣ በቀን 5ወደ ምዛን ሄዱ ስሄዱ ፀበሉ መዘጋቱ ያዉቁ ነበር ግን በዛ ምትክ ወደ እመቤታች በቴክርስትያን እንድሄዱ ታዘዙ ከዛም ሰማዕቷ ተመስላ ስለ ፀበሏ መዘጋት አለቀሰች ምዕመኑም አብሯት አለቀሰ እንሆ ዛሬ የመጨረሻዋ ቀን 7 በማያልቀዉ ፈዉሷ የ ቀረት 6 ጠጠሮች ወተዉ እርኩስ መንፈስ ተቃጥሎ ኤህቴ ተፈወሰች ቤታችን ሰላም ገባ ክብር ለ መድአንአለም የኛን ሰላም የ መለሰችልን ሳሰለች የፈወሰችን ቅድስት አርሴማ በ ሁላችዉም ቤት ትግባ ወስበአት ለ እግዝአብሔር!!! 


አንዲት እህት ከሆዷ ውስጥ ጥቁር ወፍ ወጣላት


Monday, June 13, 2016

ተነግሮ የማያልቀው የሸንኮራ ዮሐንስ ድንቅ ተአምር

ስለ ሸንኮራ ቅዱስ ዮሐንስ ጸበል ምን ያህል ያዉቃሉ? የሸንኮራ ዮሐንስ ፀበል በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ንዑስ ከተማ በሆነችዉ በባልጪ ከተማ አጠገብ በርካታ ተገልጋዮች ከተለያዩ ቦታዎች በመምጣት ፈውስ የሚያገኙበት ፀበል ነው፡፡ ፀበሉ በፈዋሽነቱ በይፋ መታወቅ የጀመረዉ:- አባ ካሳ የሚባሉ መናኝ ባህታዊ በሸንኮራ ቅ/ዮሐንስ ቤ/ክ መቃብር ቤት ዉስጥ ዘግተዉ ይኖሩ ነበር፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በህልማቸዉ ከቤተ ክርስቲያኑ በስተምስራቅ ከወንዙ ዉስጥ ጸበል ፈልቋልና ወርደህ አይተህ ለህዝቡ ንገር እዉራን የሚያበራ፣ ለምፅ የሚያነፃ፣ ጎባጣ የሚያቀና ጸበል ፈልቋል በልና ንገር ብሎ በህልማቸዉ ነገራቸዉ፡፡

ሲነጋ ጠዋት በተነገራቸዉ መሰረት ወደ ወንዝ ወርደዉ ጸበሉን ሲፈልጉ አላገኝ አሉት፡፡ አባ ካሳ የዕድሜ ባለፀጋ ሲሆኑ ሲፈልጉ ዉለዉ በድካም ወደ ቤታቸዉ ተመለሱ፡፡ እንደገና ሌሊት በህልማቸዉ "ጠዋት ተነሣና ወደ ጸበሉ ዉረድ ጸበሉ ከጫካ ዉስጥ ፈልቆ ታገኘዋለህ ከፊ ከፊትህ የምትመራህ ርግብ ታሳይሃለች"አላቸዉ፡፡ በታዘዙት መሰረት ከጠዋት ተነስተዉ ወደ ወንዝ ሲሄዱ ርግብ ከፊት ከፊት እየመራቻቸዉ ከወንዙ ዉስጥ ሲደርሱ ጸበሉ ከፈለቀበት ገደል ላይ ክንፏን ዘርግታ አረፈች፡፡ከዚያም አባ ካሣም እግዚአብሔርን አመስግነዉ የፈለቀዉን ጸበል ጠጥተዉ እግራቸዉን ክፉኛ በሽታ ያማቸዉ ስለነበር ጸበሉን ሲያስነኩት ከያዛቸዉ በሽታ ወዲያዉኑ ተፈዉሰዋል፡፡ ከዚህ በኋላ አባ ካሳ የፈለቀዉን ጸበል ለህዝቡ ነግረዉ ሚያዝያ 30 ቀን ታቦተ ህጉ ወደ ጸበሉ ወርዶ በደማቅ ሁኔታ ተክብሯል፡፡ ይህንን ራዕይ ያዩት ሚያዝያ 15ቀን 1654 ዓ.ም ገደማ ሲሆን 354 ዓመት ያስቆተረ ጸበል ነዉ ተብለዉ ይገመታል፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ በረከት ከሁላቸን ጋር ይሁን አሜን ።


ቤቱ ከአፋፍ ላይ ጸበሉ ከጅረት የድውያን ዳባሽ መጥምቀ መለኮት የስሙ ትርጉዋሜ ፍስሐ ወሐሴት በልደቱ የፈታ የአባቱን አንደበት እማሆይ ሂሩተ ገብርኤል ይባላሉ ተወልደው ያደጉት እዚሁ አዲስ አበባ ነው ትምህርታቸውን ጨርሰው ዮንቨርስቲም የሁለተኛ አመት ተማሪ ሳሉ በደረሳቸው መለኮታዊ ጥሪ በምናኔ ወደ ገዳም በመግባት ለ5 አመታት አገልግለው ደጅ ጠንተው በገዳሙ ማህበር ፈቃድ ምንኩስናቸውን ተቀብለው አገልግሎታቸውን በሰፊው በመስጠት ላይ ሳሉ ድንገት ባላሰቡት ሁኔታ በጡት ካንሰር በሽታ ይለከፋሉ አዲስ አበባ ለህክምና በመምጣት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታልና በሌሎችም የግል ህክምና መስጫ ምርመራ ቢያደርጉም የታመመው አካል በአስቸኩዋይ ካልተቆረጠ ካንሰሩ ይሰራጫል ይባላሉ ህመሙ ከባድና ጽኑ ነበር በተለይ የጨረር ህክምና ተብለው የባሰ ተሰቃዮ እማሆይ ምርር ብለው ያለቅሳሉ ገና በማለዳ ነፍሴን ለገነት ስጋዬን ለአራዊት ብዬ መንኜ እንዴት ገላዬ ተገልጦ ክብሬ ይቃለላል ይህስ እንዲሆን አምላኬ ለምን ፈቀድክ ብለው ያዝናሉ የታመመ አካላቸውን ለማስቆረጥ ቀጠሮ ይይዛሉ እማሆይ እንደተናገሩት ፒያሳ አካባቢ ነዳይ መስለው ተሰውረው የሚኖሩ ባህታዊ ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ስወጣ "ሸንኮራ ዮሐንስ ሂጂ አንቺ ፈላሲ "ይሉኛል የምን እብድ ነው ብዬ አለፍኩት ክንክን አደረገኝና ተመልሼ ባይ ጠፉብኝ ልቤ ተነሳሳ ስቃዮ ደግሞ ረፍት ነሳኝ ደምና መግል ከታመመው አካሌ ይወርዳል እንደምንም ሸንኮራ መሪ ሰው ይዜ ገባው እምነቱን ጸበሉን ስቀባው ከረምኩኝ ይፈስ የነበረው የደም ጎርፍ ጠፋ ህመሜም ቀነሰ እንቅልፍም በደንብ እተኛ ጀመር ሰላሜ ተመለሰ የቀጠሮውም ቀን አለፈ ፍጹም ጤነኛ ሆንኩኝ የአይነ ከርሙ ባህታዊ ነብየ ልኡል ሰማእቱ መጥምቁ የጌታዬ የአምላኬ ወዳጅ በአድያመ ዮርዳኖስ በሸንኮራ ምድር በስሙ በፈለቀው ጸበል ጡቴን ከመቆረጥ አዳነኝ ዳግም ተመርምሬ ፍጹም ጤነኛ ነሽ ተብያለው ወደምወደው ገዳሜ በደስታ ተመልሻለው ብለዋል እናታችንይህን ያደረገ የዮሐንስ አምላክ ክብር ይግባው ይግባው ከኛም የማይበጀንን ነገር ቆርጦ ይጣልልን አሜን

Thursday, June 9, 2016

ተአምራት በሸንኮራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ዮሐንስ - 2

ሸንኮራው ቅዱስ ዮሐንስ ጸበል እጹብ ድንቅ ተአምራት የተደረገላቸው ግብጻዊትዋ እናቴ
ወ/ሮ ናዲያ ሁለተኛዋ እናቴ ኢትዮጵያ አቡነ ዘበሰማያት ብለህ እራይ የምታይባት ቅድስት ምድር ናት የሚሉ ከ40 አመት በላይ የሚኖሩት እዚሁ አዲስ አበባ ነው እኔ የማውቃቸው አፍ ከፈታው ከህጻንነት እድሜዬ ጀምሮ ነው በአፍሪካ ህብረት ከወላጅ እናቴ ጋር ረጅም አመት ሰርተዋል ዛሬም በመስራት ላይ ይገኛሉ እኝህ እናት ግብጽ ደማንሁር የምትኖር አብሮ አደግ እህታቸው በማህጸንዋ ውስጥ ምን እንደሆነ ያልታወቀ ነገር ተገኝቶ ለ5አመታት ስትሰቃይ ልጅ ነው አንዳንዴምን እጢ ነው ስትባል በመጨረሻ ወደ አውስትራሊያ ሄዳ ኦፕራሲዮን ብትደረግም ምንም ማህጸንዋ ውስጥ አልተገኘም በቅድመ ምርመራ ዶክተሮቹ ምንነቱ ያልተለየ ነገር አለ መውጣት አለበት ብለው ነው የከፈትዋት በመጨረሻም ወደ ግብጽ ተስፋ ቆርጣ ተመልሳ ሳለ ወ/ሮ ናዲያ የቀድሞውን ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስን ከቅድስት ስላሴ ቀዳሽ እያሉ ከ60ቹ ጀምሮ ይተዋወቃሉና ቡራኬ ለመቀበል ሄደው ችግራቸውንም አውርተው ሲጨርሱ ፓትርያርኩ የዮሐንስን ጸበል ላኩላት ብለዋቸው ኖሮ እኔን ይጠይቁኛል ግዜ ስላልነበረ ከወ/ሮ ሳባ ሐብቶም ቤት ጸበሉን ተቀብዬ ሰጠዋቸው ታማሚዋ ጸበሉ ግብጽ ደርሶ በቀመሰችበት ደቂቃ ያ ያሰቃያት ለሐኪሞች ከአእምሮ በላይ የነበረው ነገር እንደ ልጅ 5አመት ይዛው የተንከራተተችው ማህጸዋ ተከፍቶ የተሰወረው 2ኪሎ እጢ ወጣ እላይዋ ያደረው እርኩስ መንፈስም ታሪኩን ለፈለፈ ዛሬ እህታችን ትዳር ይዛ የ1 ልጅ እናት ሆና ካናዳ ትኖራለች መጥምቁንና ያከበረውን አምላኩን ሸንኮራ ድረስ መጥታ ደጁን ስማ ስጦታዋን አስገብታለች ለናዲያ ያደረገውን አስደናቂ ተአምር ወደፊት እናወራዋለን የመጥምቁ አምላክ ክብር ምስጋና ይግባው አሜን

