Tuesday, September 30, 2014

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ?

የኢንተርኔት አገልግሎት ፈጣን ባልሆነበት ቦታ በአማራጭነት ይህንን በጽሑፍ መልክ ያንብቡ:: ረጅም ትምሕርት ሲሆን በተቻለ መጠን በቂ መልክቱን በጽሑፍ አቅርበናል:: የቃላት ግድፈት ካለ እያረሙ እንዲያነቡ እንጋብዛለን::
የጸሎት ቦታ እንዴት ላዘጋጅ?

ክፉንና ደጉን ለመለየት አምልኮ ያስፈልጋል:: አምልኮ የሌለበት ህይወት አለም ላይ የወደቀ ነው ስለዚህም የአምልኮት ራእይ አንድ ክርስቲያን ሊኖረው ይገባል:: ማምለክ ማለት እግዚያብሔርን ከልብ መውደድ: ቃሉን በልቦና ማኖር: እና መጠበቅ: እርሱን ተስፋ ጉልበታችንን ማድረግ ነው:: በተግባር ደግሞ ኑሮን ጠባይን ለእግዚያብሔር መስጠት: ውስጣዊ ህይወታችንን ለክብሩ የተዘጋጀ ማድረግ :: ስለ ሐጢአታችን ንሰሐ ገብተን ሥጋውና ደሙን መውሰድ: እለት እለት ስለበደላችን ስለሐጢአታችን ለእግዚያብሔር መንገር:: እለት እለት እግዚያብሔርን የምናመሰግንበትን ግዜ ካገኘን የአምልኮት ሕይወት ገበና አለን ማለት ነው:: ሰብአ ሰገል ክርስቶስን በፍቅር ፈልገው እንደመጡ አንድ ክርስቲያንም ክርስቶስን ፈልጎ መምጣት አለበት:: በአምልኮት ባሕርይ ሔሮድስን ማለፍ ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ነው:: ሔሮድስ ማለት የዚህ አለም ነገሮች ናቸው እነዚህም :የአለምን ሰዎች እውቀት: ሳይንስ እግዚያብርሔን የሚከለክል : የድንግል ማርያም ልጅ ክርስቶስን የሚከለክል ነው:: ሔሮድስ ማለት ሐብት : ስልጣን: ማዕረግ የመሳሰሉት እነዚህ ሁሉ የሔሮድስ መንገድ ጠቋሚ ናቸው:: ሰዎች የጥፋት ሞት ውስጥ የሚገቡት የአምልኮት ሕይወት በማጣት ነው:: እግዚያብሔርን የሚፈልጉ ሰዎች ሔሮድስ ጋር መቅረት የለባቸውም:: ኮከቡን ማየት አለባቸው ኮከቡም ያለው በሰማይ ነው::

ብዙ ክርቲያኖች ወደ እግዚያብሔር ቤት አይሔዱም ወይም ወደ ሰማይ ቀና አይሉም:: በዚህም ወደ ልባቸው የሚሔድባቸው መጣባቸው:: ሰይጣን ወደ ቤታቸው ወደ ኑሮአቸው ወደ ሕይወታቸው መጣ:: በዚህ ዓለም ገለልተኛ ሆኖ መኖር አይቻልም:: በዚህ አለም ሁለት ነገር ነው ያለው:: ጽድቅና ኩነኔ: ጨለማና ብርሃን: ሓጢአትና ጽድቅ: ሰላምና ጦርነት::ከፈለክ ወደ ብርሃን ካልፈለክ ወደ ጨላማ: ከፈለክ  እውነት ካልፈለክ ሐሰት: እንዲህ በጥንድ የተያያዘ ነው:: የእግዚያብሔርን በቅድምያ ከሰማን የእግዚያብሔር ጽድቅ ይገለጥልናል: የሰዎችን ከሰማን ሁል ግዜ እንደተደናገግርን ተስፋችንን በአልሆነ አቅጣጫ እየጠበቅን እንኖራለን:: ሔሮድስ ክፉ መሆኑን የምናውቀው ስናመልክ ነው::

