Wednesday, June 24, 2015

ተናገሩ ድንቅ ስራዉንም መስክሩ

"ተናገሩ ድንቅ ስራዉንም መስክሩ"
ከአዲስ አበባ 650 ኪሎ ሜትር መጓዝ ግድ ይላል ታላላቅ የገጠር ከተሞች አሉ በተለይ ከጊቤ በረሃ እንደተሻገርን ግራና ቀኝ አይናችንን እንዲንከራተት ፈቀድንለት ወሊሶ፣ ወልቂጤ፣ ጅማ፣ በደሌ፣መቱን እንዳለፍናት ጎሬ ስንደርስ አንድ ሐውልት ከቤተክርስቲያኑ በር አካባቢ በግርማ ሞገስ ተሸፍኖ ቆሟል፡፡




"ብጹዕ አቡነ ሚካኤል"
ይባላሉ ፋሽስት ኢትዮጵያን በወረራት ጊዜ ልክ እንደ አቡነ ጴጥሮስ በተመሳሳይ ጊዜ ህዝቤም መሬቱም አይገዛልህ ብለው በማውገዛቸው በግፍ በመትረየስ ተረሽነዋል ተገድለዋል፡፡ሰኔ23
ከፓትሪያርኩ ጀምሮ ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት የሐውልት
ምርቃትና የሰማዕትነትን ስም ያገኛሉ፡፡
ይህንን በረከት ለመሳተፍ ከመላው ኢትዮጵያ በርካታ ህዝብ ከየአካባቢው ይጎርፋል፡
እኛም ተገኝተን ሰፊውን ታሪክ ያኔ እናቀርባለን፡፡
የኢሉባቡር ሀገረ ስብከት ይህንን ታላቅ በዓል
ሐይማኖቱንና ታሪኩን የሚወድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ
እንዲገኝ ጥሪ አቅርበዋል፤ይኸው ይድረሳችሁ፡፡