 
የመጥምቁ ዮሐንስን ድንቅ ተአምር በህጻን አንደበቱ የመሰከረው ህጻን ፍቅረ ዮሐንስ ናዝሬት ከተማ ተወልዶ ያደገው ይህ ልጅ ባጋጠመው የአጥንት ካንሰር ምክንያት በህክምና መፍትሔ ሲጠፋ ወላጅ እናቱ ወደሸንኮራ ዮሐንስ ይዛው ትመጣለች ክብር ምስጋና ለዮሐንስ አምላክ ካርድ አውጣ ኤክስሬ ተነሳ መድሐኒት ግዛ የለ የመጥምቁ ጸበል የታመመ እግሩ ሲመታው ያሰቃየው የነበረው በነቀርሳ(ካንስር)የተበላው አጥንቱ ስጋውን ዘንጥሎ ወጥቶ ጤናውን አግኝቶዋል ቆሜ እራመዳለው ኩዋስ እጫወታለው ትምህርቴንም ጀምሬያለው ብሎ በህጻን በሚጣፍጥ አንደበቱ የወጣለትን አጥንት ይዞ ከወላጅ እናቱ ጋራ ምስክርነቱን በአወደ ምህረቱ ሰጥቶዋል የዮሐንስ አምላክ ክብር ይግባው
 
 

Wednesday, June 8, 2016

ተአምራት በሸንኮራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ዮሐንስ

ሸንኮራ ዮሐንስ ከአየር ላይ ሲታይ የገደሉ መሐል ጸበሉ ያለበት ነው ያች 8የማይበልጡ የጭራሮ ጎጆ የነበረች መንደር ዛሬ የፈውስ መዲና ሆና ዘምናለች 20 ሰው የምትይዘው ቤተክርስቲያን ዛሬ ታላቅ ህንጻ ተገንብቶባታል የነፍስም የስጋም ሆስፒታል ሆናለች አጥቢያዋ



















አቶ በላይ ደምሴ የተባሉ አባት ከባሌ ክፍለሐገር
ሁለቱም ጆሮዋቸው መስማት አይችልም ነበር አባታችን የመጥምቁን የፈውስ ዝና ቢሰሙም ወደ ሸንኮራ ለመምጣት አቅም ያጣሉ አንድ በአካባቢያቸው የሚያውቁትን ወጣት ጸበል አምጣልኝ ብለው 500 ብር ለትራንስፓርት ሰጥተው ይሸኙታል ልጁ እዛው ሲያውደለድል ተደብቆ ከርሞ ከወንዝ ውሐ ቀድቶ ይሰጣቸዋል አቶ በላይም የተሰጣቸውን ውሐ በእምነት ሲጠጡት ጆሮዋው ተከፈተ ድንቅ ነው በዚያው ቅጽበት የወጣቱ ሁለቱም ጆሮ መስማት አቆመ ይህ ወጣት ጥፋቱን ያውቃልና በንስሐ አባቱ አማካኝነት ወደ ሸንኮራ መጥቶ ለነፍስም ለስጋው ንስሐ ገብቶ ቀኖና ተቀብሎ ይፍታህ በሚባልበት 14ኛ ቀኑ ላይ ጆሮው ተከፍቶ በአንደበቱ የሰራውን ጥፋትና የተደረገውን ድንቅ ተአምር መስክሮዋል ይህን ያደረገ የመጥምቁ አምላክ ክብር ይግባው አሜን

ወ/ሮ ሐዱሽ ገ/ዋህድ ይባላሉ ከገጠሪቱ ኢትዮጵያ 16 አመት የታወረ አይናቸውን ለመታከም ነው ወደ መሐል ሐገር የመጡት አዲስ አበባ ኦፕራሲዮን ቢያደርጉም ተስፋ የለውም እንዲሁ ይኑሩ ይባላሉ ቤተክርስቲያን ለመሳለም ሄደው የሸንኮራን ታሪክ ሰዎች ሲያወሩ ሰምተው አድራሻ ጠይቀው መሪ አስታማሚ ይዘው ጉዞ ወደመጥምቁ ቤት ተከራይተው ጸበሉን መጠመቅ ይጀምራሉ 8ኛ ቀን ላይ ወደ ጸበሉ መውረጃ ገደሉን መንገድ ከመሪያቸው ጋር ይጀምራሉ መሪያቸው ድንገት ወደ ጫካ ለሽንት ትገባለች እሳቸውም ከምቆም ብለው መንገድ ይጀመራሉ በምርኩዛቸው ድንገት ያላሰቡት ነገር ተከሰተ የለበሱትን ነጠላ ቆንጥር ያዘብኝ መንገዱም ቁልቁለት ላይ ነበርና የያዝኩትምርኩዜም ከእጄ አምልጦ ተንሸራቶ ርቆ ወደቀ በቆምኩበት ደነገጥኩኝ ተማረርኩኝ ሞቴን ተመኘው አዘንኩኝ ምነው ዮሐንስ ብዬ ነጣላዬን ከእሾኩ ለማላቀቅ ፊቴን ሳዞር የጠፋው አይኔ ቦግ አለ ማመን አልቻልኩም እየተመራው የወረድኩትን ገደል ህዝቡን እየመራው በእልልታ በሆታ ወጣውት ብለው መስክረዋል እኝህ እናት በወቅቱ ከደስታቸው ብዛት ግቢው ውስጥ ይንከባለሉ ነበር ይህን ያደረገ የመጥምቁ አምላክ ክብር ይግባው አሜን

ሸንኮራን የሚያውቅ ሁሉ ምንትዬ ዮሐንስ ምን እንዳደረገላት የማያውቅ የለም በስምዕ ጽድቅ ጋዜጣ በዜና ቤተክርስቲያን በደብሩ መጽሔት ታሪክዋ በሰፊው ተመዝግቦዋል ስቃየ ብዙዋ እህታችን አዲስ አበባ ጎፋ መካነ ህያዋን ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ተማሪ የሆነችው ምንትዬ ታሪክዋ ሰፊ ስቃይዋ ዘግናኝ ነበር አትተኛም አትቀመጥም አትራመድም የዮሐንስ ያለህ ያዮ ይመስክሩ በልብ በኩላሊት በደም ብዛት እረ የበሽታዋ አይነት ብዛቱ መለኮትን ባጠመቀበት እጁ ዮሐንስ የታሰረችበትን ደዌ ሁሉ ፈታት ከሰውነትዋ የሚወደው ደምና መግል ተወግዶ ሞትሽን ጠብቂ በሳጥር ተቁዋጥረሽ ልትጣይ ነው የተባለችው ምንትዬ ይህው ዛሬ በእግርዋ ቆማ የመጥምቁን ደጅ ጥዬ አልሄድም ብላ እንግዳ ተቀባሪ ጸበልተኛ አጉራሽ ሆናለች እስቲ ሰኔ 30 ኑና የመጥምቁን ታሪክ ጽናት ትእግስትዋን ተማሩ ህወታችሁን አለምልሙ የምስጋናን ህይወት እንድትጀምሩ የቀጠሮ ሰው ይበለን አሜን

እናታችን ከባሌ ነው የመጡት ያወኩዋቸው ጫካ ጸበል ለመጠጣት ወጥቼ ነው ወይዘሮ ደሜ ይባልሉ ከንፈራቸው ላይ በወጣ ቁስል ምክንያት መላ ፊታቸው ይቆስልና ሽታም ያመጣል በሐኪም ብዙ አቅሜን ጨረስኩኝ ጠንቁዋይም ገንዘቤን ጨረሰብኝ የሸንኮራ ዮሐንስን ድንቅ ተአምር ሰማው ተነስቼ መጣው ጠረኔ ከሰው ስለማያቀላቅልና የቆሰለው ፊቴንም ደፍሮ የሚያይ ስለሌለ ጫካ እውላለው ጸበልም ሰው ሳይኖር እወርዳለው አሉኝ በእውነት ዘግናኝ አጋጣሚ ነበር 8አመታት የተሰቃዮበት ያ የቆሰለው ፊት እንደ ሰንኮፍ ውልቅ ብሎኝ በቁስል የነፈረው ከንፈራቸው ደርቆ ጠረን መአዛቸው ተለውጦ በዛ ህመምተኛ በነበረ አንደበታቸው እልልታን ብቻ ሳይሆን ንስሐ ገብተው ስጋ ወደሙም ተቀብለው ብጽአታቸውን በእጃቸው የፈተሉትን ግምጃ ስእሉን ሲጋርዱ አይቻለው እኝህ ምስኪን እናት ሸንኮራ ለጥቂት ሳምንታት ተቀምጠው ነው ፈውስን ያገኙ ዛሬ በየአመቱ ሰኔ 30 ከደጁ አይቀሩም የኛንም ክፉ መአዛ አምላከ ዮሐንስ ያጣፍጥልን አሜን