የጸሎት ቦታ
የጸሎት አቅጣጫ ምስራቅን የተመለከተ መሆን አለበት:: በመንበርከክ በግንባር ልክ የእመቤታችን የቅዱስ ሚካኤል የቅዱስ እና የቅዱስ ገብርኤል በግራና ቀኝ : በመቆም ልክ የስላሴ የመድኃኔአለም ስእል ይደረጋል:: ከስእሉ ራቅ የሚባለው ክፍተቱ የመጽሐፍ መግለጫ ያህል ነው:: ስእሎቹ ተጸልዮባቸው ቅባ ቅዱስ ይቀባሉ ቢቻል ቤተ ክርስቶያን ተባርካው በቅዳሴ ግዜ ቅባ ቅዱስ ተቀብተው መሆን አለበት:: ስእሎቹ በጥሩ ፍሬም የተሰሩ ስእሎች መሆን አለባቸው:: ከስራቸው የጸሎት ወሃ : እጣን: እምነት:የወይራ ዘይት: የመጽሀፍ ማስቀመጫ: የምንጠቀምባቸው እንደ ሽቶ ዎች ካሉ አጠገብ መሆን አለባቸው:: ሽቶ የሚወዱ ዛሮች አሉ:: ተጸልዮበት ሽቶ ብንጠቀም ሽቶ የሚወዱ ዛሮችን መከላከል ይቻላል : የመንበርከኪያ ቦታ ደረቅ ያለ የጥጥ ፍራሽ ቢሆን ይመረጣል:: ግልበት በሚሰግድበት ግዜ መመቻቸት አለበት ነገር ግን በጣም የሚመች ሥፕንጅ መሆን የለበትም: ስንፍና እንዳይሰማው: የሚሞቅ ነገር መሆን የለበትም መቀዝቀዝም የለበትም:: በሚሰግድበት ግዜ በስእሎቹ ፊትለፊት  መስገድ ሲጀምር የሚከተሉትን ምልክቶች ያያል:- መዛል:መድከም መልፈስፈስ :: በሚጸልይበት ግዜ ከስእሎቹ የሚወጣ መንፈሳዊ እሳት አለ:: በሰውነቱ ላይ ከስእሎቹ ተጠግቶ ሲጸልይ መውረር መቅበጥበጥ:ማቃጠል የሚታይበት ይሆናል:: አንዳንዱም መንፈሱ ወዲያው መገለጥ ጠባይ አለው:: መንፈሱ ጸሎት በከፍተኛ ሁኔታ ጸሎት እየከለክለው የሚያጠቃው ከሆነ የቅዱስ ሚካኤልን ስእል በፍሬም በጥሩ ሁኔታ ሰርቶ  መሬቱ ላይ አድርጎ እጁ ላይ እና ሰይፉ ላይ በሚሰግድበት ግዜ መንፈሱ ሊጥለው ይችላል:: በዚህ ግዜ መቁጠርያ ያስፈልጋል::ጸጥ በል በጌታየ በየሱስ ክርስቶስ ስም ብሎ ሲመታው ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እሰርልኝ ሲለው  በስእሉ ፊት ያለው ሐይል እየተገለጠ ቅዱስ ሚካኤል ሊያስርለት ይችላል:: ሰውየው እየሰማም እያወቀም መንፈሱን ሊያስርለት ይችላል:: በዚህ ግዜ ፕሮግራም ይዞ ወድ  እኔ ደውሎ አንዳንድ መረጃ እንለዋወጣለን:: የሚደክም ከሆነ ይደክማል የሚሸኝም ከሆነ ይሸኛል:: ሆኖም ግን  እነዚህን ልምምዶች በቀላሉ የሚመጡ  አደሉም:: ሰውየው በጥሩ የበረከት መንፈሳዊ ህይወት ለማለፍ እራሱን ማዘጋጀት አለበት:: ጸሎትን እንደ ደስታ አምላክን እንደማማረርያ ጎዳና ሳይሆን "ሁል ግዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ:ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ::ገርነታችሁ ለሰው ሁሉ ይታወቅ::" እንዲል ገራገር መሆን አለበት:: "ጌታ ቅርብ ነው::በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ::" ፊልጵስዮስ 4:4-6