በተለይ ጅማን ይዛችሁ የኢሉባቡር ክልል በግራና
በቀኝዎት ጥቅጥቅ ያለው ደን የተለያዩ የዕጽዋት
ዘር ያለበት ሲሆን በተለይ አመቱን መሉ በአረንጓዴ የተሸፈነው እጅግ ውብና ማራኪ ስፍራ፦ ቀረሮ፣ሰሳ፣ዋንዛ፣ማንጎ፣አቡካዶ፣ቡና፣በቆሎ የመሳሰሉት ተክሎች ይገኙበታል፤
አንዳንዴም እንደው የራበው
መንገደኛ ጫካ ውስጥ ገባ ብሎ ቢወጣ የእለት ጉርሱን አያጣም ይባላል፡፡
አሁን ትንሽ ጉዞ ነው የቀረን ጉመሮ ሻይ ቅጠል ሰፊ የእርሻ መሬት ላይ ደርሰናል
"የመስሊሟ ታሪክ ጀመረ"
፦የዛሬ 3ወር እዚህ ቦታ ላይ
14ሰው የተፈቀደለት ዶልፊን መኪና የዛን ዕለት ግን
27ሰው ጠቅጥቆ ከመቱ ወደ ኡካ ከተማ ጉዞ ጀመረ ፀሐይ ለጨረቃ ፈረቃዋን ቀይራለች ጭለማው በርትቷል የመኪናው ከፍተኛ ፍጥነት ቀጥሏል ከምሽቱ 1ሰዓት ግን ፊለፊቱ ቢራ የጫነ የጭነት መኪና ጋር ፊት ለፊት ተገናኙ ያኔ ነበር እጅግ የአመቱ ዘግናኝ አደጋ ነው የተከሰተው 11ሰዎች ወድያው ላይመለሱ አንቀላፉ ፤ከባድ ጉዳት የደረሰባቸውም አካላቸውን አተዋል ታዲያ "አዋጉ ሠኢድ ኢመማ"
አምቡላንስ እስኪመጣ ከ11አስክሬን ጋር ቅጠል
አልብሰዋት ከሞቱት ጋር ተቆጠረች፤በቆይታ በኋላ
ፊቷ በደም ቢሸፈንም የተረፈው አንድ አይኗ እንደመንቀሳቀስ ሲል የአምፑላንሱ ሹፌር ድንገት
አይቷት ከሞቱት መካከል ለያት ወደ መቱ ሆስፒታል
ሄደች አልተቻለም በኮንትራት መኪና አዲስ አበባ
ጥቁር አምበሳ ሆስፒታል ታከመች፤ እንደ እድል ሆኖ
የተሰበረው እግሯን ሳይጠግኑላት በሚያሳዝን ሁኔታ
ወደ መንደሯ ተመለሰች፡፡
3ወር ሙሉ አትናገርም አትጋገርም ተኝታ ብቻ ማቃሰት መወራጨት ብቻ በሙስሊሞች ባህል ሁሉን አረጉላት መፍትሔ የለም፡፡
አንድ ነገር ቤተሰብ ተማከሩ ይሄ ነገር አንደበቷን የቆለፋት ሰይጣን ሳይሆን አይቀርም ብለው ወደ ቤተክርስቲያን አመሩ አባቶችንም አናግረው ወደ
ቤታቸው ጸሎት እንዲደረግላቸው ተማጸኑ
የቅዱስ ገብርኤልን ጸበል ቤተሰቦቿ በጀሪካን ይዘው
ቀሲስ ትህትና ደግሞ ዳዊታቸውን ሸክፈው አመሩ፡፡
እንግዲህ ሂዱና አህዛብን ሁሉ "በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃቹኃቸው" ያዘዝኳችሁን ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራቹኃቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፡፡
እነሆ እኔ እስከ ዓለም ፍፃሜ ድረስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ፡(ማቴ 28፥28)
እንደ ስርዓተ ቤተክርስቲያን ከዳዊት፣ውዳሴ ማርያም፣ ኪዳንና ትምህርተ ኀቡአት ካዳረሱ በኋላ
ጸበል እረጯት ጆሮዋም እየተከፈተ መጣ ለካ ከመኪናው በወደቀችበት ሰዓት አጅሬ ሰይጣን አግኝቷታል፡፡
ቀሲስ በሥላሴ ስም በድንግል ማርያም
ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እያሉ በመስቀል ይዳብሷታል ኡኡኡ እለቃለሁ አጋንንት ነኝ ጂኒ ነኝ መስቀሉ አቃጠለኝ,,,,,,ቄሱም እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቤተሰብ "አንደበቷ መከፈቱ "ለነሱ እንደ ተአምር ነው በልባቸው ለገብርኤል ተስለዋል::
አሁን ልቀቅ አታሰቃያት ይሉታል ለቅቄ ወዴት እሄዳለሁ? በተረፈው አንድ ዓይኗ ወደ ቄሱ እያፈጠጠ