በሸንኮራው ዮሐንስ ጸበል ከጡት ካንሰር የዳነችው
የአጥቢያችን ብስራተ ገብርኤል ነዋሪ ሳባ ሐብቶም እህቴም እናቴም የሆነችው ሳባ ወደ ሸንኮራ ከመሄድዋ በፊት በጽኑ ስቃይ በካንሰር በሽታ ትሰቃይ ነበር በወቅቱ የነበራት ስቃይ ከቃላት በላይ ነበር አቅሙም ነበራትና ያልደረስችበት ህክምና የለም በተለይ የግል ሐኪምዋ ፕሮፌሰር ታዬ እንዲሁም በጥቁር አንበሳ ብሩክ ክሊኒክ ህክምናዋን ብትከታተልም ካንሰሩ ወደ መላ አካላትዋ ተሰራጭቶ ሞትዋን ስትጠብቅ ወደ ምንጃር ሸንኮራ ጸበል በመምጣት ሸንኮራ በወቅቱ ጥቂት ጎጆዎች ብቻ የነበረባት ትንሽ መንደር ነበረች ከሞላ ቤትዋ ወጥታ የጭራሮ ጎጆ ተከራይታ ጸበልዋን ጀመረች ጽናትዋ ትእግስትዋ ይደንቅ ነበር ቅዱስ ዮሐንስ ደጅ ጥናትዋን ስቃይዋን ተመልክቶ ከአምላኩ አማልዶ በህልም በራእይ ሳይሆን በገሐድ በመገለጥ እንደዳበሳትና 4አመት በዘግናኝ ሁኔታ ያበጠው ሰውነዋ ፈንድቶ ብዙ ደምና መግል ከሰውነትዋ ወጥቶ ፈውስን ተቀዳጅታለች አዲስ አበባ መጥታ ተመርምራ ሙሉ ጤናማ መሆንዋን አረጋግጣለች ይህው 17 አመት ሆናት የቀብር ማስፈጸሚያ በርበሬ የተፈጨላት ጤፍ የተሸመተላት የንፍሮ እህል የተለቀመላት መግነዝ ጨርቅዋን ከቤት ብሞትም ብላ ይዛ የወጣችው ሳባ መጥምቁ ዳብሶ ፈውስን አግኝታ ለእንባ አድርቅ የታሰበው እህል ለዝክር ሆነንዋል ሳባቆማ ትሆዳለች በእለተ ፋሲካ በየአመቱ ቤትዋን በአወደ አመት ዘግታ የአክፋይዋን በመጥምቁ ደጅ ላሉ ካህናት ጸበልተኞች ነዳያን ይዛ ጾም ታስፈታለች መጥምቀ መለኮት ነብየ ልኡል እኛ ከማናውቀው የታሰርንበት ክፉ ነገር ይፍታን አሜን

ነቢየ ልኡል ሐዋርያው ሰማእቱ መጥምቀ መለኮት ድንግላዊው ባህታዊው ካህኑ ከሴት ከተወለደ የሚተካከለው የሌለ ቅዱስ ዮሐንስ በልደቱ የአባቱን የታሰረ አንደበት የፈታ የስሙ ትርጉዋሜ የሁሉ ደስታ የሆነ ዛሬም በደዌ የታሰረውን በጸበሉ የሚፈታ ቃልኪዳኑ ዛሬም ያልተሻረ በመጥምቁ ደጃፍ ያገናኘን በፎቶ የምናየው ወንድም በሸንኮራ ጸበል የተፈወሰ ነው
የቀጠሮ ሰው ይበለን አሜን



ፀበሉ ፈዋሽ ዘብር ቅድስ ገብርኤል


 ምንጭ

Wednesday, June 1, 2016

መጻሕፍቶቻችን ስለ ቅ/ያሬድ ምን ይላሉ?

መጻሕፍቶቻችን ስለ ቅ/ያሬድ ምን ይላሉ?
ኢትዮጵያ ተለይታ ከምትታወቅባቸው እና ቤተ ክርስቲያናችንም ለሀገሪቱ ካበረከተቻቸው ብዙ ነገሮች አንዱ ያሬዳዊ ዜማ ነው። የዚህ ልዩ ሀብት ጀማሪ የሆነው ግንቦት ፲፩ ቀን ክብረ በዓል የሚደረግለት ቅ/ያሬድ ኢትዮጵያዊ ቅዱስ፣ ካህን፣ ሊቅ፣ መዓርዒረ ዜማ፣ ደራሲ (የዜማ እና የመጻሕፍት)፣ የመጻሕፍት መምህር
፣ ባለቅኔ (በድጓው ውስጥ ያሉ ቅኔዎችን መዘርዘር ይቻላል)፣ ሰማዕት (ያሬድ ማኅሌተ እግዚአብሔርን ሲያደርስ ንጉሡ ገብረ መስቀል ተመስጦ እግሩን ስለወጋው ደሙን አፍስሷልና) ወዘተ. የሚሉት ስለ ክብሩ የሚቀጸሉ መጠሪያዎቹ ናቸው።
ቅ/ያሬድ ሲነሳ ሁሌም ቀድሞ በአእምሯችን የሚመጣው በኢትዮጵያ ውስጥ ዜማን የጀመረ መሆኑና ግእዝ፣ ዕዝል፣ አራራይ ብሎ በሦስት መደብ መክፈሉ ነው። ዜማው ከዛሬ 1500 ዓመታት በፊት ተጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የማይሰለችና ልዩ መንፈሳዊ ሐሴትን የሚያጎናጽፍ ሰለሆነ በእርሱ ዜማ የመመሠገነው ልዑል አምላክ፣ አመሥጋኞቹ ካህናትንም ምድራውያን መላእክት የሚያሰኝ ነው። ቅ/ያሬድ ከመነሳቱ በፊት በኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ውርድ ንባብ ያለ ትሑት ቃል እንጂ ምልክት ያለው በዜማ የሚደርስ ማሕሌት አልነበረም። ስለዚህ ዜማ ሲነሳ ያሬድ መጠራቱ አይቀሬ መሆኑን ሁሉም የሚስማማበት ነው። ሌላው የቅ/ያሬድ አስተዋጽኦ እና በብዙዎች ዘንድ የማይታወቀው ሥራው በኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመሪያው ደራሲ እሱ መሆኑ ነው። እስካሁን በተደረገው ጥናት የኢትዮጵያ ጽሑፎች እስከ ያሬድ መነሳት ድረስ ትርጉሞች (በተለይ ከግሪክ ቋንቋ) ነበሩ። ብሔራዊ ድርሰትን (ሀገር በቀል) በኢትዮጵያ የጀመረ ያሬድ ነው። ለዛሬ የማቀርበው ጽሑፍ ቅ/ያሬድ የደረሳቸውን መጻሕፍትና የኋላ ሊቃውንት ስለ እርሱ ክብር የጻፉትን በመጠኑ ይመለከታል። (ስለ ሕይወት ታሪኩ በብዙ ቦታ ስለተጻፈ ብዙም አልዳስሰውም።)
በሀገራችን ከሚገኙት መጻሕፍት ስለ ቅዱስ ያሬድ የሚናገሩ መጻሕፍት በርካታ ናቸው፤ በጥቅሉ በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች እንመድባቸዋለን። የመጀመሪያዎቹ ራሱ ቅ/ያሬድ የጻፋቸው የዜማ መጻሕፍት ሲሆኑ፤ ሁለተኛዎቹ ስለ ቅ/ያሬድ ክብር የተደረሱ የምሥጋና ድርሰቶች፤ ሦስተኞቹ የቅ/ያሬድን ታሪክ የያዙ ሌሎች መጻሕፍት ናቸው። ዝርዝራቸውን ቀጥሎ እንመልከት።

ሀ) እርሱ የጻፋቸው፤
ከላይ በመግቢያው እንዳልነው ቅ/ያሬድ የምሥጋና እና የአምልኮ መግለጫ የሆኑ የዜማ መጻሕፍትን በግዕዝ ቋንቋ ጽፏል። እነዚህም በስፋት የሚታወቁት አምስቱ የዜማ መጻሕፍቱና በታሪክና በትውፊት የተቀበልናቸው ሌሎች መጻሕፍት ናቸው። እነርሱም፥
1) ድጓ - ከቅ/ያሬድ ድርሰቶች ውስጥ ትልቁ የዜማ መጽሐፍ ድጓ ሲሆን በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች የተከፈለና በቤ/ክ ከዓመት እስከ ዓመት የሚደርስ ምስጋና ነው። በተለያዩ ዘመናት የተገለበጡ የድጓ ቅጂዎች በኢትዮጵያ የሚገኙ ሲሆን አንዳንድ ጠቃሚ እና ትክ የማይገኝላቸው ቅጂዎች ከባሕር ማዶ ተሻግረው ይገኛሉ (ለምሳሌ ቫቲካን [Vat. Aeth. 28]፣ በርሊን [Orient. 1000])። በሀገራችን ከሚገኙት ዕድሜ-ጠገብ ድጓዎች መካከል በላሊበላ ቤተ-ጊዮርጊስ የሚገኘው (12ኛ መ/ክ/ዘ)፣ በጣና ቂርቆስ የሚገኘው (13 መ/ክ/ዘ)፣ በደብረ ብርሃን የሚገኘው (16ኛመ/ክ/ዘ)፣ የሐይቁ ድጓ (17መ/ክ/ዘ)) ይጠቀሳሉ። “መጽሔተ፡ ጥበብ” በመባል የሚታወቀው የቅ/ቤተልሔም (ደ/ጎንደር) ድጓ ለምስክር አብነት ነው።
2) ጾመ ድጓ - በዐቢይ ጾም የሚደርስ ምሥጋና ነው። ጾመ ድጓ በዋናው ድጓ (ከአስተምህሮ ድጓ) ክፍል ተካቶ ይገኛል። ክፍሉ በዓቢይ ጾም ውስጥ ባሉት ሰንበታት ልክ ሲሆን ተራቸውም፤ ዘወረደ፣ ቅድስት፣ ምኵራብ፣ መጻጕዕ፣ ደብረ፡ ዘይት፣ ገብር፡ ሔር፣ ኒቆዲሞስ እና ሆሣዕና የሚል ነው።
3) ምዕራፍ - ይህ የዜማ መጽሐፍ ከመዝሙረ ዳዊት የተውጣጡት ምሥጋናዎችን በመስመር በመስመር እየከፈለ የሚደርስ የስብሐተ እግዚአብሔር መጽሐፍ ነው።
4) ዝማሬ - ማሕሌት ሲቆም የሚደርስ ሆኖ በጊዜ ቅዳሴ ከድርገት በኋላ የሚቀርብ ምሥጋና ነው። ዝማሬ አምስት ክፍሎች ያሉት ሲሆን እነዚህም ኅብስት፣ ጽዋ፣ መንፈስ፣ አኮቴት እና ምስጢር የሚባሉት ናቸው። የዚህ የዝማሬና የመዋሥዕት ማስመስከሪያ ቤተ ጉባኤው ቅ/ያሬድ ባስተማረበት ቦታ በዙርአባ አረጋዊ ቤ/ክ (ደቡብ ጎንደር) ነው።
5) መዋሥዕት - ካህናት በተዋሥኦ (በመቀባበል) የሚያዜሙት ሲሆን በተለይ በጸሎተ ፍትሐት ጊዜ እና በቀዳም ሥዑር ዕለት የሚደርስ ምሥጋና ነው።
6) አንቀጸ ብርሃን - ቅ/ያሬድ ይህን የእመቤታችንን ምሥጋና ያደረሰው በአክሱም ጽዮን ቤ/ክ ውስጥ ከታቦተ ጽዮን ፊት ቆሞ ሲሆን ድርሳኑ ይህንን እንዲህ ይገልጻል “ወሶቤሃ፡ ቦአ፡ ያሬድ፡ ውስተ፡ ታቦተ፡ ሕጉ፡ ለእግዚአብሔር፡ እንተ፡ ይእቲ፡ ገበዘ፡ አክሱም፡ ወአንበረ፡ ፪እደዊሁ፡ ውስተ፡ ርእሰ፡ ታቦት፡ ወከልሐ፡ በልዑል፡ ቃል፡ እንዘ፡ ይብል፡ ቅድስት፡ ወብፅዕት፡ ስብሕት፡ ወቡርክት፡ ክብርት፡ ወልዕልት፡ አንቀጸ፡ ብርሃን፡ መዓርገ፡ ሕይወት፡ እስከ፡ ተፍጻሜቱ። ..... ።” ገድሉ እና ተአምሩ (ሦስተኛው) እመቤታችንን እየለመነ አንቀጸ ብርሃንን በዕዝል ዜማ ሲያደርስ ቁመቱ አንድ ክንድ ያህል (“ተለዓለ፡ መጠነ፡ እመት፡”) ከምድር ወደ ላይ ከፍ ይል እንደነበር መዝግበውታል። ለዚህ ጸሎት ምላሽ እመቤታችንም ተገልጻ በቃል ታናግረው ነበር።
7) የሦስት ቅዱሳንን ገድል ጽፏል፤ በትውፊት እንደሚታወቀው ቅ/ያሬድ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል የሦስቱን ቅዱሳን ገድል ጽፏል። እነዚህም ገድለ አረጋዊ፣ ገድለ ጽሕማ እና ገድለ ይምአታ ናቸው።
8) ቅዳሴ - የታተሙት ቅዳሴያት 14 በብዛት ይታወቃሉ፤ ነገር ግን ያልታተሙ ሌሎች ስድስት ቅዳሴያትም አሉ፤ የቅ/ያሬድ ቅዳሴም ካልታተሙት አንዱ ነው።