ራእይን ምሪቱን ለማግኘት ደግሞ የጸሎት ቦታችን ላይ ለባልና ሚስት የመኝታ ያህል መኖር አለበት: ቤተሰብ ካለው ከሌለው

Tuesday, August 19, 2014

ከእጇ ዘይት የሚፈልቅ የቅድስት ኤልሳቤጥ አስገራሚ ታሪክ

ወንድሞቼ እና እህቶቼ ይህንን ድንቅ ተአምር ስናገር እግዚአብሔር ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ እመቤታችንም ምን ያህል ክብርት እንደሆነች እያደነቅሁ ነዉ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነዉ ይህች የምትመለከቷት ቅድስት የድሮ ስሟ ሳሚያ ዮሴፍ ባሲሊዮስ ትባላለች፡፡ የቅርብ ጊዜ ቅድስት ናት ያረፈችውም 6 ወር በፊት ነዉ፡፡ ከእጇ ዘይት የሚፈልቅበት ምክንያቱ እንዲህ ነዉ፡፡ይህች ሴት በኃጥያት ትኖር ነበር(በሕይወቷ ቤተ ክርስትያን የሔደችዉ ልጇን ክርስትና ልታስነሳ ነበር) ሴት ልጇ ደግሞ ወደ ቤተክርስትያን ትሄዳለች ልጅቷ ስለእናቷ ወደ ቤተክርስትያን እንድትሔድላት ትጸልይ ነበር እናትየዋ በቀን 60 ሲጋራ ከማጨሷም በላይ ልጅቷን ልትመታት ትደርስ ነበር በቤቱ የአቡነ ሺኖዳ ስብከት ከተከፈተ ንዴቱ ይብስባት ነበር ዘፈን ከሆነ ግን ደስታውን አትችለውም፡፡ልጅቷ ግን መፀለይዋን አላቋረጠችም እንደውም ንስሐ አባቷን እያመጣች ልታስመክራት ስትሞክር ፈቃደኛ አልነበርችም፡፡ነገር ግን ንስሐ ተስፋ አልቆረጡም እንደውም በቅዳሴ ጊዜ ስሟን ጠርተዉ ስለፀለዩላት በሌላ ቀን ሲመጡ ተቀበለቻቸዉ ከመግባታቸዉ በፊት በሩ ላይ የመስቀል ምልክት አድርገዉ ነበር፡፡ከዚያ ለምን ወደ ቤተከርስትያን አትመጪም ሲሏት ቤተክርስትያን ያሉት ሰዎች ጥሩ አይደሉም ምክንያቱም ቅዱስ ቁርባን ተቀብለናል ብለዉ ግን ደግሞ ይተማማሉ አንዱ ላንዱ ጥሩ ጥሩ አይመኙም ብላ ለካህኑ ነገረቻቸዉ እርሳቸውም ልጄ ኃጥያተኛም እንዳለ ሁሉ ጻድቃንም አሉ ስለዚህ ጻድቃኖችንም ማየት ይኖርብናል ብለዉ ነገሯት ከዚያም ልጇ ከትምህርት ቤት ስትመጣ የእናቷን እና የካህኑን ውይይት ስታይ ደነገጠች ተደሰተችም ከዚያም ዓርብ ቤተክርስትያን እንድትሔድ ቃል አስገባቻት(ዓርብ ያለችበት ምክንያት ግብፅ ውስጥ ዓርብ በሙስሊሞቹ ምክንያት ሰለሚዘጋ እሁድ ደግሞ በክርስያኖቹ ምክንያት ስራ ዝግ ነዉ፡፡ቅዳሜ የስራ ቀን ነዉ፡፡

ከዚያም ዓርብ ደርሶ ቤተክርስትያ ሄዱ ቅዳሴዉ ሲጀመር እናትየዋ ማልቀስ ጀመረች ሙሉ ቅዳሴውን እስኪያልቅ ታለቅስ ነበር፡፡ካህኑ ቅዳሴውን በዓረብኛ ነበር የቀደሰዉ በኮፕት ቋንቋ ከቀደሰ ግን ቋንቋ ከቀደሰዉ ገና ከጅምሩ ላይገባት ስለሚችል ብሎ

የዘማሪ አለማየሁ ኡርጌ ምስክርነት- በፀበል ኃይል ከሞት መዳን

ዘማሪ አለማየሁ ኡርጌ ከአገልግሎት መልስ ባላወቀው ሁኔታ ከባድ ሕመም አጋጠመው::ያጋጠመው ሕመም ግን መፍትሔ እንደሌለው እና እግሩ መቆረጥ እንዳለበት ተነገረው:: በፀበል ኃይል እግዚያብሔር ያደረገለትን ድንቅ ተዓምር ከምስለ ወድምጹ ይከታተሉ::

 