እያጓራ አንተላይ ወጥቼ ልምጣ እያለ መፎከር ጀመረ መሪጌታ ቀሲስ ትህትና፡ የእሷን ሰላም ማግኘት
እንጂ የአጋንንቱ ዛቻ አላስፈራቸዉም፤ግድ የለም
በእግዚአብሔር ቃል አሸንፍካለው ና!እያሉ ያናዝዙታል
ዳዊታቸውን ትራስጌዋ ላይ አድርገውላት 4ሰዓት ተኩል ላይ አረፍ ትበል ብለው ወደ ባለቤታቸው
ሱቅ ሄዱ፡፡
ከሱቃቸው ጎን ካለው ሻይ ቤት አረፍ እንዳሉ ኬት
መጣ ሳይባል ትልቅ እባብ ይጠመጠምባቸዋል
እስቲ ለአንድ አፍታ እግራችሁን አስቡት ለዛውም መርዘኛ እባብ ግማሽ አካሉ መሬት ሆኖ የተጠመጠመው አንገቱ ጉልበታቸው ላይ ደርሷል፡፡
" እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንደሚል" ያ ልጅቷ ላይ ሆኖ የፎከረዉ አጋንንት ለካ ተከትሏቸዋል፡፡
"እነሆ እባብና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኃለሁ የሚጎዳችሁም ምንም የለም" (ሉቃ 10፥19)
እንዲህ ስገልጽላቹ ቀላል ይመስላል ቀሲስ እንደ ሰዉ ደካማ ናቸውና እየዘለሉ ለማስለቀቅ ብዙ ታግለው ከሳቸው ለቆ ወደ ሚስታቸው ሱቅ እንደተላከ ህፃን የተሳበ ሲገባ አንድ የሻይ ቤቱ ባለቤት ሙስሊም በዱላ ጨፍጭፎ ገደለው፡፡
ወድያው ለሙስሊሞቹ ተነገራቸው በስልክ
(ማሽ አላህ ማሽ አላህ) ተመስገን ለፈጣሪ ምስጋና ይገባው እያሉ የቄሱን እምነት አደነቁ
እኔም ይህ ተአምር ከተከሰተ ከ3ቀን በኋላ ለቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በዓል እዛ ከተማ ተገኝቼ ስለነበር ሁሉንም ታሪክ ከሙስሊሞቹ ሰምቻለሁ፡፡
አንደበቷ የተከፈተውንም አውርቻታለው የምታዩትን ፎቶ አነሽቻታለው በመስቀል በቅባ ቅዱስ ቀሲስ እየጸለዩላት፡፡
ባለፈው የፉጡማ ጂብሪል አዲስ የኦርቶዶክስ እንግዳ ብያቹ ነበር፤ ልክ ነኝ
፨አሚራ የምትባለው ከSISI ነፍሰ በላዎችን መርጣ ወደ ሞት መንገድ ሄደች(ተቀላቀለች)ልብ ይስጥልን፤
፨ፋጡማ ጂብሪል ደግሞ በጥምቀት ወደ ዘላለም ህይወት ሰላምን መርጣ የሥላሴ ልጅነት አገኘች ህይወት የሆነውን የኢየሱስ የክርስቶስን አማናዊ ቅዱስ ስጋውንና አማናዊ ክቡር ደሙን ተቀበለች ዛሬ ማንም የማይቀማትን በጎ እድልን መርጣለችና ለእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ ሆነች፡፡በፎቶ ላይ እንዳያችሁት በሰንበት ትምህርት ቤት መዘመር ጀምራለች፡፡ ሁለቱ ወንድምና እህቶችም ከፉጡማ
ቀደም ብለው ወደ ክርስትናው ገብተዋል፦እንድሪስ መሐመድና አይሻ መሐመድ ናቸው፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን ቀጣይ አንግዶቼ ይሆናሉ፡፡
የፋጡማ አዲስ ስሞ" ናርዶስ ጂብሪል"
"ስመ ክርስትናዋ ወለተ ሰማዕት"
ምስጋና ፦በአገልግሎት አብረውኝ የነበሩ ቀሲስ ታምራት
መ/ር ኤርምያስ አሰፉ፡ መ/ር መላኩ፣ለሰበካ ጉባኤ
ለሰንበት ትምህር ቤተ መዘምራን ለማህበረ ቅዱሳን፣
ለግርማና ለኡካ ነዋሪዎች ይሁን፡፡አሜን!!!
share በማድረግ ሐይማኖቶን ይመስክሩ፡፡
ለማንኛውም መረጃ ወይም አስተያየት በ Viber- what'sup ቁጥር 0911652083 መልእክት ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡ቸር እንሰንብት,,,,