ለ) ስለ ቅ/ያሬድ ክብር የተጻፉ
ከኢትዮጵያ ቅዱሳን ሊቃውንት ግንባር ቀደም የሆነው ማሕሌታይ ያሬድ በዜማ ደራሲነቱ በዓለም ደረጃ የሚታወቅ ሲሆን ካበረከተው ዘመን ተሻጋሪ ሥራ አኳያ ስናየው ግን ስለ እርሱ ክብር የተጻፈው አነስተኛ ነው። ድርሳን እና ገድል ተጽፎለታል ሆኖም በጣም አጫጭር ናቸው። እስካሁን ከተገኙት ውስጥ ዕድሜ ጠገብ የሆነው በሐይቅ ገዳም (ደቡብ ወሎ) ከሚገኘው “ገድለ ቅዱሳን” ውስጥ የሚገኘው “ድርሳን ወገድል ዘቅ/ያሬድ” ሲሆን የተጻፈበት (የተቀዳበት) ዘመኑም በ16ኛው መ/ክ/ዘ ነው። በሁለተኛ ደረጃ ጥንታዊ የሚባለው የቅ/ያሬድ ድርሳን እና ገድል በ17ኛው መ/ክ/ዘ/ የተጻፈው እና በሀገረ እንግሊዝ የሚገኘው ሲሆን፤ ሦስተኛው ደግሞ በዘመዶ ማርያም (ሰሜን ወሎ) የሚገኘው ሲሆን ዘመኑም በ18ኛው መ/ክ/ዘ ነው። በ19ኛው እና በ20ኛው መ/ክ/ዘ ሌሎች በርካታ ቅጂዎች በብዙ ቦታዎች ይገኛሉ። በውጭ ሀገር ከሚገኙት ቅጂዎች ውስጥ በፓሪስ ቤ/መጻሕፍት የሚገኘውን ገድል ኮንቲ ሮሲኒ የሚባል ምሁር ከግዕዝ ወደ ላቲን ተርጉሞ እ.ኤ.አ. በ1904 አሳትሞታል። ድርሳን፣ገድል፣ ተአምር እንዲሁም መልክአ ያሬድን ይዟል። ቀጥለን በዝርዝር እንመልከታቸው፤ 


1) ድርሳነ ያሬድ - ለቅዱስ ያሬድ ታሪክ ዋና ምንጭ ሆኖ የሚጠቀሰውና ከገድሉ ይልቅ ስፋት ያለው ድርሳኑ ነው። ሲጀምር እንዲህ ይላል፥ “በስመ፡ አብ፡ ወወልድ፡ ወመንፈስ፡ ቅዱስ፡ ፩አምላክ። ድርሳን፡ ዘቅዱስ፡ ያሬድ፡ ካህን፡ ቀርነ፡ ቤተ፡ ክርስቲያን፡ ዘይጼውዖሙ፡ ለመሃይምናን፡ ከመ፡ ይሴብሕዎ፡ ለእግዚአብሔር፡ በክላሕ፡ ወበዓቢይ፡ ቃል፡ ከመ፡ ሱራፌል። ....”

2) ገድለ ያሬድ - የቅ/ያሬድን የሕይወት ታሪኩንና ተጋድሎውን ዜና በአጭሩ የሚዘክር ሲሆን ሲጀምር እንዲህ ይላል፥ “በስመ፡ አብ፡ ወወልድ፡ ወመንፈስ፡ ቅዱስ፡ ፩አምላክ። ገድል፡ ወስምዕ፡ ዘቅዱስ፡ ወንጹሕ፡ ወብፁዕ፡ ወኅሩይ፡ ያሬድ፡ ካህን፡ ጸሎቱ፡ ወበረከቱ፡ ወሀብተ፡ ረድኤቱ፡ የሀሉ፡ ምስሌነ፡ ....” 

3) ተአምረ ያሬድ - ካህኑ ያሬድ የፈጸማቸው ገቢረ ተአምራት በርካታ ቢሆኑም በገድሉ ላይ ተመዝግበው የምናገኛው ግን ሦስት ናቸው። 

4) መልክአ ያሬድ - የኋላ ሊቃውንት ስለ ቅ/ያሬድ ክብር እንዲሆን “መልክእ” ደርሰውለታል። ሲጀምር እንዲህ ይላል፥ “በስመ፡ እግዚአብሔር፡ ሥሉስ፡ ዘበሰማያት፡ አቡነ። በምግባር፡ ወግዕዝ፡ ዘወለደነ። ያሬድ፡ ወጠንኩ፡ ለመልክእከ፡ ድርሳነ። አብርህ፡ ኅሊናየ፡ ወዘልብየ፡ ዓይነ። ወበልሳንየ፡ ጸሐፍ፡ ሐዲሰ፡ ልሳነ።” ... ይህ መልክእ በብዙ ቦታ የሚገኝ ሲሆን እኔ ማስተያየት የቻልኩት ፓሪስ ከሚገኘው እና ኮንቲ ሮሲኒ (1904) ካሳተመው ነው። 

5) የግንቦት ፲፩ ስንክሳር ንባብ - የግዕዙ ስንክሳር (እንዲሁም የባጅ - እንግሊዝኛ ትርጉም 1928፣ የኮሊ - የፈረንሳይኛ ትርጉም 1997፣ የትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት ሕትመት - የአማርኛ ትርጉም 1993 ዓ.ም.) ስለ ቅ/ያሬድ ሕይወት ይዘረዝራል። ሲጀምር እንዲህ ይላል፤ “ወበዛቲ፡ ዕለት ካዕበ፡ አዕረፈ፡ ያሬድ፡ ማኅሌታይ፡ አምሳሊሆሙ፡ ለሱራፌል። ወዝንቱ፡ ቅዱስ፡ እምአዝማዲሁ፡ ለአባ፡ ጌዴዎን፡ ውእቱ፡ እምካህናተ፡ አክሱም፡ ....” 

6) ነግሥ ዘያሬድ - ለቅ/ያሬድ ካተደረሱት የ“ነግሥ” ምሥጋናዎች መካከል አንዱ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የደረሰው ብሎ ይጀምራል፥ “ያሬድ፡ ቀሲስ፡ መዓርዒረ፡ ዜማ፡ ማኅሌታይ። መዓንዝር፡ ከመ፡ ወልደ፡ ዕሴይ። .....” ሁለተኛው ደግሞ አፄ ዘርአ ያዕቆብ የደረሰው ምሥጋና ሲሆን እንዲህ ይላል “ሰላም፡ እብል፡ ለያሬድ፡ ቀሲስ፡ ምሉዐ፡ መንፈስ፡ ለኢትዮጵያ፡ ነደቀ፡ በሃሌ፡ ሉያ፡ ምድራስ። አስተባልሐ፡ ደቂቃ፡ በዜማ፡ ሠላስ። መኃልይሁ፡ ውዱስ። በስብሐት፡ ሐዲስ።”

7) አርኬ - ፓሪስ የሚገኘው (ኮንቲ ሮሲኒ ያሳተመው) እና በትንሣኤ ማሳተሚያ የታተመው የስንክሳሩ አርኬ ስለ ቅ/ያሬድ ምሥጋናውን እንዲህ ብሎ ይጀምራል - “ሰላም፡ ለያሬድ፡ ስብሐተ፡ መላእክት፡ ለሕዋጼ። እንተ፡ አዕረገ፡ በልቡ፡ ሕሊና፡ መንፈስ፡ ረዋጼ።...”። በ17 መ/ክ/ዘ የተጻፈውና ለንደን (ብሪቲሽ ቤ/መ) የሚገኘው የስንክሳር አርኬ እንዲህ ይላል፤ “ሰላም፡ ለዝክረ፡ ስምከ፡ ዘተጸውዖቱ፡ መዓር።...”