ወንቅእሸት - ሙት አንሳው- ቅዱስ ገብርኤል ገዳም
ሸንኮራ ዩሐንስ ጸበል; አንጀት ካንሰር; ፍቅርተ; የእግር እብጠት

Wednesday, July 30, 2014

ድንቅ ተዓምር በሸንኮራ ቅዱስ ዩሐንስ ጸበል


የተወደዳችሁ የእግዚያብሔር ቤተሰቦች ዛሬ የምንመሰክራላችሁ ተዓምር ለወንድም አንተነሕ ኃይሌ የተደረገለት ሲሆን: ይህ ወንድም በ2005 ዓ.ም ታሞ ወደ ሕክምና ጣቢያ በመሔድ ምርመራ ያደርጋል:: ነገር ግን ውጤቱ አስደንጋጭ ብሎም ያልተጠበቀ ነበር:: የሕክምና ዶክተሩ የአንጀት ካንሰር እንዳለበት ይነግሩታል:: ይህ ብቻ አደለም ሌላ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ነገርም ነገሩት እርሱም በዚች አለም በህይወት ሊቆይ የሚችለው ቢበዛ ለ 3ወር ብቻ እንደሆነም ጭምር ያስረዱታል:: በዚህም አስደንጋጭ ዜና ተስፋ መቁረጥ ቢደርስበትም የተለያዩ ሆስፒታሎች ጋር በመሔድ የሕክምና እርዳታን ይሞክር ጀመር:: ለምሳሌ ኮርያ ሆስፒታል: ተክለሐይማኖት ሆስፒታል: ብሩክ ክሊኒክ ላንድ ማርክ እና ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከሔደባቸው የተወሱኑ የሕክምና ጣቢያዎች ሲሆኑ የተሻላ ነገርን ግን ማግኘት አልቻለም:: በስተመጨረሻ ላይ ግን ወደ እግዚያብሄር መፍትሔዎች አዳኝነት በመመለስ በሸንኮራ ዩሐንስ ጸበል በመጠጣት የእግዚያብሔር አዳኝነትን መጠባባቅ ያዘ:: በዚህ አመት ባደረገው ምርመራ በአሁኑ ግዜ በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ ሲሆን "የካንሰር ስፔሻሊስት" እና የቅዱስ ዩሐንስ ሸንኮራ ጸበል ረድተውኛል" ሲል ቃል በቃል ተናግሯል:: ከዚህ በታች በምታዩት ፎቶ ላይ ዶክመንቶቹን እያሳየ እንዳለ እናያለን::

"እግዚያብሄር በጻድቁ እንደተገለጠ እወቁ..":: መዝ 4:3




Friday, April 25, 2014

ከአፄ ዋሻ ማርያም ገዳም የተሰረቀው ታቦት ከጅቡቲ በተዓምራት ተመለሰ



የእስራኤልን አምላክ ታቦት ስደዱአት፤ እኛንና ሕዝባችንን እንዳትገድል በስፍራዋ  ትቀመጥ፡፡ /1ኛ ሳሙ. 5፤ 12/
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በደብረ ብርሃን አካባቢ ከአፄ ዋሻ ማርያም ገዳም የተሰረቀው የመድኀኔዓለም ታቦት ከጅቡቲ በተዓምራት ተመለሰ፡፡

ከአፄ ዋሻ ማርያም ገዳም የተሰረቀው የመድኀኔዓለም ታቦት ጅቡቲ ውስጥ ለ17 ዓመታት በአንድ ግለሰብ ቤት ተደብቆ ከቆየበት ተዓምራቱን በመግለጡ በተደናገጠው ቤተሰብ ጠቋሚነት፤ ጅቡቲ ለሚገኘው ለምሥራቀ ጸሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን  በማስረከብ ሚያዚያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ተመልሷል፡፡

“በ1938 ዓ.ም. የተቀረጸውና በአፄ ዋሻ ማርያም ገዳም የነበረው የመድኀኔዓለም ታቦት ሐምሌ 28 ቀን 1989 ዓ.ም. የቤተ ክርስቲያኑን በርና መስኮት ተሰብሮ  መሰረቁን ለወረዳው ቤተ ክህነትና ለፖሊስ በወቅቱ አሳውቀን ነበር፡፡ ለማፈላለግ ያደረግነው ጥረት ሁሉ መና ሆኖብን ቆይቷል፡፡ እግዚአብሔር በወደደ ጊዜ ወደ ቤቱ ይመለስ ዘንድ ፈቀደ፡፡” ይላሉ የገዳሙ አስተዳዳሪ ቄስ ኃይለ ጊዮርጊስ መኮንን፡፡