Wednesday, June 10, 2015

የወሊሶ ቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ምእመናን የተፈወሱባት የወሊሶ ቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ቅዳሴ ቤት ይከበራል አትም ኢሜይል
ግንቦት 8 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
01w
በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በወሊሶ ከተማ የምትገኘው የቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ሕንፃ ግንባታ ተጠናቅቆ ቅዳሴ ቤቱ ግንቦት 20 እና 21 ቀን 2007 ዓ.ም. ቅዱስ ፓትርያርኩ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን በተገኙበት በድምቀት እንደሚከበር የገዳሙ አስተዳደር ገለጸ፡፡
የወሊሶ ቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም በ1971 ዓ.ም. በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የተመሠረተች ሲሆን፤ በ1996 ዓ.ም. በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ የሕንፃ አሰሪ ኮሚቴ በማዋቀር ግንባታው ቢጀመርም በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታው ዘግይቶ በዐሥር ዓመቱ ሊጠናቀቅ እንደቻለ አስተዳሩና የሕንፃ አሰሪ ኮሚቴው ገልጸዋል፡፡

የቤተ ክርስቲያኑን ዲዛይን በማኅበረ ቅዱሳን ባለሙያዎች ተሰርቶ ቀድሞ የነበረውን ዲዛይን በድጋሚ ማስተካከያ በማድረግ የወረዳ ማእከሉ ባለሙያዎች በቅርበት እየተከታተሉት ለሁለተኛ ጊዜ በተዋቀረው ሕንፃ አስሪ ኮሚቴ አማካይነት ሊጠናቀቅ ችሏል፡፡

01ww01wy
የገዳሙ መሥራች የሆኑት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ /መምህር ወልደ ትንሣኤ ግዛው/ የሕይወት ታሪካቸው እንደሚያስረዳው መጋቢት 21 ቀን 1911 ዓ.ም. በቀድሞው በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ የተወለዱ ሲሆን፤ በ1921 ዓ.ም. ከግብፃዊው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ዲቁና፤ ነሐሴ 24 ቀን 1933 ዓ.ም. በደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ምንኩስናን፤ በ1940 ዓ.ም. በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ከኢትዮጵያዊው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ቁምስና፤ ግንቦት 30 ቀን 1979 ዓ.ም. በብፁዕ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ኤጲስ ቆጶስ ሆነው ተሹመዋል፡፡
በአዲስ አበባ በቀጨኔ መድኃኔዓለም፤ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም፤ በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ፤ በድሬደዋ ቅዱስ ሚካኤል፤ በሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጅጅጋ፤ ኦጋዴን እና አሰበ ተፈሪ ካገለገሉባቸው አድባራትና ገዳማት ውስጥ ይጠቀሳሉ፡፡ በ1946 ዓ.ም. ወደ ቀድሞው ጨቦና ጉራጌ አውራጃ፤ በአሁኑ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ወሊሶ /ግዮን/ ከተማ በመምጣት አሁን ገዳሙ በሚገኝበት ቦታ ላይ መሬት በመግዛት አዳራሽ ሠርተው ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው ጸጋ በአጋንንትን የተያዙ ሕሙማን እየፈወሱ ቆይተዋል፡፡ አገልግሎታቸው ወደ ቀድሞው ንጉሥ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ በመድረሱ የያዙትን ቦታ አስፍተው እንዲያገለግሉ መሬት እንዲሰጣቸው አድርገዋል፡፡

በ1971 ዓ.ም. የሚያገለግሉበት አዳራሽና ሰፊውን ቦታ በደርግ እንደሚነጠቁ የተረዱት ብፁዕነታቸው በሚያገለግሉበት አዳራሽ ጽላት በማስገባት ቤተ ክርስቲያኗ ተመሠረተች፡፡

01www01wwww
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ከ10 ሚሊዮን በላይ ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በአጋንንት የተያዙ ሕሙማንን ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው ሀብተ ፈውስ እንደፈወሱ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

ብፁዕነታቸው ጥር 18 ቀን 1989 ዓ.ም. ዐርፈዋል፡፡
ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ግንቦት 20 እና 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በቅዱስ ፓትርያርኩ ተባርኮ ጽላቱ የሚገባ ሲሆን፤ ዓመታዊ የእመቤታችን የንግስ በዓል በድምቀት እንደሚከበር ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ምእመናን በዚህ ታሪካዊና የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ሲከናወንበት በነበረው ገዳም ተገኝተው የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ የገዳሙ አስተዳደርና ሕንፃ አስሪ ኮሚቴ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

Monday, June 8, 2015

እሙሀይ ብርሐን - ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም

በዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም 【በቤተክርስታን ቅፅር ግቢ ውስጥ የሚኖሩት 】እሙሀይ ብርሐን እናታችን የተሰጣቸው ፀጋ በጣም ለሰሚው ጆሮ በጣም ሊከብድ ይቻላል እናታች በቤተክርስታን ቅፅር ጊቢ መኖር ከጀመሩ ከ30 ዘመናት በላይ ሆኗቸዋል በነዚህ ዘመናት ባዶ ሜዳ ላይ ተቀምጠው ☞ ዝናብ ሲዘንብ እሳቸው የተቀመጡበት ቦታ ደረቅ ሆኖ እሳቸውንም ሆነ የተቀመጡባትን አካባቢ ዝናብ አያገኘውም እሙሀይ በዚህ ሲኖሩ የሚመገቡት ቱልት የተባለውን ቅጠል ሲሆን እናታችን ብዙ ተማዕራትን በተለያየ ግዜ ሲያደርጉ በአካባበው ምዕመናን ታይተዋል ከዚህ አልፎ በዋልድባ ገዳም የሚኖሩ አባቶች ከሰማይ በቀስተደመና አምሳል ከሰማይ ብርሐን ሲወርድላቸው አይተው መጥተው የእሙሀይን በረከት በረከትዎ ይድረስብን እናታችን ብለው እጅ ነስተዋል የእናታችን በረከት በጣም አስገራሚ እና አስደናቂ ነው እሰኪ ሁላችንም የእሙሀይ ብርሐን በረከት በየአለንበት ይድረሰን እሙሀይንም በቦታው ተገኝተን የበረከቷ ተካፍይ ያድርገን።



