Saturday, April 19, 2014

ትንሳኤን በተመለከተ መልክት ከ መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ

 መምሕር ግርማ በሙኒክ የበራቸው ኣገልግሎት እና ውጣ ውረዶች
ከሙኒክ  ደ/ብ/ ቅዱስ ገብርኤል ሰበካ ጉባኤ የተሰጠ መግለጫ



























 የኣዘጋጅ ኮሚቴው ምላሽ




24.10.2014 በ ሙኒክ የተደርገ የብሶት ሰልፍ


የመምህር ግርማ ወንድሙ መልክት በራዲዩ አቢሲኒያ




Sunday, March 30, 2014

ባሕታዊ አባ ገብረ ጊዮርጊስ

ባሕታዊ አባ ገብረ ጊዮርጊስ በቦሌ አየር ማረፊያ ደ/ፀ/ቅ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የተደረጉ የስብከት እና የፈውስ አገልግሎት

Holy water at Entoto Kidane Mihret Church የ እንጦጦ ኪዳነምህረት ጸበል

Thursday, March 20, 2014

ሰበር ዜና - ሕገ ወጥ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን "መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ" በሚል ስያሜ የተበተነው ደብዳቤ ሕገ ወጥ በመሆኑ የሚመለከተው ሁሉ ይህን ግንዛቤ እንዲወስድ አሳሰበች፡፡
በሚል ከዚህ ጋር ተያይዞ የወጣውን እና የተሰራጨውን ደብዳቤ አስነብበናል:: አሁን ከ ከ ቅዱስ ፓትሪያሪኩ  http://www.eotc-patriarch.org/#
 ድኅረ ገጽ በወጣው መግለጫ ደብዳቤው ጥንቃቄ እንዲደረግበት ማሳሰቢያ ተሰጥቷል:: ደብዳቤው ከታች እንደምትመለከቱት ነው::
የቀድሞውን ደብዳቤ በተመለከተ መምህር ግርማ በሬድዮ አቢሲኒያም ሆነ ተከታታይ በወጡት VCD 26 እና 27 ላይ የተናገሩት ነገር የለም:: ደብዳቤውም ወጣ የተባለበት ከአመት በላይ ያለፈው ግዜ 05/19/2005 በዚህ ጉዳይ ላይ መምህር ግርማ ያረጋገጡልን ነገር የለም:: ስለዚህ ይህን አይነት ድርጊት እየሰራ የመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙን ስም ለማበላሸት የሚጥሩ ስላሉ እርሳቸውን ተጠያቂ ከማድረግ እንድንቆጠብ እናሳስባለን:: ሰሞኑን የርሳቸው ቭኢዲዮ ከነድረገጹ ሁሉ በማጥፋት የ እግዚያብሔር ስራ እንዳይተላለፍ እንቅፋት የሆኑ እንዳሉ የምናውቀው ነው:: ከ ሁለት ደርዘን በላይ ምስሎች አሁን በ ንቁ ተአምረ ጽዩን ማየት የሚቻለው የተወሰኑንት ብቻ ነው::

ይህ ድረ ገጽ የተሳሳተ መረጃ በማቅረብ አላስፈላጊ መደነጋገር ውስጥ ስለከተትን ይቅርታ እንጠይቃልን::  የመምህር ግርማ አገልግሎት መስፋፋት እና የሕዝቡን መዳን ስለምንወድ አገልግሎታችንን ከበፊቱ ይልቅ የተጠናከረ እንዲሆን እንተጋለን:: 

መዝ 119: 121 "ፍርድንና ጽድቅን ሠራሁ፤ ለሚያስጨንቁኝ አሳልፈህ አትስጠኝ።"

Thursday, February 27, 2014

መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ ተሰጣቸው

ከዚህ በፊት መምህር ግርማ ወንድሙ ከ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አገልግሎት መታገድ በተያያዘ የቀድሞው የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አስተዳዳሪ መላከ ሰላም ዘላለም እሰይ ስለ መምህር ግርማ ምን ይላሉ? በሚል አገልግሎታቸው የተቋረጠበትን መልካም ያልሆነ ድርጊት እና የመምህር ግርማ ወንድሙን እውነተኛ ማንነት የሚያስረዳ ቃለምልልስ አስደምጠን ነበር:: ከታች በተያያዘው ደብዳቤ ላይ መላከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ የተሰጣቸው መሆኑን ያሳያል::
ደብዳቤው እንደሚከተለው ይነበባል
ቀን 26/12/2005
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ የወንጌል አገልግሎትና እንዲሁም የሕሙማን ሐብተ ፈውስ እንዲሰጡ ከብጹዕ ወቅዱስ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልካም ፍቃድ የተፈቀደልዎት ሲሆን ይህን አውቀው በፍቅር በሰላም እንዲያገለግሉ እናስታውቃለን::
በክርስቶስ ሰላም
ተጨማሪ መረጃ
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13144
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ማናቸው?

VDC part 26 ወጥቷል::

የቀድሞው የእገዳ ደብዳቤ

በሮም ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የተላከ ደብዳቤ 25/09/2006