ሐ) ስለ ቅ/ያሬድ የሚያስረዱ ሌሎች መጻሕፍት
1) ገድለ አረጋዊ - ከላይ እንዳየነው በትውፊት የገድለ አቡነ ጸሐፊ ቅ/ያሬድ እንደሆነ ይነገራል። የታተመው ገድለ አረጋዊ የጸሐፊነቱን ሚና ለሌላ ይሰጠዋል፤ ሁለቱን ሃሣቦች ስናገናዝባቸው ሊሆን የሚችለው መጀመሪያ ያሬድ ጽፎት በኋላ ሌሎች ገልብጠውታል ማለት ነው። ወደ ገድለ አረጋዊ ስንዘልቅ በርካታ ቦታዎች ላይ የቅዱስ ያሬድን ታሪክ መዝግቦት ይገኛል። ያሬድ በዘመነ ገብረ መስቀል ማሕሌቱን እንደጀመረ፣ ድርሰቱን ከብሉይ ከሐዲስ እንዳውጣጣው፣ ዜማውን ከመላእክት እንደሰማው፣ ወዘተ.... ይዘረዝራል። እንዲሁም ወደ ደብረ ዳሞ ወጥቶ ሕንጻ ቤ/ክ ሲመለከት “ወከልሐ፡ በቃለ፡ መዝሙር፡ ወይቤ፡ ይሔውጽዋ፡ መላእክት፡ እስመ፡ ማኅደረ፡ መለኮት፡ ይእቲ፡ ዖድክዋ፡ ዖድክዋ፡ ዖድክዋ፡ ወርኢኩ፡ ሥነ፡ ሕንጼሃ፡ ለቅድስት፡ ቤተ፡ ክርስቲያን።” ብሎ እንደዘመረ፡ ይናገራል።
2) ድርሳነ ዑራኤል - የቅ/ያሬድን ታሪክ ከያዙት የቤ/ክ መጻሕፍት መካከል አንዱ ድርሳነ ዑራኤል ሲሆን እመቤታችን ተገልጻ ቅ/ኤፍሬምንና አባ ሕርያቆስን “ዜማ እንዲደርስልኝ ውዳሴዬንና ቅዳሴዬን ለያሬድ ስጡት” ብላ እንዳዘዘቻቸውና ቅ/ያሬድም በተሰጠው ሀብተ ዜማ እንደዘመረ ይናገራል። ለቅ/ያሬድ ጽዋዓ ልቡና ያጠጣው መራሔ ብርሃናት ዑራኤል እንደሆነ ድርሳነ ዑራኤል ይገልጻል።
3) መጽሐፈ አክሱም - ይህ መጽሐፍ የአክሱም ጽዮንን ታሪክ እና የርስት ጉልቷን ሥሪት የሚናገር ሲሆን ስለ ቅ/ያሬድ ዜማ ድርሰት ይናገራል። እንዲሁም ከላይ በድርሳነ ዑራኤል የተገለጸውን ታሪክ (እመቤታችን ተገልጻ ቅ/ኤፍሬምንና አባ ሕርያቆስን “ዜማ እንዲደርስልኝ ውዳሴዬንና ቅዳሴዬን ለያሬድ ስጡት” ያለችውን) መዝግቧል።
4) ታሪከ ነገሥት - የኢትዮጵያን ታሪክ ከያዙት መጻሕፍት አንዱ የሆነው የዙርአባ (ዙራምባ) ታሪከ ነገሥት የቅ/ያሬድን ታሪክ የያዘ ሲሆን በተለይ በዑራኤል መሪነት ከአጼ ገ/መስቀልና አባ አረጋዊ ጋር ወደ ዙርአባ ተራራ እንደወጡ፣ በዙርአባ ለሦስት ዓመታት ቅ/ያሬድ ዝማሬና መዋሥዕትን እንዳስተማረ ይናገራል።

የቅዱስ ያሬድ በረከት ከሁላችን ላይ ይደርብን፤

ግንቦት ፳፻፰

Monday, May 30, 2016

ፖርት ሳይድ ማርያም ፡ ዘይት የምታፈልቀው ስእል

እህታችን ማሕሌት መኮንን  በግብጽ ፖርት ሳይድ ማርያም ተገኝታ ዘይት የምታፈልቀውን የእመቤታችንን ስእል ተኣምሩን በ ምስል ወድምጽ ታቀርብልናለች፥፥  ከዚህ በፊት ስለዚህ ተኣምር በሚከተሉት ፖስቶች ኣስነብበን ስለነበር በተያይዝነት ብታነቡት ሙሉ ተኣምሩን ትረዳላችሁ::


ከእጇ ዘይት የሚፈልቅ የቅድስት ኤልሳቤጥ አስገራሚ ታሪክ

ፖርት ሳይድ ማርያም በግብጽ

 

 

የእመቤታችንን ተአምር - ዲያቆን ሳሙኤል


የእመቤታችንን ተአምር ልንገራችሁ ማለትም ለእኔ ያደረገችልኝ ስሜ ዲያቆን ሳሙኤል ሀ'/ማርያም ይባላል የተወለድኩት በምስራቁ የሀገራችን ክፍል ሲሆን በዛ አካባቢ ኢ አማንያን ይበዛሉ ተወልጄ አንድ ዓመት ሲሞላኝ በፀና መታመሜን እና እናቴ ለድንግል ማርያም ተስላ እንደተረፍኩኝ ትነግረኛለች ከዛም 5 ዓመት እንደሞላኝ እናቴ ስዕለቷ ለቤተክርስቲያን ብፅዓት አድርጋ መስጠት ስለነበረ ወደ ታላቁ ገዳም አሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም ወስዳ ለአበ ምኔቱ አስረከበችኝ ልብ በሉ ይህ ገዳም ወንዶች ብቻ የሚኖሩበት ገዳም ነው እኔም ገና ብላቴና ሳለሁ ከአባቶች ጋር ተቀላቀልኩኝ በመቀጠልም ካለ ወጥ የሚበላውን የቃል ኪዳን ዳቤ እየበላሁ የቆሎ ትምህርቴን ጀመርኩኝ ህፃን ስለነበርኩኝ አዕምሮዬ ያስተማሩኝል ሁሉ ይቀበል ነበር በእንደዚህ ያለ ህይወት እየኖርኩኝ የግብረ ዲቁና ትምህርቴን አጠናቀቁኝ ከዛም ማዕረገ ዲቁና ተቀበልኩኝ አሁን ላይ ልብ በሉ ገዳሙ የዓንድነት ገዳም ስለሆነ የቀንድ ከብቶች እና የጋማ ከብቶች አሉት ስለዚህም ባህታውያን መናኞች እንዚህን ከብቶች በየተራ ወደ ጫካ በማሰማራት ይጠብቃሉ በተጨማሪም ለተላላኪነት ሁለት ሁለት ህፃን ይመደብላቸዋል በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ እኔም በ1991 ዓ.ም ምደባው ደረሰኝ ግንቦት 21 የመቤታችን ዕለት ማለትም 20 ለ21 አጥቢያ ህልም አየሁ አስደንጋጭ ህልም በወቅቱ ያሳድጉኝ የነበሩ አባት ባህታዊ ኀይለ ሚካኤል ስነግራቸው ገባድ ነገር ይገጥማሀል ግን ምን አትሆንም አሉኝ እሺ አባቴ ፀልዩልኝ ብዬ አብረን ከተመደብነው ልጅ ጋር ወደ ጫካ ሄድን የሄድንበት ጫካ በአካባቢው ስም ሶራ ይባላል ብዙ ኢ አማንያን ዘላኖች ያሉበት ቦታ ነው ከዛም ልክ ከኑ 6 ሰዓት ግንቦት 21 1991 ዓ.ም አስደንጋጭ ነገር ተከሰተ ሽፍቶች ማለትም በአጋባቢው አጠራር ኢሳዎች ያዙን እጃችንን የፍጥኝ አሰሩን ልብ በሉ እኛ ገና ያልጠነከርን ጨቅላዎች ነበርን ኡኡኡ ብለን ጮህን ከተራራው ድምፅ በስተቀር የደረሰልን የለም ሊያርዱን ቢላዋ ከሰገባቸው መዘዙ ጭንቀት ተፈጠረ አስተውሉ የሞት አፋፍ ላይ ነው ይህ በእንዲህ እዳለ በደመነፍስ እየታገልኩኝ ወደ ሰማይ ቀና አልኩኝ አንድ ነገር በአፌ ወጣ በታፈነ ድምፅ የአምላኬ እናት የጭንቅ አማላጇ ማርያም ሆይ እባክሽ ከልጅሽ ጋር ድረሽልኝ ከዚህ ጭንቅ ካወጣሽኝ በእራሴ እጅ የተሰራ ሰሌን (ማለትም የዘንባባ ሥሪት ምንጣፍ) ለቤተክርስቲያንሽ አስገባለሁ ብዬ ድምፄን ከፍ አድርጌ ጮኩኝ እመቤቴ በፍጥነት ደረሰችልኝ ሊያርደኝ የሚታገለኝ ሰው ከመቅፅበት ለቀቀኝ እኔም እሮጨ ነጭሎ የሚባል ዛፍ ስር ተደበኩኝ እመቤቴ በውስጤ ገባች አንዱ ጓደኛዬም እንዲሁ ተሳለ ደረሰችለት እነኛ አራጆች የእኛን ፊት ማየት አቅቷቸው ከብቶቹን በመያዝ ወደ ገላግሌ የሚባል አካባቢ ሮጡ እኔም በእመቤቴ ምልጃ ከሞት ተርፌ ወደ ገዳሙ እሮጥኩኝ የአደጋ ደወልም ደወልኩኝ ሁሉም መናንያን ምንድነው ብለው ተሰበሰቡ የሆነውን ነገርኳቸው ሁሉም በህብረት እንባቸውን አውጥተው አለቀሱ ከሞት የአተረፈኝን የድንግል ማርያምን ልጅ አመሰገኑ ከዛ ከብቶችን የዘረፉት ሰዎች ሲካፈሉ እርስ በእርስ ተገዳደሉ የአካባቢው ሽፍቶችም ወተቱን ሲጠጡ በተቅማጥ መሞት ጀመሩ የሚያደርጉት ሲጠፋቸው ገዳሙ ይቅርታ ያድርግልን ብለው ከብቶቹን መለሱ እናም ዛሬ ላይ ዓለም የእመቤታችንን ምልጃ ይሰማ ዘንድ ውስጤ አስገደደኝ ይህ ታሪክ ህያው እግዚአብሔር ያውቃል እሙን ነው ሼር በማድረግ ለዓለም እናድርስ የገዳሙ ታሪክ በዘሁ አምድ ይቀጥላል ለእኔ የደረሰች ድንግል ማርያም የአምላክ እናት ለእናንተም ትድረስላችሁ
አሜን
አሜን
አሜን
ያነበበው ሁሉ ሼር እንዲያደርግ በድንግል ማርያም ስም እጠይቃለሁ
ለበለጠ መረጃ 0911072282 ዲያቆን ሳሙኤል

ድንቃ ድንቅ ተኣምራት በቅዱሳን ገዳማት

Wednesday, May 18, 2016

ተዐምረኛው ጅሩ ሥላሤ ገዳም

ይህ የምታዩት ጅሩ ሥላሤ ገዳም ይባላል አሣሮ ወረዳ ወቅሎ ጊዮርጊሥ ቤ/ክ ጅሩ አርሤማ መንገድ ላይ ይገኛል:: ገዳሙ በብዙ ህዝበ ክርሥቲያን ያልታወቀ እና ያልተጎበኘ ነው:: ብዙ በረከት እና ተአምራት ያለበት ገዳም ሢሆን የጉዞ ማህበራት ወደዚ ገዳም ጉዞ በማዘጋጀት ምዕመናኑን የበረከቱ ተካፋይ እንድታረጉ እና ገዳሙንም እንድትደግፉ ሥል በሥላሤ ሥም ጠይቃለው:: ወሥብሃት ለእግዚዐብሄር::



ድንቅ ተዓምር በ ለጀት ኪዳነምህረት

Tuesday, May 10, 2016

የጠቋር መንፈስ ጠባያትና አያያዝ .

