Wednesday, April 23, 2014

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ድንቅ ተአምር በግብጽ ቤ/ክ

     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የተደረገ ተአምር ይህ ነው::

ለዓይኖቻችን በጣም አስፈላጊ የሆነው ክፍል የእይታ ድራብ ረቲና የሚባለው ነው:: እይታ ድራብ የሌለው ሰው አንዳችም ነገር ማየት አይችልም:: በመሆኑም ዓይነ ስውር ሆኖ ተወለደ ማለት ነው:: እንዲህ አይነቱ አብሮ የሚወለድ በሽታ ሊድን አይችልም:: ማሪና ከተወለደች ከጥቂት ቀናት በኋላ ወላጆቿ ወደ እርሷ ሲቀርቡ ትደናገጥና ማልቀስ ትጀምራለች:: አንድ ቦታ ላይ አትኩራ አለመመልከቷንና ዓይኖችዋ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴን አለመከተላቸውን ወላጆቿ ይገነዘባሉ:: በአጠቃላይ ዓይኖቿ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የላቸውም::

     አራት ወር ሲሞላት ወደ ሕክምና ተቋም ትወሰዳለች:: የምርመራውም ውጤትም በዓይኖቿ ውስጥ የ እይታ ድራብ ስለሌለ ዓይነ ስውር ሆኖ መቀጠል እንዳለባት ያረጋግጣል:: የማሪና ወላጆች ከሌሎች ብዛት ያላቸው የሕክምና ባለሙያዎች ጋር ለንደን ድረስ ሔደው በመገናኘት ቢያስመረምሯትም እይታ ደራብ ስለሌላት ልትድን አለመቻሏን ደግመው ያረጋግጡላቸዋል::

   ከአማላጂቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ቅርርብ ያላቸው የማሪና ወንድ አያት በዚህ ጉዳይ ክፉኛ ያዝናሉ:: ከዚያም ዘይቱን ውስጥ ወደሚገኘው ወደ እመቤታችን ቤተ ክርስቲያን በቀጥታ በመሄድ በስዕሏ ፊት ተንበርክከው በእናቱ አማላጅነት ተደግፈው እግዚያብሔር የልጅ ልጃቸውን ዓይኖች ያበራ ዘንድ በጸሎት ይማጸኑታል:: በጸሎታቸው "የብርሃን እናት ሆይ: ልጅሽ ማሪና ይህን ብርሃን ሳትመለከት እንድትኖር አታደርጊያትም" ይሉ ነበር:: በዚህ ጊዜ አንዲት እማሆይ ትከሻቸውን ነካ ካደረገቻቸው በኋላ በርኅራሄ ቃል "ልቅሶህ ይብቃ! ማሪናን ያዝና ወደ ሴቶች ገዳም ሂድ" ትላቸውና ከዓይናቸው ትሰወራለች::

    ከዚህ በኋላ የማሪና አያት ድንቅ የሆነ የሰላም ስሜት ሲያድርባቸው ይታወቃቸዋል:: አስቀድመው ይህ ገዳም መኖሩን ፈጽሞ ሰምተው ስለማያውቁ ወደዚያ ያቀኑት አቅጣጫውን እየጠየቁ ነበር;; ከቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በመውጣትም ላይ ሳሉም ወደ

Saturday, April 19, 2014

ትንሳኤን በተመለከተ መልክት ከ መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ

 መምሕር ግርማ በሙኒክ የበራቸው ኣገልግሎት እና ውጣ ውረዶች
ከሙኒክ  ደ/ብ/ ቅዱስ ገብርኤል ሰበካ ጉባኤ የተሰጠ መግለጫ



























 የኣዘጋጅ ኮሚቴው ምላሽ




24.10.2014 በ ሙኒክ የተደርገ የብሶት ሰልፍ


የመምህር ግርማ ወንድሙ መልክት በራዲዩ አቢሲኒያ




Sunday, March 30, 2014

ባሕታዊ አባ ገብረ ጊዮርጊስ

ባሕታዊ አባ ገብረ ጊዮርጊስ በቦሌ አየር ማረፊያ ደ/ፀ/ቅ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የተደረጉ የስብከት እና የፈውስ አገልግሎት

Holy water at Entoto Kidane Mihret Church የ እንጦጦ ኪዳነምህረት ጸበል

Thursday, March 20, 2014

ሰበር ዜና - ሕገ ወጥ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን "መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ" በሚል ስያሜ የተበተነው ደብዳቤ ሕገ ወጥ በመሆኑ የሚመለከተው ሁሉ ይህን ግንዛቤ እንዲወስድ አሳሰበች፡፡
በሚል ከዚህ ጋር ተያይዞ የወጣውን እና የተሰራጨውን ደብዳቤ አስነብበናል:: አሁን ከ ከ ቅዱስ ፓትሪያሪኩ  http://www.eotc-patriarch.org/#
 ድኅረ ገጽ በወጣው መግለጫ ደብዳቤው ጥንቃቄ እንዲደረግበት ማሳሰቢያ ተሰጥቷል:: ደብዳቤው ከታች እንደምትመለከቱት ነው::
የቀድሞውን ደብዳቤ በተመለከተ መምህር ግርማ በሬድዮ አቢሲኒያም ሆነ ተከታታይ በወጡት VCD 26 እና 27 ላይ የተናገሩት ነገር የለም:: ደብዳቤውም ወጣ የተባለበት ከአመት በላይ ያለፈው ግዜ 05/19/2005 በዚህ ጉዳይ ላይ መምህር ግርማ ያረጋገጡልን ነገር የለም:: ስለዚህ ይህን አይነት ድርጊት እየሰራ የመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙን ስም ለማበላሸት የሚጥሩ ስላሉ እርሳቸውን ተጠያቂ ከማድረግ እንድንቆጠብ እናሳስባለን:: ሰሞኑን የርሳቸው ቭኢዲዮ ከነድረገጹ ሁሉ በማጥፋት የ እግዚያብሔር ስራ እንዳይተላለፍ እንቅፋት የሆኑ እንዳሉ የምናውቀው ነው:: ከ ሁለት ደርዘን በላይ ምስሎች አሁን በ ንቁ ተአምረ ጽዩን ማየት የሚቻለው የተወሰኑንት ብቻ ነው::

ይህ ድረ ገጽ የተሳሳተ መረጃ በማቅረብ አላስፈላጊ መደነጋገር ውስጥ ስለከተትን ይቅርታ እንጠይቃልን::  የመምህር ግርማ አገልግሎት መስፋፋት እና የሕዝቡን መዳን ስለምንወድ አገልግሎታችንን ከበፊቱ ይልቅ የተጠናከረ እንዲሆን እንተጋለን:: 

መዝ 119: 121 "ፍርድንና ጽድቅን ሠራሁ፤ ለሚያስጨንቁኝ አሳልፈህ አትስጠኝ።"