Wednesday, June 3, 2015

የቅዱስ ገብርኤል ጽላት በአንድ አባት ራእይ ተገኘ



ታላቅ የምስራች!!
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአለልቱ ወረዳ ልዩ ስሙ ቁምጤ በተባለ አካባቢ የአብሳሪው ቅዱስ ገብርኤል ጽላት፣ ልዩ የፀበል ቦታና ሌሎች የብራና መፃሕፍት በአንድ ቅዱስ አባት ራእይ( ህልም) አማካኝነት ተገኝቷልና መጥታችሁ ጎብኙ። አካባቢው ከመዲናችን አ.አ 55 km ወጣ ብሎ የሚገኝ ቅርብ ቦታ ስለሆነ መጥታችሁ የበረከቱ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናቀርባለን።
እባካችሁ ይህን መልዕክት ለሌሎች በማካፈል ለሁሉ እንዲደርስ የበኩላችንን አስተዋፅኦ እናድርግ


 በአለልቱ አካባቢ ስለተገኝ የቅዱስ ገብርኤል ጽላት አጭር መረጃ (ለማታውቁት)፦ ዕለቱ ስኞ ግንቦት 24 /2007 ዓም የተክልዬ የበአል ቀን ነበር። በነገራችን ላይ አለልቱ ማለት የአባታችን ተክለኃይማኖት የትውልድ ቦታ እና የበርካታ አብያተ ቤተ ክርስትያናትና ገዳማት መገኛ ወረዳ ናት። እናም እኝህ በፎቶው ላይ የምታዩዋቸው ባህታዊ አባት የመጡት ከሌላ አካባቢ ሲሆን በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ በህልም (በራእይ) ተገልፃላቸው ወደዚህ አካባቢ በመምጣት ፅላቱ የተገኘበት ቦታ ላይ ሄደው ቁፋሮ እንዲጀመር ያዛሉ። ሆኖም ግን ያው እንደምናውቀው አንዳንድ የኃይማኖት መሪዎችና መናፍቃንን ጨምሮ ጥቂት ሰዎች " አባ ምን ነካቸው ይቃዣሉ እንዴ " እያሉ በጥርጣሬ ሲያሟቸውና ሲሳለቁባቸው ነበር። ነገር ግን ከጥቂት ሰአታት በኋላ እግዚአብሔር ለሁሉም ያስደመመና ያስደነገጠ ልዩ ተአምራቱን አሳየ። እጅግ ግዙፍ ከሆነ ድንጋይ ሥር በጥንታዊ ቆዳ የተጠቀለለና ልዩ መአዛ ያለው ጽላትና የብራና መፅሐፍ ተገኘ። የፀበል ቦታውንም ጭምር። በዚህ ሰአት ቦታው የመንገድ ዳርቻ (አስፋልት) ስለሆነ መንገደኛ ሁሉ ከመኪናው እየወረደ ሁኔታውን ለማየት ይጎርፍ ጀመር። ከመቅፅበትም ሌላ ጉድ ታዬ።

በአለልቱ ከተማ በአባታችን በአባ ገብረ ሕይወት ራዕይ ከተገኘው የቅዱስ ገብርኤል ፅላት ጋር አብሮ የተገኘው 600 አመታትን ያስቆጠረው የብራና መጽሐፍ ይህ ነው። የመለዓኩ ቅዱስ ገብርኤል በረከት በሁላችን ይደር። ቅዱስ ገብርኤል ይጠብቃችሁ።