የጠቋር መንፈስ ጠባያትና አያያዝ .
የጠቋር መንፈስ ከሌሎች ክፉ መንፈሶች ሁሉ እጅግ በጣም ለየት የሚያደርገው ስዎችን ከአቅም በላይ በሆነ መንገድና ሁኔታ ውሰጥ በእጅጉ የሚፈትን አሮጌውን በአዲስ ለመተካት የሚያስችል የተለያዩ የጥቃት ሥልቶች ያሉትና በአንድ ጊዜ በርካታ የጥቃት ግንባሮችን በሰው ህይወት ላይ መክፈት የቻለ ወይም የሚችል አደገኛ መንፈስ መሆኑ ነው ፡፡ በህብረተሰቡ ውስጥ መንፈሳዊ መልአክ ጠባቂና ጸሎተኞ የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ይህንን ስም ተከትሎ የሚሄድ ማንኛውምንም ሌላ መንፈስ በመጫን ለራሱ የተሻለ ቦታ በመስጠት እልከኞ የመሆን ከፍተኛ አቅም ያለውና የመሪነት ስሜት የሚታይበት መንፈሰ ነው ፡፡
. .
መንፈሱ የህንን ሥያሜውን ያገኘው ለብዙ ዘመናት በኮከብ ቆጠራ ሲያሟርቱ በሚኖሩ ሰዎች አማካኝነት ነው ፡፡ የመጠሪያውንም ጠባይ ተከትሎ ጠቋር የሚለው ቃል አፍሪካዊ መንፈሰ መሆኑን ለማሳየት ነው ፡፡ በመሆኑም ሥያሜው ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥና ይዘት ያለው ሆኖ የሚንቀሳቀስ መንፈስ ነው ፡፡
. .
ከዚህ በተጨማሪም ሥራው የጠቆረ ህይወት የጨለማ ኑሮን የሚገልጥ የሚያመለክትና የሚያጎናጽፍ ነው ፡፡ ግብር ስጦታውና ሽልማቱ ጥቁር ቀለም ያለበት እንስሳም ይሁን አልባሳት የፍላጎቱ መለያ ነው ፡፡ በአብዛኛው ለማለት ይቻላል ጥቁር ቀለም የጠቋር ዋነኞ መገለጫ ነው ፡፡
. .
ጠቋር በግራ እጁ ለሚሰራ ሰው ግራውን በቀኝ ለሚሰራውን ሰው ደግሞ ቀኙን ይይዛል ፡፡ ሰው እንደ ልቡ ተንቀሳቅሶ እንዳይሠራ ዋናውን ሀይሉን ክንዱንና ሕሊናውን በሥውር ይቋጣጠራል ፡፡ ሴቷ አጋንንት ሻንቂት ስትባል ወንዱ ደግሞ ጠቋር ሻንቆ ይባላል ፡፡ መንፈሱ ስያሜውን ያገኘው በአውደ ነገሥት ውስጥና ቀደም ሲል ሌዋውያን አይሁዶች ኢትዮጵያ በመጡበት ወቅት ሲሆን በዚሁ ጊዜም ሁለት ዓይነት ደብተራዎች አብረው መጥተው ነበር ፡፡
. .
የመጀመሪያዎቹ ታቦተ ጽዮንን የሚያገለግሉ የምሥጋናና የአምልኮት እግዚአብሔር ደብተራዎች (መንፈሰሳዊ ሊቃውንት) ሰሆኑ ሁለተኞቹ ደግሞ ምትሀታዊውን ትምህርት ከአረማውያን የተማሩ ሌዋያን ማለትም የእስራኤል ነገዶች ነበሩ ፡፡ ሁለቱም አገራችን ከገቡ ጊዜ ጀምሮ ሰፋ ያለ ቦታ ከማግኘታቸው ጋር ተያይዞ ሁለተኛው ወገን በቀጥታ የክፉው መንፈስ አካል ሆኖ በአውደ ነገሥቱ ምሪት ውስጥ ጠቋር የምለውን ስያሜ አገኘ ፡፡
. .
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲህ ዓይነቱ መንፈስ በገዢነት ላይ ሆኖ ከላይ እንደቆየ የሚያሳየን በዮሐንስ ወንጌል ፰ : ፴፱ ላይ የአብርሃም ዘር ነን የሚሉትን ተቆጣጥሮአቸው ነበር ጌታ ኢየሱስም ለመንፈሳዊ በረከት ተዘጋጁ ሲላቸው እኞ የቃል ኪዳን ተስፋና የአብርሃም ልጆች ነን ፡፡ እኞ ቀደም ሲል አምልኮት ራእይ ተስፋና የተሻለ እድል ከነበራቸው ዘሮች ውስጥ ነን እያሉ ይመጻደቁ ነበር ፡፡
. .
በቀደሙት አባቶች አምልኮት እየተኩራሩና እየተመኩ አስተሳሰባቸው ተግባራቸው ግን ተግባር የሌለው የወግ አምልኮትን መንገድን የተከተለ ነበር ፡፡ በቀደመው በአብርሀም ስም ሰማያዊ ተስፋን የሚያገኙ መሥሏቸው ኑሮአቸውን ግብዝነት በተመላ ፈሪሳውያንነት ይመሩ ነበር ፡፡
. .
በዮሐንስ ወንጌል ፰ : ፴፱
" መልሰውም። አባታችንስ አብርሃም ነው አሉት። ኢየሱስም። የአብሃም ልጆች ብትሆኑ የአብርሃምን ሥራ ባደረጋችሁ ነበር ፡፡ ነገር ግን አሁን ከእግዚእብሔር የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ፤ አብርሃም እንዲህ አላደረገም። እናንተ የአባታችሁን ሥራ ታደርጋላችሁ አላቸው። እኛስ ከዝሙት አልተወለድንም አንድ አባት አለን እርሱም እግዚአብሔር ነው አሉት፡፡ ኢየሱስም አላቸው። እግዚአብሔርስ አባታችሁ ከሆነ በወደዳችሁኝ ነበር፤ እኔ ከእግዚአብሔር ወጥቼ መጥቻለሁና፤ እርሱ ላከኝ እንጂ ከራሴ አልመጣሁምና ። ንግግሬን የማታስተውሉ ስለ ምንድር ነው? ቃሌን ልትሰሙ ስለማትችሉ ነው።እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ ፡፡" አላቸው ዲያብሎስ አባት ሊሆን የሚችልበት መንገድና አጋጣሚ በጣም ሰፊ ነው ፡፡ ከዚህ አንጻር ጠቋር የሚባለው መንፈስ ይህንኑ መንገድ ያጠናክራል ፡፡
. .
የፈሪሳውያን መንፈስና የጠቋር ሥልት በብዙ መንገድ ተመሳሳይነት ያለው ሲሆን የሁለቱም መግለጫ በማስመሰል ዘመንና ጌዜን ጨርሶ ከእግዚአብሔር ክብር መለየት ነው ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ሲነግረን
. .
"ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ለሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፥ እንዲህ ሲል። ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ መቅደስ ወጡ፥ አንዱ ፈሪሳዊ ሁለተኛውም ቀራጭ። ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ ። እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤ በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ። ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን ። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር ። እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል።"
. የሉቃስ ወንጌል ፲፰ : ፱
በማለት የሚገልጸው ቃል ክፉ መንፈስ በሰዎች ላይ ሲያድር እንዲህ ዓይነት የውስጥ ትዕቢት በማሳደር ፈረሐ እግዚአብሔር በማራቅ እምነትን የሚፈትን መሆኑንን ከፊሪሳዊው የጸሎት ልምድ መገንዘብ እንችላለን ፡፡ በመሆኑም ጠቋር በመንፈሳዊ ሥፍራና በጸሎት ወቅት በትቢት ሰዎችን ሊያስትና አቅጣጫቸውን ሊያስለውጥ ይችላል ፡፡ በአገራችን ልማዳዊ አነጋገር ጠቋር ዳዊት ደጋሚ አሸዋ ቃሚ ቅጠል ለቃሚ የባላል ፡፡ እናቶች በዚህ መንፈስ በጣም ተታለዋል ፡፡ መንፈስ ውስጣቸው እያለ አብረው ይመነኩሳሉ < የእኔ እኮ...ዳዊት ደጋሚ ነው ! እንዲህ ቀላል አይደለም ቤተክርስቲያን ሳሚ ገዳማዊ መነኩሴ ነው ...ወዘተ እያሉ በስፋት እንዲቀበሉት የሚደርጋቸው ሲሆን አውደ ነገሥቱም ይህንን መንፈስ ያጠናክረዋል ፡፡
. .
. .
. የጠቋር መንፈስ ሥልቶች .
ይህ የጠቋር መንፈስ ከፍተኛ የማስገደድ ኃይል ስላለው ራሱን ትልቅ አድርጎ በማሳየት ሌሎች በግድ በትልቅነት እንዲቀበሉት ያደርጋል ፡፡
. .
• በሕልም በማስፈራራት
• ያሳየውን ራእይ በሚቀጥለው ቀን ተግባራዊ በማድረግ
• በሰውነት ውስጥ የተለያዩ ምልክቶች በመስጠት ነው ፡፡