ጅቡቲ እንዴት እንደተወሰደ እስካሁን በግልጽ የታወቀ ነገር እንደሌለ የሚገልጹት የጅቡቲ ምሥራቀ ጸሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስስቲያን አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ዮናስ መልከ ጼዲቅ “ታቦቱ በግለሰቡ ቤት ታላቅ ተዓምራትን ነው ያደረገው፡፡ በቤቱ ውስጥ ደብቆ ያስቀመጠው ግለስብ ሚስት ስታብድ ልጁ ሞቶበታል፡፡ በዚህ የተደናገጠው ሌላው የሰውየው ልጅ በቤታቸው ውስጥ ታቦት እንዳለና ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲወሰድ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ጉዳዩን በመከታተል ከጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲና ከሌሎችም ጋር መረጃ በመለዋወጥ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ችለናል” ብለዋል፡፡

ምንጭ

Wednesday, April 23, 2014

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ድንቅ ተአምር በግብጽ ቤ/ክ

     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን:: በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የተደረገ ተአምር ይህ ነው::

ለዓይኖቻችን በጣም አስፈላጊ የሆነው ክፍል የእይታ ድራብ ረቲና የሚባለው ነው:: እይታ ድራብ የሌለው ሰው አንዳችም ነገር ማየት አይችልም:: በመሆኑም ዓይነ ስውር ሆኖ ተወለደ ማለት ነው:: እንዲህ አይነቱ አብሮ የሚወለድ በሽታ ሊድን አይችልም:: ማሪና ከተወለደች ከጥቂት ቀናት በኋላ ወላጆቿ ወደ እርሷ ሲቀርቡ ትደናገጥና ማልቀስ ትጀምራለች:: አንድ ቦታ ላይ አትኩራ አለመመልከቷንና ዓይኖችዋ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴን አለመከተላቸውን ወላጆቿ ይገነዘባሉ:: በአጠቃላይ ዓይኖቿ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የላቸውም::

     አራት ወር ሲሞላት ወደ ሕክምና ተቋም ትወሰዳለች:: የምርመራውም ውጤትም በዓይኖቿ ውስጥ የ እይታ ድራብ ስለሌለ ዓይነ ስውር ሆኖ መቀጠል እንዳለባት ያረጋግጣል:: የማሪና ወላጆች ከሌሎች ብዛት ያላቸው የሕክምና ባለሙያዎች ጋር ለንደን ድረስ ሔደው በመገናኘት ቢያስመረምሯትም እይታ ደራብ ስለሌላት ልትድን አለመቻሏን ደግመው ያረጋግጡላቸዋል::

   ከአማላጂቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ቅርርብ ያላቸው የማሪና ወንድ አያት በዚህ ጉዳይ ክፉኛ ያዝናሉ:: ከዚያም ዘይቱን ውስጥ ወደሚገኘው ወደ እመቤታችን ቤተ ክርስቲያን በቀጥታ በመሄድ በስዕሏ ፊት ተንበርክከው በእናቱ አማላጅነት ተደግፈው እግዚያብሔር የልጅ ልጃቸውን ዓይኖች ያበራ ዘንድ በጸሎት ይማጸኑታል:: በጸሎታቸው "የብርሃን እናት ሆይ: ልጅሽ ማሪና ይህን ብርሃን ሳትመለከት እንድትኖር አታደርጊያትም" ይሉ ነበር:: በዚህ ጊዜ አንዲት እማሆይ ትከሻቸውን ነካ ካደረገቻቸው በኋላ በርኅራሄ ቃል "ልቅሶህ ይብቃ! ማሪናን ያዝና ወደ ሴቶች ገዳም ሂድ" ትላቸውና ከዓይናቸው ትሰወራለች::

    ከዚህ በኋላ የማሪና አያት ድንቅ የሆነ የሰላም ስሜት ሲያድርባቸው ይታወቃቸዋል:: አስቀድመው ይህ ገዳም መኖሩን ፈጽሞ ሰምተው ስለማያውቁ ወደዚያ ያቀኑት አቅጣጫውን እየጠየቁ ነበር;; ከቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በመውጣትም ላይ ሳሉም ወደ

Saturday, April 19, 2014

ትንሳኤን በተመለከተ መልክት ከ መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ

 መምሕር ግርማ በሙኒክ የበራቸው ኣገልግሎት እና ውጣ ውረዶች
ከሙኒክ  ደ/ብ/ ቅዱስ ገብርኤል ሰበካ ጉባኤ የተሰጠ መግለጫ



























 የኣዘጋጅ ኮሚቴው ምላሽ




24.10.2014 በ ሙኒክ የተደርገ የብሶት ሰልፍ


የመምህር ግርማ ወንድሙ መልክት በራዲዩ አቢሲኒያ




Sunday, March 30, 2014

ባሕታዊ አባ ገብረ ጊዮርጊስ

ባሕታዊ አባ ገብረ ጊዮርጊስ በቦሌ አየር ማረፊያ ደ/ፀ/ቅ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የተደረጉ የስብከት እና የፈውስ አገልግሎት