. .
ጠቋር ሰዎችን በቀላሉ ለመያዝ የሚከተለው ሥልት ከሌሎች በላቀ ሁኔታ የተለያየና የበለጠ ነው ፡፡ከእነዚም ውስጥ በገባበት አጭር ጊዜ ውስጥ በአስገዳጅነት ከፍተኛ ሀይልን ተጠቅሞ በፍጥነት ልቡናን ሰውሮ ሕሊናን በማስጨነቅ ወደፈለገው አቅጣጫና በሚፈልገው መንገድ መምራት መቻሉ አንድ ነው ፡፡ ይህን ክፉ መንፈስ ብዙ አባቶችና እናቶች ለምደውታል ፡፡ ልምምድም በባሕር ውስጥ ካለው መሸነፍ ጋር የያይዞ ለአምልኮት ከሚሰጡት ቦታና በጸሎት ከሚቃወሙት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ደካማነት የተነሳ በቀላሉ ተቀብለውት እንዲኖሩ ያደርጋል ፡፡
. .
ጠቋር ከሕቡዓን (ከተሰወሩ) ቅዱስ ጋር ያገናኛል በማለት የመናፍስቱ ሹክሹክታ እንደዚ ቅዱሳን ድምፅ ምናባዊ ውልብታውን ደግሞ እንደ ፃድቃን ብርሃናዊ ገጽ በመቁጠር ለማሳመን የሚሞክር መንፈስ ነው ፡፡
በባሕርይ ውስጥ አባት ሆኖ የመቀመጥ የመያዝ ጠባዩ በሥፋት የታወቀ ነው ፡፡ ብዙዎች ጠቋርን መንፈሳዊ ነው! ምንም ጉዳት አያመጣም እንዲያውም ጠባቂ ረዳትና አጋዥ ነው ይሉታል ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ራእይን ይገልጣል ተብሎ የተለያዩ መሻቶችን የሚጠይቅና ባመኑትና በሰገዱለት ዘንድ የሚገበርለት መንፈስ ነው ፡፡
. .
. ጠቋር በጸሎት ሥፍራ የጸሎቱን ባሕርይ በዝማሬ ቦታ የዝማሬውን ባሕርይ ወዘተ ... ይከተላል ፡፡ መንፈሱ በጣም ጥንቃቄ የሚያደርገው በቅዱስ ቁርባን አምልኮት ላይ ብቻ ነው፡፡ በዚህ በኩል የሚመጣበትን የእግዚአብሔር መንፈሰ ጨርሶ ሊቋቋመው ስለማይችል ሰዎች ወደ ቅዱስ ቁርባንና ወደ እግዚአብሔር አምልኮተ እንዳይገቡ የመጀመሪያውን የመዘግየትና የመጎተት ውጊያ ይከፍታል ፡፡ ኑሮአቸውን የተሟላና የተሳካ እንዳይሆን አስሮ በመያዝ በእግዚአብሔር አምላክ እንዲማረሩ ያደርጋል ፡፡ በቤተሰብ ምሥረታ ውስጥም ገብቶ በልጆች አእምሮና ሕሊና ውስጥ አፍዝ አደንግዝ ለመሆን ጊዜ አይፈጅበትም ፡፡ ምክንያቱም አባት ተብሏልና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "እናንተ ከአባታቸው ከዲያብሎስ ናችሁ " ተብሏል ፡፡ ከላይ የሚነሳ ወንዝ ወደታች ለመውረድ ምን ያስቸግረዋል ? ጠቋር ከላይ ያለውን አጥብቆ ያዘ ማለት ታች ያለውን መቆጣጠር ይችላል ፡፡
. .
ጠቋር ሥልታዊ መንፈስ በመሆኑ ወደ ሰውነት ለገብ ሌሎች መንፈሶች የአሥራር ሥልቱን ያስተምራል ፡፡ ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ጸሎተና ጸበል ሥፍራ ሰንሄድ ውጭ ተለይቶ የሚጠብቁንን መንፈሶች ሥልታቸውን ለውጠው ከጸሎትና ከጸበል መልስ ወደ ሰውነት ውስጥ በመግባት በልብ ውስጥ የነበረውን ሠላምና ጤና ማወክ እንዲጀምሩ ያበረታታል ፡፡
ሌሎች መንፈሶች እንዲደበቁ ተራ በተራ እንዲጨው ጊዜ እንዲያባክኑና ያስከተሉት ችግር እንዲባባስ ከማድረጉም በላይ የጠቋር መንፈስ ቶሎ እዳይያዝ በዋላ የገባውን መንፈስ አጋፍጦ በመስጠት ራሱን ደብቆ መንፈሶቹ ከወጡ በዋላ ተመልሰው እንዲገቡ ደጋግሞ በሌላ ዓይነት አቀራረብ እንዲናገሩና እንዲጮዉ በማድረግ ዘዴውን ይቀይሳል ፡፡
" የአማልክት አምላክ፥ የነገሥታትም ጌታ፥ ምሥጢርም ገላጭ ነው። "
( ትንቢተ ዳንኤል ፪ : ፵፯)
ጠቋርን በሁለት መንገድ እናገኘዋለን
1'ወደ አውደ ነገስት የኮከብ ቆጠራ ውስጥ ስንገባ
2'ጊዜና ዘመኔን ፍታልኝ ብለን ወደ ጠንቋይ ቃልቻው አስማተኛውና መተተኞው ዘንድ ስንሄድ ነው ፡፡
. .
. 'ከጠቋር የረቀቀ ምሥጢራዊ የጥቃት ዘዴዎች መካከል .
. .
• ሰዎችን በፍጥነት የመልመድ ጠባዩና በከፍተኛ ደረጃ ተመሳስሎ የመኖርና የማድፈጥ ችሎታው
• አንዳንዴ የምታያቸውን ራእዮች እውነተኞ ለማስመሰል ሰፋ ያለ ጊዜና መንገድ በሕይወትህ ውሰጥ መምራት መቻሉ
• ባሕርይህን የመምሰል ጠባዩ የተዋጣለት መሆኑ
'ለጸሎት ስትዘጋጅና ስትጸልይ የሚያመጣው ፈተና '
• የትግሉ ሥልት በኑሮህ ውስጥ ያሉትን ጎዶሎዎች በሙሉ በልብህ ላይ ይጽፍልሃል በዚህም ሃሳብህ ይከፈልና ጸሎትህን ያሰናክላል
• ባለፋ ጉዳዮች ላይ እንድትጨነቅና ምነው እንዲህ ባረኩት ኖሮ ብለህ እንድታስብ በጸልሎትህ ሰዓት ሃሳብ ያመጣልሃል
• ወደፊት የምትሠራቸውን ሥራዎች ከፊትህ ያመጣብህና እንከኖችን በመደርደር በሀሳብ እንድትዋጥ ያደርግሃል በዚህ ጊዜ ፍንጭ ሳይሰጥህና የማንነቱ ጠባይ ሳይታወቅ በመንፈሳዊ ሕይወትህ ውስጥ ባሉት ርምጃዎች ሁሉ ብዙውን መንገድ አብሮህ ስለሚጓዝ አታውቅውም ፡፡ ምክንያቱም ማንነቱና ምንነቱ በአንተ ባሕርይ ውስጥ የተደበቀ ነው ፡፡
. .
ይህ መንፈስ በጠበል ቦታ ራሱን የመደበቅና የመሰወር ከፍተኛ ችሎታ የለው ብቻ ሳይሆን የሚያስገርመው በጠበልና በተለያየ የአገልግሎት ሥፍራዎች ላይ እየጮኸና ወጥቶ የሄደ እየመሰለ በማዘናጋት የተዳፈነ እሳት ሆኖ ለጊዜው ውስጣችን ተረጋግቶ ጸጥ ብሎ መቀመጥ የሚችል መንፈስ መሆኑ ነው ፡፡
. .
ሌላው የረቀቀ ሥልቱ ደግሞ ራሱን በማመሳሰል እንደ ቅዱስ መልአክም ለመሆን እየቃጣው ንስሐ ግቡ ጫማ ከመግቢያ በር አውልቁ እያለ በጠበል ቦታና በአንዳንድ የጥምቀት ቦታዎች ገላጭ በመሆን የብዙ ክርስቲያኖችን ልቦና በመሳብ ውስጣዊውን የእግዚአብሔር አምልኮ
ጥንካሬያቸውን ያጠናል ይሰልላል ፡፡
. .
. ውጫዊ እይታን ማደናገር .
. .
የጠቋር መንፈስ ካሉት ክፉ ጠባያት መካከል አንዱና ዋናው ውጫዊ እይታን በማዘበራረቅ ልቦናን መረበሽ ነው ፡፡ ክፉው መንፈስ በዓይንና በልብ ውስጥ በማድፈጥ መንፈሱ ያለበት ሰው ለሚያየው ነገር ትኩረት እንዳይኖረው አድርጎ ያንን የተመለከተውን ነገር አዛብቶ በማቅረብ ልቦናውን በመረበሽ አእምሮውን ይበጠብጣል ፡፡
. .
. ውጫዊ ድምጾችን አጣሞ ማሰማት .
. .
ዘመድ ቤተሰብ ጎረቤት ጓደኛ ውስጥ ተንኮል እንደሚፈጽሙ አድርጎ ማሳየት ሳይናገሩ እንደተናገሩ አድርጎ ማሰማት ያላወሩትን እንደ አወሩ አድርጎ በማሳመን በክፉ እንድናስባቸውና እንደናያቸው ያደርጋል ፡፡
. .
, የእንስሳትን ድምጽና ጩኸት መተርጎም .
. .
. ከመንፈሱ ሥውር ወጥመዶች መከላከል ለምሳሌ : ጅብ ሲጮህ መቁጠር ወፏ ያለ ወትሮዋ ለየት ያለ ዝማሬ አሰማች ውሻው እንዲህ ብሎ አላዘነ ጉንዳን በስልፍ ሆኖ ወደ ቤት ገባ ወዘተ ... በማለት እየተረጎምን የሚመጣውን ጊዜ ከክፉ ነገር ጋር በማዛመድ በሥጋትና በፍርሃት ተቆራመደን እንድንኖር ማድረጉ አንዱ ነው ፡፡
. .
. . . ሌላ ሰው የማያየውን መመልከት .
. .
ጠቋር ዓይን ላይ በመቀመጥ በአንድ ሰው ላይ ያደረን ክፉመንፈስ በማሳየት ያስደምመዋል አንዳንዴም መላእክትን አስመስሎ በመናገር በብዥታ ውስጥ መልእክት ያስተላልፍለታል ፡፡
. .
. የሸክም ጫና መፍጠር .
" ጫንቃውን ከሸክም፥ እጆቹንም በቅርጫት ከመገዛት አራቅሁ።"
(መዝሙረ ዳዊት ፹፩:፮)
. .