Holy water at Entoto Kidane Mihret Church የ እንጦጦ ኪዳነምህረት ጸበል

Thursday, March 20, 2014

ሰበር ዜና - ሕገ ወጥ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን "መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ" በሚል ስያሜ የተበተነው ደብዳቤ ሕገ ወጥ በመሆኑ የሚመለከተው ሁሉ ይህን ግንዛቤ እንዲወስድ አሳሰበች፡፡
በሚል ከዚህ ጋር ተያይዞ የወጣውን እና የተሰራጨውን ደብዳቤ አስነብበናል:: አሁን ከ ከ ቅዱስ ፓትሪያሪኩ  http://www.eotc-patriarch.org/#
 ድኅረ ገጽ በወጣው መግለጫ ደብዳቤው ጥንቃቄ እንዲደረግበት ማሳሰቢያ ተሰጥቷል:: ደብዳቤው ከታች እንደምትመለከቱት ነው::
የቀድሞውን ደብዳቤ በተመለከተ መምህር ግርማ በሬድዮ አቢሲኒያም ሆነ ተከታታይ በወጡት VCD 26 እና 27 ላይ የተናገሩት ነገር የለም:: ደብዳቤውም ወጣ የተባለበት ከአመት በላይ ያለፈው ግዜ 05/19/2005 በዚህ ጉዳይ ላይ መምህር ግርማ ያረጋገጡልን ነገር የለም:: ስለዚህ ይህን አይነት ድርጊት እየሰራ የመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙን ስም ለማበላሸት የሚጥሩ ስላሉ እርሳቸውን ተጠያቂ ከማድረግ እንድንቆጠብ እናሳስባለን:: ሰሞኑን የርሳቸው ቭኢዲዮ ከነድረገጹ ሁሉ በማጥፋት የ እግዚያብሔር ስራ እንዳይተላለፍ እንቅፋት የሆኑ እንዳሉ የምናውቀው ነው:: ከ ሁለት ደርዘን በላይ ምስሎች አሁን በ ንቁ ተአምረ ጽዩን ማየት የሚቻለው የተወሰኑንት ብቻ ነው::

ይህ ድረ ገጽ የተሳሳተ መረጃ በማቅረብ አላስፈላጊ መደነጋገር ውስጥ ስለከተትን ይቅርታ እንጠይቃልን::  የመምህር ግርማ አገልግሎት መስፋፋት እና የሕዝቡን መዳን ስለምንወድ አገልግሎታችንን ከበፊቱ ይልቅ የተጠናከረ እንዲሆን እንተጋለን:: 

መዝ 119: 121 "ፍርድንና ጽድቅን ሠራሁ፤ ለሚያስጨንቁኝ አሳልፈህ አትስጠኝ።"

Thursday, February 27, 2014

መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ ተሰጣቸው

ከዚህ በፊት መምህር ግርማ ወንድሙ ከ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አገልግሎት መታገድ በተያያዘ የቀድሞው የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አስተዳዳሪ መላከ ሰላም ዘላለም እሰይ ስለ መምህር ግርማ ምን ይላሉ? በሚል አገልግሎታቸው የተቋረጠበትን መልካም ያልሆነ ድርጊት እና የመምህር ግርማ ወንድሙን እውነተኛ ማንነት የሚያስረዳ ቃለምልልስ አስደምጠን ነበር:: ከታች በተያያዘው ደብዳቤ ላይ መላከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፍቃድ የተሰጣቸው መሆኑን ያሳያል::
ደብዳቤው እንደሚከተለው ይነበባል
ቀን 26/12/2005
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ የወንጌል አገልግሎትና እንዲሁም የሕሙማን ሐብተ ፈውስ እንዲሰጡ ከብጹዕ ወቅዱስ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልካም ፍቃድ የተፈቀደልዎት ሲሆን ይህን አውቀው በፍቅር በሰላም እንዲያገለግሉ እናስታውቃለን::
በክርስቶስ ሰላም
ተጨማሪ መረጃ
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13144
መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ ማናቸው?

VDC part 26 ወጥቷል::

የቀድሞው የእገዳ ደብዳቤ

በሮም ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የተላከ ደብዳቤ 25/09/2006