የጠቋር ክፉ መንፈስ ከሌሎች ውቃቢዎች አውሊያዎችና ዛሮች ለየት የሚያደርገው በቀኝ ትከሻ ላይ ተቀምጦ ትልቅ ድንጋይ ወይም ከባድ ዕቃ የተሸከምን ያህል እንዲሰማን በማድረግ ብርቱ በትከሻ ላይ ድበታና ጫናን መፍጠር ሌላው የሚታወቅበት ገጽታው ነው ፡፡ ሌላው ችግር በትከሻ ላይ ወይም በጀርባ በኩል ሆኖ በብዥታ የቆመ ሰው መስሎ ገጽታውን ማሳየት የተለመደ ልዩ ተግባሩ ነው ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በአውላላ ሜዳ ላይ የቡና ሽታ ወይም የሽቶ መዓዛ በማምጣት የመንፈሱን የሽታ ፍላጎት ከሚሸተው ሰው ስሜት ጋር በማስተሳሰር የልብን አምሮትና መሻትን በሽታው መዓዛ አማካይነት እንዲናፍቅ ያደርገዋል ፡ ፡
. .
- ውስጥን ማድመጥ .
ውስጥን አዳምጦ በጎውን ነገር መሸሽ ፣ ውስጥን አዳምጦ ክፋትን መለማመድ ፣ ውስጥን አዳምጦ የሌሎችን ሕይወት ለመተናኮል መመልከት ፣ ውስጥን አዳምጦ አጋንንቱን ማገልገል እነዚህ ውጥን የማድመጥ ልምምዶች በብዙዎቻችን ሕይወት ውስጥ ሥር ሰደው ከተቀመጡ ቆይተዋል ፡፡ ምክንያቱም ቤተሰባችን ከቅዱስ ቁርባን ሀይልና ከመንፈሳዊ በረከት በመውጣቱና በመራቁ ነው ፡፡ በሌላ አነጋገር በዘራችን ውስጥ ዘልቀው ጣልቃ የገቡ ርኩሳን መናፍስት አብረውን ዘር ሆነዋል ፡፡ ስለዚህ ውስጣችን ስናዳምጥ ብዙ እንጎዳለን ፡፡
. .
ጠቋር ከውስጥ ሆኖ የነገረህን ሀሳብ የበለጠ እንድታምነው በሕልም አሳምሮና አስተካክሎ ያሳያል ፡፡ ከዚህ መተጨማሪም በስው ላይ አድሮ ያንኑ ሀሳብ ከሌላ ሰው አንደበት እንድትሰማው ሰው የዘጋጅልሃል ፡፡
. .
, የጠቋር መንፈስ በአውደ ነገሥቱ ከፍተኛ ቦታ የተሰጠውና ከስያሜው የተነሳ ታላቅ የተባለ ቆየት ብሎ ቀኝን በመያዝ ጠባቂ መልአክ የሚባል ልዩ ስያሜና ክብር የተሰጠው ነው ፡፡ ብዙዎች ሳያውቁት ተከትለውታል የአምልኮት ክብር ሰጥተውት በውስጥ በኩል የሚነግራቸውን እያዳመጡ ችግራችንን ይቀርፋልናል ብለው በጨላማው የአስተሳሰብ ስሜት ይመሩበታል ፡፡ ይህ የተሳሳተ የጥፋት መንገድ በትውልዳቸውም ውስጥ ቀጣይ ሆኖ አብሮ በመወለድ በተለያየ ዓይነት ሁኔታ ልጆቻቸው በመንፈሱ እርግማን እንዲፈተኑ ያደርጋቸዋል ፡፡
. .
'የጠቋር መንፈሰ ለሰዎች የሚያወርሳቸው አንዳንድ ጠባያት
. .
የጠቋር መንፈሰ አጋንንት እና ሰይጣን ቢሆንም ንግሥናውና የሚጠራበት ስም በዛሮችና በውቃቢዎች ዘንድ እንደ ትልቅ ማዕረግ ስለሚታወቅለት ራሱን ታላቅና ሀያል አድርጎ ይቆጥራል ፡፡
. . . መንፈሱ የሰው ልጆችን ሕይወትና ኑሮ የሚፈትንና ለፈተና አሳልፎ የሚሰጥ ወይም የሚዳርግ ክፉ የዲያብሎስ መንፈስ በመሆኑ አንዴ ውስጣችን ከገባ ባሕርያችንን ለውጦ እልከኛ ፣ ደፋር ፣ ጉልበተኛ ጠበኞ ትዕቢተኛ ቁጡና ሀይለኞ .. ወዘተ ስለሚያደርገው ሕይወታችንን ከሌሎች ሰዎች ጋር ያለንን መልካም ግንኙነት ሁሉ አደጋ ላይ በመጣል ያበላሻል ፡፡
. .
. ጭንቀትን መፍጠር .
" በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፥ ከመከራቸውም አዳናቸው፤" (መዝሙረ ዳዊት ፻፯:፮)
አእምሮአችን ውስጥ የእርሱን ውሳኔ የራሳችን ውሳኔ እንዲመስለን ያደርጋል ውሎ ሲያድር ግን ምን ሆኜ ነው እንደዚህ ዓይነት ውሳኔ የደረኩት ብለን እንድንጨነቅና ሕሊናችንን ክፉኞ እንድንወቅስ ያደርጋል ፡፡ በዚህ ሁኔታ መንፈሱ ከአእምሮ ከሕሊህና ከልቦናህ በአጠቃላይ ከራስህ ጋር እየተጣላህ እንድትኖር ስለሚያደርግህ ጭንቀት የማይለየው ሰው ትሆናለክ ፡፡
• የጭንቀቱ ዓይነቶች •
ሀ.ራስህ የምትደብቀው ጭንቀት ፣ የሚያስጨንቀው ጉዳይ የሚታወቅ ይሆንና ለምሳሌ ባል ለሚስቱ ሚስት ለባልዋ የማይገልጹት ይሆናል ፡፡
ለ.የተሰወረ ጭንቀት ፣ አስጨናቂው ፡ ጭንቀት ጭንቀት ይልሃል ፡፡
ሐ.የተገለጠ ጭንቀት ፣ የጭንቀቱ ጉዳይና ሁኔታ በደንብ ልታውቀውና ልትገልጸው ትችላለህ ፡፡ ነገር ግን ወደ መፍትሔ እንዳትሄድ ጭንቀትህን የሚያባብስ የሚጫንህ መንፈስ ይኖራል ፡፡
• የፍርሀት መንፈስን ማንገሥ •
" በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም። " ( መዝሙረ ዳዊት ፳፫ : ፬ )
. .
ሀ.የሥጋ ፍርሃት (ውጫዊ ) ለምሳሌ አውሬ ስናይና ከፍተኛ ድምፅ ሲጮህብን የሚፈጠርብን ድንጋጤ ከነባራዊው ዓለም ወይም አውጭ የሚመነጭ የሥጋ ፍርሃት ነው ፡፡ ዲያብሎስን ብዙ ጊዜ በሥጋዊ ዓይናችን የምንገነዘበውን ከመንፈሳዊ ጉዟችን ለማደናቀፍ ይህን ዓይነቱን ፍርሃት ያመቻችልናል ፡፡
ለ.የነፍስ ፍርሀት ( ውስጣዊ ) ከውስጣችን የሚመነጭ የፍርሀት አየነት ነው ፡፡ ነፍስን የሚያስፈራው ሀይል ደግሞ ዲያብሎስና ሠራዊቱ ነው ፡፡ቤታችንን ኑሮችንን ሀብታችንን ጤናችንን ... በአጠቃላይ ሕልውናችንን ረግጦ የያዘው ዲያብሎስ የውስጥ ፍርሀታችንና ጭንቀታችን ሁሉ መሠረት ነው ፡፡ ሐኪሞቻችንና ሌሎች የመስኩ ሙያተኞች ለሁሉም የፍርሃት ዓይነቶች ፎቢያ የሚል የጋራ መጠሪያ አበጅተውለታል፡፡
. .
. ለምሳሌ aqua phobia - ውሃን መፍራት
. Achluo phobia - ጭለማን መፍራት
. Avio phobia - የአውሮፕላን ጉዞን መፍራት
. gamo phobia - ጋብቻን መፍራት
. Ecclesio phobia - ቤተክርስቲያን መፍራት
. .
. የጠቋር መንፈስ የፍርሀት ጥላዎች .
. ይህ መንፈስ መንፈሳዊ መሠረት የሌላቸውንና ጾም ጸሎት ስግደት የማያውቁትን እንዲሁም ልማዳዊ አምልኮት የሚከተሉትን ሰዎች በማስፈራራት የሚበረታ ሲሆን በዓይን-ሕሊናቸው በፍርሃት እንዲዋጡ በብዥታ ማደናገርና ከዋላቸው ጥላ መስሎ በመቆም በመክበድ በበላያቸው በማንዣበብ ሰውነታቸውን በመጎንተልና ማስደገጥ የልብ መራድና የአእምሮ መጨነቅን በመፍጠር ወደ እብደት የሚወስደውን የአእምሮ ሕመም እንዲፈጠርባቸው ያደርጋል ፡፡
. .
. በአጠቃላይ ይህ የድፍረት መንፈስ የሰው ልጆችን ሕይወትና ኑሮ እየፈተነ በስኬት በእድገት ጎዳና ላይ እንዳይረማመዱ አድርጎ ወደ ጨለማ የሚመራ ቢሆንም በእምነት ሀይል እግዚአብሔር በሰጠን የእግዚአብሔር ልጅነት በምሕረቱና በቸርነቱ ጥላ እየታገዝን በቅዱሳን መላእክት እርዳታ በፃድቃን መንፈስ ምልጃ እየተረዳን በቅዱስ ወንጌል የቃሉ ብርሃን እየተመራን በክርስቶስ ሥጋና ደም ስንታተም ይህንን ጠላታችንን ከሕይወታችንና ከዙሪያችን ልናስወግድበት የምንችልበት ሀይል እግዚአብሔር ይሰጠናል ፡፡
" አንተ መብራቴን ታበራለህና፤ እግዚአብሔር አምላኬ ጨለማዬን ያበራል።በአንተ ከጥፋት እድናለሁና በአምላኬም ቅጥሩን እዘልላለሁ።"
. መዝሙረ ዳዊት ፲፰ : ፳፰ - ፳፱
ምንጭ "በማለዳ መያ`ዝ መጽሐፍ" ✞ በመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ
!!! እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ በቅርቡ ቀን !!!
☞ ክፉ መናፍስቶችን የማዋረስ ምሥጢራዊ ጥበብ

የዝሙት መንፈስ ምንድነው? አይነጥላ ምንድነው?